Paster yoseph official Macaafa Qulqulluu💒


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Inglizcha
Toifa: Din


❍ Tajaajila Channel Kanaan dhiyaatu:
Âť Barnoota Amantii Cimsannaa
Âť Dhugaa Wangeelaa
Âť Ergaa Ganamaa
Âť Leenjiilee Hafuuraa
Âť Ergaa Dargaggootaa
Âť Qo'annaa Macaafa Qulqulluu
Âť Faaruu Ganamaa
Âť Kitaabilee hafuuraa PDF fi kan kana fakkaatanidha
► Join

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Inglizcha
Toifa
Din
Statistika
Postlar filtri


አድርጎናል። ስለሆነም፥ እኛም ከልጁ ከክርስቶስ ጋር አብረን ወራሾች ነን (ሮሜ 8፡17)። ከመወለዳችን በፊት እንኳን እግዚአብሔር ልጆቹ፥ የመንግሥቱ ሕጋዊ ወራሾችና የመንግሥተ ሰማይ አባላት እንደምንሆን ወስኗል። በምድር ላይ ምንም ያህል ድሆች ብንሆንም፥ በሰማይ የነገሥታት ንጉሥና የጌቶች ጌታ ልጆች ነን። ሰማያዊ ስፍራችን በምድር ላይ ካለው ከማንኛውም የንጉሥ ልጅ የላቀ ነው።
ጳውሎስ ለእግዚአብሔር ምርጫ ምን ያህል ትልቅ አጽንኦት እንደ ሰጠ ልብ በል። እግዚአብሔር ለእያንዳንዳችን ይህን ዕድል የሰጠን በበጎ ፈቃዱ እንደ ወደደ ለጸጋው ክብር ምስጋና ነበር። እግዚአብሔር የመረጠን ልዩ ስለሆንን ወይም አንድን ታላቅ ተግባር ስላከናወንን አልነበረም። ይህ ምርጫ ከእግዚአብሔር ፈቃድ የመነጨ ነው። እግዚአብሔር የመረጠን ለእኛ ባለው ፍቅርና ለጸጋው ምስጋና ነው።
የውይይት ጥያቄ፡- ሀ) የእግዚአብሔር ሕጋዊ ልጅ መሆን አስደናቂ የሚሆነው እንዴት ነው? ይህ ልጅነት የሚያስገኝልህን መልካም ዕድሎች ዘርዝር። ለ) እግዚአብሔር በቸርነቱ ልጁ እንድትሆን ስለመረጠህ አሁኑኑ አመስግነው።
ሐ. እግዚአብሔር በክርስቶስ ደም ዋጅቶናል፤ የኃጢአት ይቅርታም ሰጥቶናል። ቤዛ የሚለው ቃል ባሪያዎች ከሚሸጡበት ገበያ የተወሰደ ነው። በገበያ ላይ አንድ ሰው ለአንድ ባሪያ ካዘነለት ሊገዛውና ሰንሰለቱን ፈትቶ በነፃ ሊለቅቀው ይችል ነበር። ይህ ሰዎችን ነፃ ለማውጣት የሚካሄድ ግዥና ሽያጭ ቤዛነት ይባል ነበር። በተመሳሳይ ሁኔታ እኛም የኃጢአትና የሰይጣን ባሪያዎች እንደ ነበርን መጽሐፍ ቅዱስ ይናገራል። ክርስቶስ ግን በሞቱ ለኃጢአታችን ዋጋ በመከፈል ሊገዛንና ነፃ ሊያወጣን ችሏል። በእግዚአብሔር ላይ የፈጸምነውን ኃጢአት ሁሉ ይቅር አለን። ይህ እግዚአብሔር በቸርነቱ በእኛ ላይ ያወረደው ጸጋ ምሳሌ ነው። ይህን ለምን አደረገ? ከፍቅሩ እንደ መነጨ ከመናገር በቀር ሌላ የምንረዳው ነገር የለም። ይህ የተደረገው የእግዚአብሔርን ታላቅ ጥበብና አሳቢነት በሚያሳይ መልኩ ነበር።
መ. እግዚአብሔር የፈቃዱን ምሥጢር አስታወቀን። በአዲስ ኪዳን «ምሥጢር» የሚለው ቃል የእግዚአብሔርን ስውር ምሥጢር ሳይሆን፥ ቀደም ሲል በከፊል ሳይገለጥ የቆየውንና አሁን ግን ለሰው ልጆች የተገለጠውን የእግዚአብሔርን ፈቃድ ነው። ጳውሎስ እግዚአብሔር እስከ አዲስ ኪዳን ዘመን ሳይገልጥ ያቆያቸውን ነገሮች ለመግለጽ በኤፌሶን ውስጥ ምሥጢር (ስውር) የሚለውን ቃል በተደጋጋሚ ተጠቅሟል። በብሉይ ኪዳን ከተሰወሩትና አሁን ግን በጳውሎስ በኩል ከተገለጡት ምሥጢሮች አንዱ፥ እግዚአብሔር ነገሮችን ሁሉ በክርስቶስ የመጠቅለሉ ጉዳይ ነው። ሰማይና ምድር ለእግዚአብሔር ክብር በሚሰጡበት መልክ ይዋሃዳሉ። ይሄ ሁሉ ግራ መጋባት፥ ኃጢአት፥ ዓመፅ ሁሉ ተወግዶ ሰማይና ምድር በኢየሱስ በኩል ለተፈጠሩበት ተግባር ይውላሉ።
ሠ. እግዚአብሔር በሉዓላዊ ምርጫው ለክብሩ ምስጋና መርጦናል። ከጥንቱ ዘመን የአዳዲስ ክርስቲያኖች ማስተማሪያ መጻሕፍት አንዱ፥ «የሰው የኋላ ኋላ መጨረሻው ምንድን ነው?» ሲል ይጠይቃል። መልሱ፥ «እግዚአብሔርን ማክበርና ለዘላለም በእርሱ ደስ መሰኘት» የሚል ነው። ድነት (ደኅንነት) ከእግዚአብሔር አንጻር ሲታይ ቀዳሚ ዓላማው እኛን ማዳን ሳይሆን፥ እግዚአብሔር እንዲመሰገን ነው። የዓመፀኛ ኃጢአተኞች መዳን በሆነ ምሥጢራዊ መንገድ ለእግዚአብሔር ታላቅ ክብርን ያመጣል። ሞት የሚገባን ኃጢአተኞች ሆነን ሳለ እግዚአብሔር እንዳዳነን ስንገነዘብ፥ እግዚአብሔርን ለአስደናቂ ሥራው እናመሰግነዋለን።
ረ. እግዚአብሔር ተስፋ በተገባው መንፈስ ቅዱስ አትሞናል። «እርሱም የርስታችን መያዣ ነው፥ ለእግዚአብሔር ያለንን ሁሉ እስኪዋጅ ድረስ. . .»ጳውሎስ ስለ መጨረሻው መንፈሳዊ በረከት (ለእግዚአብሔር ልጆች ሁሉ መንፈስ ቅዱስ ስለ መሰጠቱ) ከመናገሩ በፊት፥ ድነትን ከሰው እይታ አንጻር ይመለከታል። ስናምን ምን ይሆናል? ጳውሎስ በክርስቶስ ውስጥ እንደምንካተት ገልጾአል። በመንፈሳዊ ሁኔታ ከክርስቶስ ጋር እንዋሃዳለን። በክርስቶስ ውስጥ ሆነን እግዚአብሔር በሰማይ የሚሰጠንን በረከቶች ሁሉ እንቀበላለን። ጳውሎስ አስፈላጊው ነገር እምነት ብቻ ሳይሆን የምናምነው ነገር ጭምር መሆኑን አስረድቷል። እምነት ብቻውን አያድነንም። እምነታችን፥ በትክክለኛ ነገር ላይ ሊሆን ይገባል። ጳውሎስ «በእውነት ቃል» ማመን እንዳለብን ገልጾአል። የኤፌሶን ሰዎች አምነው የዳኑት በዚህ የወንጌል እውነት ነበር።
ጳውሎስ ማብራሪያውን እግዚአብሔር ከሚሰጠን እጅግ ጠቃሚ በረከቶች በአንዱ ይደመድማል። ይኸውም በእያንዳንዱ ክርስቲያን ልብ ውስጥ መንፈስ ቅዱስ ማደሩ ነው። ጳውሎስ ስለ መንፈስ ቅዱስ አገልግሎት ያተኮረባቸውን ነገሮች አስተውል።
1. ጳውሎስ መንፈስ ቅዱስ እንደ «ምልክት» ወይም እንደ ፊርማ መሆኑን አስረድቷል። በገዛነው መጽሐፍ ላይ ፊርማ ስናስቀምጥ መጽሐፉ የእኛ ንብረት እንደሆነና ማንም ሰው ያለ እኛ ፈቃድ ሊወስደው እንደማይችል መግለጻችን ነው። በተመሳሳይ ሁኔታ እግዚአብሔርም መንፈስ ቅዱስን ሲሰጠን የእርሱ መሆናችንን ለሰዎች ሁሉ መናገሩ ነው።
2. መንፈስ ቅዱስ ለውርሳችን ዋስትና የሚሰጥ መያዣ ነው። አንድ ሰው አንድን ነገር ለመግዛት ፈልጎ በቂ ገንዘብ በሚያጣበት ጊዜ ቀብድ ይከፍላል። ቀብዱ የቀረውን ገንዘብ አምጥቶ ዕቃውን እንደሚገዛ የሚያረጋግጥ የተስፋ ቃል ወይም መያዣ ሆኖ ያገለግላል። በሰዎች ዓቅም የቀረውን ገንዘብ ከፍሎ ዕቃውን መውሰዱ አስቸጋሪ የሚሆንበት ሁኔታ ሊያጋጥም ይችላል። በእግዚአብሔር ዘንድ ግን እንደዚህ አይደለም። እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን ሲሰጠን አንድ ቀን ወደ መንግሥተ ሰማይ እንደሚያስገባን ተስፋ መግባቱ ነው። መዋጀታችንን የምናጠናቅቅበት ጊዜ ይሆንና በእግዚአብሔር መንግሥት ለእኛ የሚሰጠንን ርስት የምንወርስ ተካፋዮች እንሆናለን።
እግዚአብሔር ይህን ልዩ በረከት የሰጠን ለምንድን ነው? ጳውሎስ ለክብሩ ምስጋና እንደሆነ ይገልጻል።
የውይይት ጥያቄ፡- ሀ) ጳውሎስ ስለ መንፈስ ቅዱስ አገልግሎት የሰጠው ማብራሪያ ብዙውን ጊዜ እኛ ስለ መንፈስ ቅዱስ ከምናስበው እንዴት ይለያል? ለ) እግዚአብሔር ወደ ሰማይ እንደሚወስደን የሚያስረዳው የተስፋ ቃል በምድር ላይ ካሉን በረከቶች ሁሉ የሚልቀው እንዴት ነው፥
(ማብራሪያው የተወሰደው በ ኤስ.አይ.ኤም ከታተመውና የአዲስ ኪዳን የጥናት መምሪያና ማብራሪያ፣ ከተሰኘው መጽሐፍ ነው፡፡ እግዚአብሔር አገልግሎታቸውን ይባርክ፡፡)


በክርስቶስ የሚገኝ መንፈሳዊ በረከት (ኤፌ. 1፡1-14)
ሁሴን በሙስሊም ቤተሰብ ውስጥ ነበር ያደገው። ነገር ግን ትምህርቱን በመከታተል ላይ ሳለ ከሌላ ተማሪ ስለ ክርስቶስ ወንጌል ሰማ። ወንጌሉን አምኖ ስለተቀበለ ቤተሰቦቹ ወዲያውኑ ከቤት አባረሩት። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ተማሪ በነበረባቸው ጊዜያት ከአንድ ክርስቲያን ቤት ወደ ሌላው እየተዘዋወረ ሲቸገር ኖረ። የሁለተኛ ደረጃ ትምህርቱን ካጠናቀቀ በኋላ ሥራ ይዞ ራሱን እንደሚያስተዳድር ተስፋ ያደርግ ነበር። ነገር ግን ሥራ ባለማግኘቱ ኑሮው ትግል የበዛበት ሆነ። ቡቱቶ ልብሱን ለብሶ ወዲያ ወዲህ ማለት አሳፈረው። በዚህ ጊዜ ክርስቶስን ለመከተል መወሰኑ ትክክል ስለመሆኑ ያመነታ ጀመር።
የውይይት ጥያቄ፡- ሀ) ለክርስቲያኖች በድህነት ውስጥ በደስታ መኖር አስቸጋሪ የሚሆነው ለምንድን ነው? ለ) ኤፌ. 1፡3-14 አንብብ። ክርስቲያኖች በሰማያዊ ስፍራ የተባረኩባቸውን ነገሮች ዘርዝር። ሐ) የበለጠ ጠቀሜታ ያላቸው ምድራዊ በረከቶች ናቸው ወይስ መንፈሳዊ የሰማይ በረከቶች? ለምን? መ) ክርስቲያኖች ድህነት ወይም ስደት በሚደርስባቸው ጊዜ መንፈሳዊ በረከቶቻቸውን ማስታወስ የሚያስፈልጋቸው ለምንድን ነው?
ብዙዎቻችን እግዚአብሔር በብዙ ምድራዊ በረከቶች ይባርከናል ብለን እናስባለን። አንዳንድ ጊዜ እንደዚያ ያደርጋል። ብዙውን ጊዜ ግን አማኞች ከገንዘብ፥ ከበሽታና ከሌሎችም ሁኔታዎች ጋር የተያያዙ ችግሮች ያጋጥሟቸዋል። ጳውሎስ ለኤፌሶን ሰዎች በጻፈው መልእክት እግዚአብሔር ድነትን (ደኅንነትን) ባገኘን ጊዜ ምን ዓይነት በረከቶችንና ዋስትና እንደሰጠን ግልጽ አድርጓል። ጳውሎስ በቁሳዊ በረከቶች ላይ ከማተኮር ይልቅ እግዚአብሔር ለልጆቹ ሁሉ የሚሰጣቸውን መንፈሳዊ በረከቶች እንድናስታውስ አበረታቶናል። ማንም ሰው ሊወስድብን በማይችላቸው በእነዚህ ዘላለማዊ መንፈሳዊ በረከቶች ልንበረታታ ይገባል።
፩) መግቢያ (ኤፌ. 1፡1-2)
ጳውሎስ በመልእክቶቹ ሁሉ በእግዚአብሔር ፈቃድ የክርስቶስ «ሐዋርያ» ሊሆን መብቃቱን ይናገራል። የኤፌሶን ክርስቲያኖች የጳውሎስን ሐዋርያነትና ሥልጣን ስላልተጠራጠሩ፥ ጳውሎስ በዚህ ጉዳይ ላይ ለገላትያ ቤተ ክርስቲያን የጻፈውን ያህል አጽንኦት አላደረገም (ገላ. 1፡1)።
ጳውሎስ መልእክቱን የጻፈው «በኤፌሶን ላሉት ቅዱሳን በክርስቶስ ኢየሱስም ላሉት ምእመናን» ነበር። «ኤፌሶን» የሚለው ቃል በመጀመሪያው የጳውሎስ መልእክት ውስጥ ስለመኖሩ ምሁራን የሚከራከሩ መሆኑን በአንደኛው ቀን ትምህርት ተመልክተናል። ይህ ለኤፌሶን ብቻ ሳይሆን በእስያ ለሚገኙ አብያተ ክርስቲያናት የተላከ ተዘዋዋሪ ደብዳቤ ሊሆን ይችላል። ኤፌሶን እጅግ አስፈላጊና በቀዳሚነት መልእክቱን የተቀበለች ቤተ ክርስቲያን በመሆኗ፥ ቀደምት ምሁራን «ኤፌሶን» የሚለውን ቃል ጨምረው ይሆናል።
እነዚህ ክርስቲያኖች ከዓለም የተለዩና ለክርስቶስ በታማኝነት የኖሩ ስለነበሩ፥ የወቀሳ አሳቦች አልተሰነዘሩም። ጳውሎስ እንዲለውጡ የጠየቃቸው አስተምህሮዎች ወይም ልምምዶች የሉም። ነገር ግን ጳውሎስ የቀድሞይቱ ቤተ ክርስቲያን የተለማመዳቸውን የጸጋና የሰላም ቡራኬ ሰጥቷል።
፪) የእግዚአብሔር ልጆች መንፈሳዊ በረከቶች (ኤፌ. 1፡3-14)
ዛሬ በምንኖርበት ዘመን ክርስቲያኖች በምድራዊ በረከቶች ላይ ያተኩራሉ። አንዳንድ ክርስቲያኖች በክርስቶስ ካመንን ሀብታሞች እንሆናለን ብለው ያስባሉ። በክርስቶስ ካመንን፥ በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኙትን እውነቶች ከተከተልንና እግዚአብሔር በሚፈልገው መንገድ ከኖርን፥ እግዚአብሔር ብዙውን ጊዜ በቁሳዊ በረከቶች ይባርከናል ይላሉ። አንዳንድ ጊዜ ግን ይህንን አያደርግም። እግዚአብሔር ቢባርከንም እንኳን እነዚህ ምድራዊ በረከቶች ዋነኛ ነገሮች አለመሆናቸውን መጽሐፍ ቅዱስ ያስረዳል። ዋነኞቹ መንፈሳዊ በረከቶች ናቸው።
ጳውሎስ ለቅዱሳን ወይም በክርስቶስ ላሉት ከሁሉም የላቀ በረከት እንደ ተሰጠ አስረድቷል። እነዚህም ምድራዊ በረከቶች ሳይሆኑ፥ ጳውሎስ እንደሚለው በሰማያዊ ስፍራ የሚገኙ ናቸው። ጳውሎስ ብዙውን ጊዜ በምሥጢራዊ መንገድ ከክርስቶስ ሞት፥ ትንሣኤና ዕርገት ጋር መተባበራችንን ሲገልጽ መቆየቱን አንስተናል። በዚህ ስፍራ ጳውሎስ በክርስቶስ ዕርገት ላይ ያተኩራል። ክርስቶስ ወደ ሰማይ ስላረገና እኛም ከእርሱ ጋር ስለተባበርን፥ እግዚአብሔር የሚሰጠን በረከቶችም ያሉት በሰማይ ነው። ከክርስቶስ የተነሣ እነዚህ ሁሉ በረከቶች የእኛ ናቸው። እነዚህ በረከቶች ምን ምንድን ናቸው?
ሀ. እግዚአብሔር በፊቱ ቅዱሳንና ነውር የሌለን እንሆን ዘንድ መርጦናል። ስለ ድነት (ደኅንነት) ስናስብ ብዙውን ጊዜ በሰዎች ሚና ላይ እናተኩራለን፥ በክርስቶስ ስለማመናችንም እንናገራለን። ጳውሎስ ግን ድነት የሚመለከተው ከእግዚአብሔር እይታ አንጻር ነው። እግዚአብሔር በማንረዳው መንገድ በዓለም ውስጥ ከሚገኙ እጅግ ብዙ ዓለማውያን መካከል መርጦናል። ድነት (ደኅንነት) እግዚአብሔር አንተንና እኔን ልጆቹ አድርጎ ከመምረጡ ተግባር ነው የሚጀምረው። የበለጠ የሚገርመው ደግሞ ጳውሎስ ይህ ምርጫ የተካሄደው ከዓለም ፍጥረት በፊት እንደሆነ መናገሩ ነው። አዳምና ሔዋን ከመፈጠራቸው በፊት እግዚአብሔር አንተና እኔ የቤተሰቡ አካላት እንድንሆን መፈለጉን ያውቅ ነበር። ስለሆነም፥ መረጠን።
እግዚአብሔር የመረጠን ድነት እንድናገኝ ብቻ አልነበረም። እኛን የመረጠበት ዓላማ ኃጢአተኞች ብንሆንም እንኳ ተለውጠን እንድንቀደስና በፊቱ ነውር የሌለን እንሆን ዘንድ ነበር። ይህ በሁለት የተለያዩ መንገዶች ይከናወናል። በመጀመሪያ፥ ድነት ስናገኝ እግዚአብሔር ያጸድቀናል ወይም የኃጢአት በደለኞች አለመሆናችንን ያውጃል። የክርስቶስ ደም ኃጢአታችንን ስለሚሸፍን፣ እግዚአብሔር በፊቱ ንጹሐን እንደሆንን አድርጎ ያየናል። እንዲሁም የኢየሱስ ክርስቶስን ጽድቅ ይሰጠናል። የክርስቶስ ጽድቅና ፍጹማዊ ቅድስና የእኛ ጽድቅና ቅድስና ይሆናሉ። በዚህም መንገድ በእግዚአብሔር ፊት ቅዱሳንና እንከን እንደሌለን ሆነን እንታያለን። ነገር ግን ጳውሎስ የሚለው ከዚህም ያለፈ ነው። ሁለተኛ፥ እግዚአብሔር ኃጢአትን በማሸነፍና ክርስቶስን በመምሰል በቅድስና እንድናድግ ይፈልጋል።
ለ. እግዚአብሔር ልጆች እንድንሆን ወስኗል። ሁለተኛው የድነት (ደኅንነት) እርምጃ እግዚአብሔር ከመረጠን በኋላ ልጆቹ ሊያደርገን መወሰኑ ነው። ይህ የእግዚአብሔር አሠራር እኛ ክርስቶስን ለመከተል ከመምረጣችን ወይም ካለመምረጣችን ጋር እንዴት እንደሚጣጣም ሙሉ ለሙሉ ለመገንዘብ አንችልም። ከእግዚአብሔር እይታ አንጻር ግን ደኅንነታችን የሚጀምረው ከእግዚአብሔር ምርጫ ነው። ከዚያም እግዚአብሔር ሁኔታዎችን በመቆጣጠር የመረጣቸውን ሰዎች ልጆቹ እንዲሆኑ ያደርጋል።
እግዚአብሔር እኛን ሲመርጥ ምን ነበር የፈለገው? ጳውሎስ እንደ ልጆቹ ሊያደርገን መፈለጉን ያስረዳል። ምናልባትም ጳውሎስ ስለ ሮም የማደጎ ልጅነት ልማድ እያሰበ ይሆናል። በሮምና በአይሁዶችም ዘንድ፥ አንድ ሰው አንድን ሕፃን በሕጋዊ መንገድ በማደጎነት ለማሳደግ በሚፈልግበት ጊዜ የሚከተለው የማደጎነት ሥርዓት ነበር። ልጁ ከባሪያዎቹ መካከል የአንዱ፥ የድሃ ጎረቤቱ ወይም የወዳጁ ሊሆን ይችላል። ልጁ ከወለዳቸው ልጆች እኩል የሆነ ሕጋዊ የልጅነትና የቤተሰቡ አባልነት መብት ይኖረዋል። ልጁ የማደጎ ልጅነትን መብት ካገኘበት ጊዜ አንሥቶ ከተወላጅ ልጆች ጋር እኩል መብትና የመውረስ ሕጋዊ መብት ይኖረዋል። እኛም ከእግዚአብሔር ቤተሰብ የራቅን የሰይጣን ልጆች ነበርን። ነገር ግን ከእግዚአብሔር ጸጋና ዘላለማዊ ፍቅር የተነሣ እግዚአብሔር ልጆቹ


2. ጳውሎስ የኤፌሶን አማኞች እንደ የክርስቶስ አካል ክፍሎች እንዴት ሊመላለሱ እንደሚገባቸው ያስተምራል (ኤፌ. 4-6)። እግዚአብሔር የባረካቸው ሰዎች እንደ እግዚአብሔር ልጆች መኖር ይጠበቅባቸዋል። እኛ የአንድ አካል ወይም የአንድ ቤተስብ አባላት ስለሆንን፥ በፍቅርና በአንድነት ልንኖር ይገባል። እግዚአብሔር የአካሉን ክፍል በመንፈሳዊ ብስለት ለመገንባት ሲል ለመሪዎች ስጦታዎችን ይሰጣል። አማኞች ሰማያዊ አባታችንን የሚመስል የተቀደሰ ሕይወት መምራት ይኖርብናል። በዚህ ቤተሰብ ውስጥ በፍቅር፥ በሥርዓት፥ በአንድነትና በመቻቻል ልንኖር ይገባል። የክርስቶስንና የቤተ ክርስቲያንን ምሳሌ በመከተል ሚስቶች ለባሎቻቸው ሊገዙ፥ ባሎች ደግሞ ሚስቶቻቸውን ሊወዷቸው ይገባል። በሥራ ቦታ በሠራተኞች (ባሮችን) እና በቀጣሪዎች (ጌቶች) መካከል መከባበር ሊኖር ይገባል። በመንፈሳዊ ውጊያችን ደግሞ ክርስቶስ የሰጠንን የጦር መሣሪያ በመጠቀም ነቅተን ራሳችንን ልንጠብቅ ይገባል።
የኤፌሶን መልእክት አስተዋጽኦ
1. ጳውሎስ ለኤፌሶን ክርስቲያኖች፥ አማኞች በክርስቶስ ማን እንደሆኑና ቤተ ክርስቲያን ምን እንደሆነች ያስተምራል (ኤፌ. 1-3)፡፡
ሀ. መግቢያ (ኤፌ. 1፡1-2)
ለ. የእግዚአብሔር ልጆች መንፈሳዊ በረከቶች (ኤፌ. 1፡3-14)
ሐ. ጳውሎስ አማኞች እንደ እግዚአብሔር ልጆች ያላቸውን መንፈሳዊ ስፍራ እንዲረዱ ይጸልያል (ኤፌ. 1፡15-23)።
መ. ሙት የነበሩ የእግዚአብሔር ጠላቶች በጸጋው ሕያዋን ሆነው ድነዋል (ኤፌ. 2፡1-10)
ሠ. ሁሉም አማኞች ሰብአዊ ክፍፍሎች በማይታሰቡባት አንዲት ቤተ ክርስቲያን ተጠልለዋል (ኤፌ. 2፡11-22)
ረ. ጳውሎስ ስለ ክርስቶስና ቤተ ክርስቲያን የሚናገረውንና የእግዚአብሔር ምሥጢር የሆነውን ወንጌል ለማወጅ የተመረጠ አገልጋይ ነው (ኤፌ. 3፡1-13)
ሰ. ጳውሎስ አማኞች የክርስቶስንና ከእርሱ ጋር ያላቸውን ግንኙነትና ታላቅነት ይረዱ ዘንድ እግዚአብሔር ጉልበት እንዲሰጣቸው ይጸልያል (ኤፌ. 3፡14-21)።
2. ጳውሎስ የኤፌሶን አማኞች ለወንጌሉ እንደሚገባ ይመላለሱ ዘንድ ያደፋፍራቸዋል (ኤፌ. 4-6)።
ሀ. ለወንጌሉ እንደሚገባ መመላለስ ማለት እንደ አማኞች አንድነትን መፍጠርና እርስ በርሳችን መዋደድ ነው (ኤፌ. 4፡1-6)
ለ. እግዚአብሔር የአካሉ ክፍሎች እርስ በርሳቸው እንዲረዳዱና በብስለት እንዲያድጉ የተለያዩ ስጦታዎችን ሰጥቷቸዋል (ኤፌ. 4፡7-16)።
ሐ. እግዚአብሔር ልጆቹ በቅድስና በመመላለስ እርሱን እንዲመስሉ ይፈልጋል (ኤፌ. 4፡17-5፡20)
መ. እግዚአብሔር የቤተሰብ አባላቱ እርስ በርሳቸው እንዴት መዛመድ እንዳለባቸው አብራርቷል (ኤፌ. 5፡21–6፡9)።
ሠ. እግዚአብሔር ልጆቹ ራሳቸውን ከሰይጣን ጥቃቶች እንዲጠብቁና የድል ነሺነትን ሕይወት እንዲመሩ መንፈሳዊ የጦር ዕቃዎችን ሰጥቷቸዋል (ኤፌ. 6፡10-20)
ረ. የመጨረሻ ሰላምታ (ኤፌ. 6፡21-24)
(ማብራሪያው የተወሰደው በ ኤስ.አይ.ኤም ከታተመውና የአዲስ ኪዳን የጥናት መምሪያና ማብራሪያ፣ ከተሰኘው መጽሐፍ ነው፡፡ እግዚአብሔር አገልግሎታቸውን ይባርክ፡፡)


የኤፌሶን መልእክት ዓላማ፣ ልዩ ባሕሪያት፣ መዋቅር እና አስተዋጽኦ
የኤፌሶን መልእክት ዓላማ
በድነት (ደኅንነት) ላይ ከሚያተኩረው የገላትያ መልእክት በተቃራኒ በኤፌሶን ውስጥ የቀረበ ዐቢይ የሐሰት ትምህርት ወይም ችግር አይታይም። የኤፌሶን መልእክት እግዚአብሔር ለአማኞች የሰጠውን በረከትና ከቤተ ክርስቲያን ጋር ያለውን ግንኙነት የሚያብራራ የትምህርት መጽሐፍ ነው። በኤፌሶን ውስጥ ጳውሎስ ስለሚከተሉት ነገሮች ጽፎአል።
ሀ. ክርስቶስ በክፋት ኃይላት ሁሉ ላይ ሥልጣን እንዳለውና ከሰይጣን ጥቃቶች የሚከላከሉ መንፈሳዊ የጦር መሣሪያዎች እንዳሉን (ኤፌ. 1፡20-22፤ 6፡10-18)። አንዳንድ ምሁራን ይህ የመንፈሳዊ ውጊያ ትምህርት የኤፌሶን ዋነኛ ርዕስ እንደሆነ ያስባሉ። የኤፌሶን አማኞች ቀደም ሲል ከፍተኛ የጣዖት አምልኮ ያካሂዱ ስለነበር የሰይጣንን ኃይል ይፈሩ ነበር። ስለሆነም፥ ጳውሎስ የክርስቶስ ኃይል ከሁሉም ኃይላትና ሥልጣናት እንደሚበልጥ ገልጾላቸዋል። እንዲሁም ሁሉም ክርስቲያኖች ክርስቶስ የሰጣቸውን የጦር ዕቃዎች በመጠቀም ሰይጣንን ሊያሸንፉ እንደሚችሉ ያሳያቸዋል።
ለ. ቤተ ክርስቲያን የእግዚአብሔር ዘላለማዊ ዕቅድ እምብርት ነች። ጳውሎስ ቤተ ክርስቲያንን የክርስቶስ አካል (ኤፌ. 1፡23)፥ የእግዚአብሔር ቤተሰብ (ኤፌ. 3፡3)፤ ሕንፃ፤ ቅዱስ መቅደስ፥ የእግዚአብሔር ግዛት (ኤፌ. 2፡21-22)፥ ምሥጢር (ኤፌ. 3፡3)፥ ወዘተ. በማለት ይገልጻታል። ቤተ ክርስቲያን እግዚአብሔር የመረጣቸው፤ የጠራቸውና በመንፈሳዊ ሁኔታ የባረካቸው ሰዎች ክምችት ነች። ቤተ ክርስቲያን የክርስቶስ አካልና (ኤፌ. 1፡22-23) ለታሪክ የወጠነው ዕቅድ መነሣሣት ናት። እግዚአብሔር ከቤተ ክርስቲያን በአይሁዶችና በአሕዛብ መካከል የነበሩትን ዓይነት የዘር ክፍፍሎች አስወግዷል። አማኞች የእግዚአብሔር ታላቅ ቤተሰብ አካል ናቸው። ሁሉን ቻዩ አምላክ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ይኖራል (ኤፌ. 2፡19– 22)።
ሐ. እማኞች በክርስቶስ ያገኟቸው አስደናቂ በረከቶች። ከመዳናችን በፊት ተስፋ የሌለን፥ በኃጢአታችን የሞትንና ያለመታዘዝ ልጆች ነበርን (ኤፌ. 2፡1-4)። እግዚአብሔር ከጸጋው የተነሣ ክርስቶስን በመላኩ በእርሱ በማመን ከርኩሰትና ከቅጣት ነፃ ወጥተናል። አሁን፥ ለእግዚአብሔር ለመኖር የሚያስችል ኃይል እንዳለንና የበረከቶቹ ወራሾቹ እንደሆንን እናውቃለን (ኤፌ. 1፡3-12)። በክርስቶስ ስናምን የቀደመውን ኃጢአታችንን ለመሸፈን የሚያስፈልገንን ነገር፥ እግዚአብሔርን ለማስደሰትና ሰይጣንን ለማሸነፍ የሚያስችለንን ኃይል፥ እንዲሁም የወደፊቱን የበረከት ተስፋዎች እናገኛለን። እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስን ስለሰጠን (ኤፌ. 1፡13)፥ ከኃጢአት መርገምና ከእስራት ወጥተን ወደ እግዚአብሔር ቀርበናል (ኤፌ. 2፡1-10)። አማኞች በአንድነትና በንጽሕና (ኤፌ. 4፡17-6፡9)፥ ወዘተ. ሊመላለሱ ይገባል።
መ. የእያንዳንዱ ክርስቲያንና ቤተ ክርስቲያን ዓላማ ለእግዚአብሔር ምስጋናና ክብር ማምጣት ነው (ኤፌ. 1፡6)።
ሠ. የእግዚአብሔር የመጨረሻ ግብ ክርስቶስን ማስከበርና በሰማይና በምድር ያሉትን ነገሮች ሁሉ በእርሱ ሥልጣን ሥር ማዋል ነው (ኤፌ. 1፡10)።
ረ. አማኞች በሥራ ሳይሆን በእግዚአብሔር ጸጋ እንደ ዳኑ፥ የትኛውም ጎሳዊ ክፍፍል በክርስቶስ ሞት እንደ ተወገደና በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ስፍራ እንደሌለው ለማስታወስ (ኤፌ. 2፡11-22)።
ሰ. ሽማግሌዎች ክርስቲያኖች ሁሉ በመንፈሳዊ ሕይወታቸው እንዲያድጉ በማገዙ በኩል የሚጫወቱት ሚና (ኤፌ. 4፡1-16)።
ሸ. የቤተሰቡ አባላት እግዚአብሔርን በሚያስከብር መንገድ እንዴት እርስ በርሳቸው ሊያያዙ እንደሚገባቸው ለማስተማር (ኤፌ. 4፡1፤ 5፡22-6፡9)።
የውይይት ጥያቄ፡– የቤተ ክርስቲያንህ አማኞች እነዚህን እውነቶች ማወቅና ተግባራዊ ማድረግ የሚያስፈልጋቸው እንዴት ነው?
የኤፌሶን መልእክት ልዩ ባሕርያት
1. የኤፌሶን መልእክት ከቆላስይስ መልእክት ጋር በቅርብ የተዛመደ ነው። ሁለቱም በተመሳሳይ ጊዜ እንደ ተጻፉ ግልጽ ነው። የኤፌሶን ከ50 በመቶ የሚበልጡ ጥቅሶች በቆላስይስ ውስጥ ተደግመዋል። ቲኪቆስ የተባለ ግለሰብ ሳይሆን አይቀርም ሁለቱንም መልእክቶች ያደረሰው (ኤፌ. 6፡21፤ ቆላ. 4፡7-8)። የኤፌሶንም ሆነ የቆላስይስ መልእክቶች በክርስቶስና በቤተ ክርስቲያን ላይ ያተኩራሉ። የኤፌሶን መልእክት ቤተ ክርስቲያን የክርስቶስ አካል መሆኗ ላይ ሲያተኩር፥ የቆላስይስ መልእክት ደግሞ ክርስቶስ የአካሉ ራስ በመሆኑ ላይ ያተኩራል።
2. በዚህ መልእክት ውስጥ ስለ መንፈስ ቅዱስ እያሌ እውነቶች ተጠቅሰዋል። እግዚአብሔር መንፈስ ቅዱስ፣ ቅዱስ (ኤፌ. 1፡13)፥ የጥበብ ምንጭና እውነትን ገላጭ ነው (ኤፌ. 1፡17፤ 3፡5)። መንፈስ ቅዱስ ሊያዝን (ኤፌ. 4፡30)፥ አማኞችንም ሊያትም (ኤፌ. 1፡13)፥ የአማኞች ውርስ መያዣ ሊሆን (ኤፌ. 1፡14)፥ ወደ እግዚአብሔር አብ የመቅረቢያ መንገድ ሊከፍት (ኤፌ. 2፡18)፥ ቤተ ከርስቲያንን ሊያንጽ (ኤፌ. 2፡22)፥ አማኞችን ሊሞላና ሊያበረታታ (ኤፌ. 3፡16፤ 5፡18)፥ ለአማኞች የእግዚአብሔርን ቃል ሊሰጥ (ኤፌ. 6፡17) እና እንዲጸልዩ ሊረዳቸው ይችላል (ኤፌ. 6፡18)።
3. ከሌሎች የጳውሎስ መልእክቶች በተቃራኒ፡ ይህንን መልእክት እንዲጽፍ ያነሣሣው ሁነኛ ምክንያት (የቤተ ክርስቲያን ወይም የአስተምህሮ ችግር) የለውም። ነገር ግን ለአማኞች ጠቃሚ መንፈሳዊ እውነቶችን ለማስተላለፍ የተጻፈ ነው።
4. ጳውሎስ ከእነዚህ እውነቶች አብዛኞቹን በሁለት ታላላቅ ጸሎቶቹ አስተምሯል (ኤፌ. 1፡15-23፤ 3፡14-21)። እነዚህ ሁለት ጸሎቶች ለእርስ በርሳችን ለመጸለይ እንጠቀምባቸው ዘንድ የጸሎት ምሳሌዎች ሆነው ያገለግላሉ።
የኤፌሶን መልእክት መዋቅር
የኤፌሶን መልእክት እንደ አብዛኞቹ የጳውሎስ መልእክቶች በሁለት ክፍሎች የተከፈለ ነው። በመጀመሪያው ክፍል ጳውሎስ በእምነታችን ላይ ተጽዕኖ በሚያሳድሩት መንፈሳዊ እውነቶች ላይ ትኩረት ሲያደርግ፥ በሁለተኛው ክፍል ደግሞ እግዚአብሔርን በሚያስከብር መንገድ እንዴት መመላለስ እንዳለብን ያስተምራል።
1. ጳውሎስ ለኤፌሶን ክርስቲያኖች ጠቃሚ መንፈሳዊ እውነቶችን ያስተምራል (ኤፌ. 1-3)። እንደ አማኞች እኛ ማን ነን? ቤተ ክርስቲያን ምንድን ናት? እነዚህ በመጀመሪያዎቹ የኤፌሶን ሦስት ምዕራፎች ውስጥ መልስ የተሰጠባቸው ዐበይት ጥያቄዎች ናቸው። እንደ አማኞች፥ አስደናቂ መንፈሳዊ በረከቶች በሰማያዊ ስፍራ ተሰጥተውናል (ኤፌ. 1፡3)። እግዚአብሔር በሁሉም ዐበይት የሕይወታችን ክፍሎች በከፍተኛ ደረጃ ባርኮናል። ጠላቶቹ የነበርን ብንሆንም፥ ክርስቶስ እንዲሞትልን ልኮታል። በአስደናቂ ጸጋው አድኖናል።
ቤተ ክርስቲያን ምንድን ናት? ጳውሎስ ቤተ ክርስቲያን በዓለም ውስጥ የእግዚአብሔር ዋነኛ የትኩረት ስፍራ እንደሆነች አስረድቷል። እግዚአብሔር ታላቅ ክብር የሚያመጡለትን የአማኞች ማኅበረሰብ እየመሠረተ ነው። ይህም ማኅበረሰብ ከአይሁዶችና ከአሕዛብ ተውጣጥተው በክርስቶስ ያመኑ፥ ቅዱሳንና የተለዩ ሕዝብ የሚገኙበት ነበር። ይህ በፍቅር፥ አንድነትና ንጽሕና ተለይቶ የሚታወቅና ጎሳዊ እውቅና ከእንግዲህ ወዲህ የማይታይበት ማኅበረሰብ ነው።


ጳውሎስ በወንጌል መልእክተኝነት ጉዞው ከየትኛውም ስፍራ በላይ በኤፌሶን ብዙ ጊዜ ቆይቷል። ጳውሎስ በአሁኗ ቱርክ ውስጥ የነበረችውን ኤፌሶንን እንደ ቁልፍ የአገልግሎት ስፍራ ነበረ የተመለከተው። ኤፌሶንን መናኸሪያ አድርጎ በመጠቀሙ ወንጌል በእስያ አውራጃ ውስጥ በፍጥነት ሊሰራጭ ችሏል (የሐዋ. 19፡10)።
የኤፌሶን ከተማ ዋነኛ የወደብ ከተማና የእስያ አውራጃ መዲና ነበረች። አብዛኛው የንግድ እንቅስቃሴ ከምዕራብ ቱርክ ወደ ኤፌሶን ከመጣ በኋላ ከዚያ ወደ ጥንቱ ዓለም ሁሉ ይሰራጭ ነበር። ጳውሎስ በዚያ በሚሠራበት ጊዜ ቢያንስ የ1100 ዓመታት ዕድሜ የነበራት ጥንታዊ የታሪክ ከተማ ነበረች። ብዙ አይሁዶችና ሌሎችም ከ500,000 የሚበልጡ ሰዎች በከተማይቱ ውስጥ ይኖሩ እንደነበር ይገመታል። በዚያ ከነበሩት አይሁዶች አንዳንዶቹ ወደ ክርስትና እምነት ሲመጡ፥ አብዛኞቹ ግን የወንጌሉ ጠላቶች ሆነው ክርስቲያኖችን ያሳድዱ ነበር።
ኤፌሶን ዳያና በተባለች ጣዖት አምልኮም ትታወቅ ነበር። ዳያና የምትመለክበት ቤተ መቅደስና ሐውልቷ እጅግ አስደናቂ በመሆናቸው ከሰባቱ የጥንቱ ዓለም አስደናቂ ነገሮች እንደ አንዱ እንደሆኑ ተደርገው ይቆጠሩ ነበር። ዳያና የሚለው ሮማዊ ስምም ሆነ አርጤምስ የሚለው የግሪክ መጠሪያ የፍሬያማነትን አምላክ የሚያመለክት ነበር። ሴቶች ዳያናን በማምለካቸው ልጅ መውለድ እንደሚችሉ ይታመን ነበር። ከዳያናና ከሌሎች ጣዖታት በተጨማሪ ኤፌሶን ዋነኛ የጥንቆላና የምትሐት ማዕከል ነበረች። የኤፌሶን ሰዎች በክርስቶስ ካመኑ በኋላ ቢያንስ 350,000 ብር የሚገመቱ የምትሐት መጻሕፍት እንዳቃጠሉ ተነግሮናል። በኋላም የሮም ንጉሥ አምልኮ ከተጧጧፈባቸው ከተሞች አንዱ ኤፌሶን ነበረች። በዚህ ሃይማኖት ንጉሡን ለማምለክ ባለመፍቀዳቸው እንደ ዓመፀኞች በታዩት ክርስቲያኖች ላይ ከፍተኛ ስደት ተከስቷል።
ጳውሎስ መጀመሪያ በኤፈሶን ወንጌልን የሰበከው በሁለተኛው የወንጌል መልእክተኝነት ጉዞው መጨረሻ አካባቢ ነበር። ጳውሎስ ወደ ኢየሩሳሌም ሲሄድ እግረ መንገዱን ከጵርስቅላና አቂላ ጋር ወደ ኤፌሶን ጎራ አለ (የሐዋ. 18፡18-19)። አንድ ጊዜ ለአይሁዶች ከሰበከ በኋላ ሰዎች እንዲቆይ ቢፈልጉም ወደ ኢየሩሳሌም አመራ። ጵርስቅላና አቂላ ግን እዚያው ቆዩ። በዚህ ጊዜ ከመጥምቁ ዮሐንስ ደቀ መዛሙርት አንዱ የነበረው አጵሎስ የሚባለው ወደ ኤፌሶን መጥቶ ማስተማር ጀመረ። ጵርስቅላና አቂላ ስለ ክርስቶስ የበለጠ ካስተማሩት በኋላ አጵሎስ በኤፌሶን ወንጌሉን እንዲያስፋፋ እግዚአብሔር በሚገባ ተጠቀመበት። ነገር ግን ብዙም ሳይቆይ ወደ ቆሮንቶስ ለአገልግሎት ሄደ።
ጳውሎስ በኤፌሶን ዐቢይ የአገልግሎት መሠረት የጣለው በሦስተኛው የወንጌል መልእክተኝነት ጉዞው ነበር። በኤፌሶን ሲሰብክና ሲያስተምር ለሦስት ዓመታት ቆየ። ይህም በየትኛውም የአገልግሎት ጉዞው ካደረጋቸው ቆይታዎች ሁሉ የበለጠ ነበር። ብዙ ሰዎች የንግድ ማዕከል ወደነበረችው ኤፌሶን የንግድ ተግባራቸውን ለማከናወን ሲመጡ ወንጌሉን ይሰብክላቸው ነበር። እነርሱም ወንጌሉን ይዘው ወደመጡበት አገር ይመለሳሉ። ከዚህም የተነሣ ወንጌሉ በእስያ አገሮች ሁሉ ተስፋፋ (የሐዋ. 19፡10)። ምናልባትም በራእይ ውስጥ የተጠቀሱት ሰባቱ አብያተ ክርስቲያናትና የቆላስይስ ቤተ ክርስቲያን የተመሠረቱት በዚህ ጊዜ ሳይሆን አይቀርም። በኤፌሶን አገልግሎቱ መጨረሻ አካባቢ ተቃውሞ እየተጠናከረ በመሄዱ በከተማይቱ ውስጥ ብጥብጥ ተነሣ። ከዚያ በኋላ ብዙም ሳይቆይ ጳውሎስ የግሪክን አብያተ ክርስቲያናት ጎብኝቶ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ።
ጳውሎስ የኤፌሶንን መልእክት የጻፈበት ዘመንና ስፍራ
የውይይት ጥያቄ፡– ኤፌ 3፡1 እና 4፡1 አንብብ። ጳውሎስ መልእክቱን የጻፈው የት ሆኖ ነበር?
ጳውሎስ ይህን መልእክት በጻፈ ጊዜ የሆነ ስፍራ ታስሮ ነበር። ግን የት እንደ ታሰረ? አያሌ ግምቶች አሉ። ቂሣሪያ ወይም ሮም ታስሮ ሊሆን ይችላል። ጳውሎስ ወደ ኢየሩሳሌም ሲደርስ መታሰሩን አስታውሰ። ለጥቂት ጊዜ በኢየሩሳሌም ታስሮ ከቆየ በኋላ ቂሣሪያ ወደተባለችው የሮም የአውራጃ ከተማ ተወስዶ ለሁለት ዓመታት ያህል ታስሯል (የሐዋ. 24፡27)። የእስር ቤት መልእክቶቹን የጻፈው በዚህ ጊዜ ሳይሆን አይቀርም። ከሁለት ዓመታት በኋላ፥ ጳውሎስ በንጉሥ ችሎት ይዳኝ ዘንድ ወደ ሮም ተላከ። እዚያም ለሁለት ተጨማሪ ዓመታት ራሱ በተከራየው ቤት ታስሮ ቆየ (የሐዋ. 28፡30-31)። አብዛኞቹ ምሁራን ጳውሎስ አራቱን የወኅኒ ቤት መልእክቶች ሮም ሆኖ በ60 ወይም 61 ዓ.ም እንደ ጻፈ ያምናሉ።
(ማብራሪያው የተወሰደው በ ኤስ.አይ.ኤም ከታተመውና የአዲስ ኪዳን የጥናት መምሪያና ማብራሪያ፣ ከተሰኘው መጽሐፍ ነው፡፡ እግዚአብሔር አገልግሎታቸውን ይባርክ፡፡)


ይህንን የአማኞች መሰባሰብ የእግዚአብሔር «ቤተ መቅደስ» ወይም የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ ይለዋል (ኤፌ. 2፡21)። ምንም እንኳ ክርስቶስ በእያንዳንዱ ክርስቲያን ልብ ውስጥ ቢኖርም፥ ከዚያ በላቀ ሁኔታ በአማኞች ኅብረት ውስጥ ይኖራል።
ዛሬ ትኩረት የሚደረገው በግለሰቦች ድነት (ደኅንነት) ላይ ነው። የሰዎችን መዳን አለመዳን እንጠይቃለን። ብዙ ሰዎች ለማምለክ ለራሳቸው ብቻ ቃሉን ለመማር ወደ ቤተ ክርስቲያን ይመጣሉ። ነገር ግን የአማኞች ኅብረት ንቁ ተሳታፊዎች አይሆኑም። በአዲስ ኪዳን ውስጥ እግዚአብሔር ለራሱ ክብር ለማምጣት በሚሠራበት የአማኞች ኅብረት ላይ ትኩረት ተደርጓል። እግዚአብሔር እያንዳንዱ ክርስቲያን በአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በንቃት በመሳተፍ የድርሻውን እንዲያበረክት ይፈልጋል።
የውይይት ጥያቄ፡- ሀ) አዲስ ኪዳን «ቤተ ክርስቲያን» ሲል የሚገልጸውን ሃሳብ ዛሬ ብዙ ሰዎች ስለ ቤተ ክርስቲያን ከሚገነዘቡት ጋር አነጻጽር። ለ) «ቤተ ክርስቲያን» የሚለው ቃል በቀዳሚነት ሰዎችን ሳይሆን የቤተ ክርስቲያንን ሕንፃ እንደሚያመለክት ስናስብ፥ ምን ምን ችግሮች ይከሰታሉ? ሐ) በቤተ ክርስቲያንህ ውስጥ የሚያመልኩት አብዛኞቹ ሰዎች መንፈሳዊ ስጦታዎቻቸውን በትጋት ይጠቀማሉ? ለምን? መ) አብዛኛዎቹ ሰዎች በትጋት ሳይሳተፉ እንደ ተመልካች በየጉባኤዎች ላይ ተገኝተው መመለሳቸው ምን ዓይነት አሉታዊ ውጤቶችን ያስከትላል?
የውይይት ጥያቄ፡- ስለ ኤፌሶን ከመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት አንብብና ስለ ጸሐፊው፥ ስለ ቤተ ክርስቲያኒቱ፥ ስለ ደብዳቤው ዓላማና ስለ ከተማው፥ ወዘተ... ጠቅለል ያለ አሳብ ጻፍ።
የወኅኒ ቤት መልእክቶች
የውይይት ጥያቄ፡– ኤፌ. 3፡1፤ ፊልጵ. 1፡12-13፤ ቆላ. 1፡24፤ ፊል. 1 አንብብ። ጳውሎስ እነዚህን መልእክቶች በጻፈበት ወቅት የት ነበር?
ምሁራን የኤፌሶንን፥ የፊልጵስዩስን፥ የቆላስይስንና የፊልሞናን መልእክቶች «የወኅኒ ቤት መልእክቶች» ብለው ይጠሯቸዋል። ለዚህም ምክንያቱ ጳውሎስ እስር ቤት (ምናልባትም ሮም) ውስጥ ሆኖ ስለ ጳፋቸው ነው። የጥንት የቤተ ክርስቲያን መሪዎች የጳውሎስን የተለያዩ መልእክቶች ባደራጁ ጊዜ ሦስቱን ረዣዥም የእስር ቤት መልእክቶች (ኤፌሶን፥ ፊልጵስዩስ፥ ቆላስይስ) አንድ ላይ አስቀምጠዋል። ከሁሉም አጭር የሆነው ፊልሞና ከጳውሎስ መልእክቶች የመጨረሻውን ስፍራ ይዟል።
(ማብራሪያው የተወሰደው በ ኤስ.አይ.ኤም ከታተመውና የአዲስ ኪዳን የጥናት መምሪያና ማብራሪያ፣ ከተሰኘው መጽሐፍ ነው፡፡ እግዚአብሔር አገልግሎታቸውን ይባርክ፡፡)
የኤፌሶን መልእክት ጸሐፊ እና ተቀባይ
የኤፌሶን መልእክት ጸሐፊ
የውይይት ጥያቄ፡– ኤፌሶን 1፡1 አንብብ። ሀ) የኤፌሶን መልእክት ጸሐፊ ማን ነው? ለ) ራሱን እንዴት ገለጸ? ኤፌ. 1፡1ን ከገላ. 1፡1 ጋር አወዳድርና ጸሐፊው ራሱን እንዴት እንደሚገልጽ አብራራ።
እንደ ሌሎች ደብዳቤዎች ሁሉ፥ ጳውሎስ የኤፌሶንን መልእክት የጀመረው ጸሐፊነቱን በመግለጽ ነበር። እንደ ሌሎች ጊዜያት ሁሉ «ሐዋርያ» የሚለውን ማዕረጉንም ጨምሮ ጠቅሷል። ጳውሎስ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ መመረጡንና የኢየሱስ ክርስቶስ ሹም ሆኖ መላኩን አመልክቷል። ጳውሎስ መልእክቱን በዚህ መንገድ የጀመረው በታላቅ ሥልጣኑ ለመመካት ሳይሆን፥ ደብዳቤው ለኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን የተላከ የክርስቶስ መልእክት መሆኑን ለማስረዳት ነው። ይህም አማኞቹ ሰምተው እንዲታዘዙት ነው።
ጳውሎስን መልእክቱን ለማን ጻፈ?
የውይይት ጥያቄ፡- ሀ) ጳውሎስ ይህን መልእክት የጻፈው ለማን ነው? ለ) ጳውሎስ የመልእክቱን ተቀባዮች የገለጸው እንዴት ነው? ሐ) የሐዋ. 18፡18-20፡1 አንብብ። ወንጌሉ መጀመሪያ ወደ ኤፌሶን የደረሰው እንዴት ነው? ጳውሎስ በዚያ ለምን ያህል ጊዜ አገለገለ?
ጳውሎስ መልእክቱን የጻፈው «ለኤፌሶን ቅዱሳን» ነበር። «ቅዱስ» የተለየ የሚል ፍች ሲኖረው፥ እነዚህ ክርስቲያኖች ፍጹም ወይም ኃጢአት እልባ መሆናቸውን አያመለክትም። ነገር ግን ክርስቲያኖች በእግዚአብሔር እንደ ተመረጡና ለእግዚአብሔር ቅዱሳን ይሆኑ ዘንድ እንደ ተለዩ ያሳያል።
ብዙውን ጊዜ ይህ መልእክት ለኤፌሶን እማኞች እንደተጻፈ እናስባለን። ኤፌሶን፥ ጳውሎስ በሦስተኛው የወንጌል መልእክተኝነት ጉዞው ውስጥ ለሦስት ዓመታት ያገለገለባት ቦታ ናት። ስለሆነም፥ ይህ መልእክት ጳውሎስ ወደ መሠረታት ቤተ ክርስቲያን የተጻፈ ይመስላል። ነገር ግን አንዳንድ ምሁራን ይህ መልእክት በቀጥታ ለኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን እንዳልተላከ በመግለጽ አያሌ ምክንያቶችን ይሰነዝራሉ። በመጀመሪያ፥ አንዳንድ ጥንታዊ የኤፌሶን መልእክት ቅጂዎች «ኤፌሶን» የሚል ቃል የለባቸውም። ነገር ግን «በኢየሱስ ክርስቶስ ለታመኑት ቅዱሳን» የሚል ሐረግ ተጽፎባቸዋል። ሁለተኛ፥ ጳውሎስ የሚጽፍላቸውን ሰዎች በአካል የሚያውቅ አይመስልም። በአካል ተገኝቶ እንደ ተመለከተ ሳይሆን፥ ስለ እምነታቸውና ፍቅራቸው እንደ ሰማ ይናገራል (ኤፌ. 1፡15)። በተጨማሪም፥ ጳውሎስ ስለ ክርስቶስ አዳኝነት የሚናገሩትን እውነቶች (ኤፌ. 4፡21፥ ብሎም ስለ አገልግሎቱ መረዳታቸውን እንደሰማ ይናገራል (ኤፌ. 3፡2)። ጳውሎስ መልእክቱን የጻፈው ለሦስት ዓመታት ላገላገላት ለኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን ቢሆን ኖሮ፥ ስለ ኤፌሶን ክርስቲያኖች እምነትና ፍቅር ራሱ ይመሰክር ነበር። ሦስተኛ፥ በተጨማሪም በመልእክቱ ውስጥ የግል ሰላምታም ሆነ ሁነኛ ችግሮች አልተጠቀሱም። ከእነዚህ ምክንያቶች የተነሣ ብዙ ምሁራን ይህ መልእክት ወደ ተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት የሚዟዟር እንደ ነበር ይናገራሉ። ጳውሎስ መልእክቱን መጀመሪያ ዐቢይ ቤተ ክርስቲያን ወደምትገኝባት ኤፌሶን ላከ። እዚያ ከተነበበ በኋላ ደብዳቤው በእስያ ውስጥ ወደሚገኙ ሌሎች አብያተ ክርስቲያናት (ምናልባትም በራእይ ውስጥ የተጠቀሱትን ሰባት አብያተ ክርስቲያናት ጨምሮ) ተላከ (ራእይ 1፡1)። በቆላስይስ 4፡16፣ ጳውሎስ ለሎዶቂያ ክርስቲያኖች ስለተጻፈ ሌላ መልእክት ጠቅሷል። አንዳንድ ምሁራን ይህ ኤፌሶን ብለን የምንጠራው ተዘዋዋሪ መልእክት እንደሆነ ያስባሉ።
ጳውሎስ እነዚህን ክርስቲያኖች «በክርስቶስ የታመኑ» ይላቸዋል። በክርስቶስ ማመን ብቻ ሳይሆን፥ ከእርሱ ጋር ያላቸውን ግንኙነት በማጥበቅ በታማኝነት ይከተሉት ነበር። የሚያሳዝነው የኤፌሶን ሰዎች ለኢየሱስ የነበራቸው ታማኝነት ዘለቄታ አልነበረውም። ከ40 ዓመታት ያህል በኋላ ክርስቶስ ለኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን ልዩ መልእክት ልኳል። ለእርሱ የነበራቸውን የመጀመሪያ ፍቅር በማጣታቸው ወቅሷቸዋል። ንስሐ ገብተው ፍቅራቸውን ካላደሱ በፍርድ እንደሚመጣባቸው አስጠንቅቋቸዋል (ራእይ 2፡1-7 አንብብ)። ቤተ ክርስቲያን ዛሬ ታማኝ መሆኗ ብቻ በቂ አይደለም። ለክርስቶስ ያለን ፍቅር በቀጣይነት ሊያድግና ሊጠናከር ይገባል። ብዙ አብያተ ክርስቲያናት በጠንካራ አቋም ጀምረው ከጥቂት ጊዜ በኋላ እየተዳከሙ ሄደዋል።
የውይይት ጥያቄ፡- ስለ ቤተ ክርስቲያንህ አስብ። ሀ) ክርስቶስ ከእርሱ ጋር ያለህን ግንኙነት እንዴት ይገልጻል? ለ) ቤተ ክርስቲያንህ ከዚህ በፊትና አሁን ከእግዚአብሔር ጋር የምታደርገውን ግንኙነቷን አነጻጽር። እየተዳከመች ነው ወይስ እየበረታች? እየተዳከመች ከሆነ፥ የእግዚአብሔር ፍርድ እንዳይደርስባት ግንኙነት ለማደስ ስለ ምን ነገሮች ንስሐ ልትገባ ይገባል?


የኤፌሶን መልእክት መግቢያ
ተስፋጽዮን በጀማ የወንጌል ስብከት ላይ ስለ ክርስቶስ ሰምቶ በክርስቶስ አመነ። ከዚያ በኋላ ከተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት ተወካዮች ጋር ተገናኘ። በስብሰባው ላይ የቃለ ሕይወት፥ የመካነ ኢየሱስ፥ የሙሉ ወንጌል፥ የመሠረተ ክርስቶስ፥ የሕይወት ብርሃንና የሌሎች ብዙ አብያተ ክርስቲያናት መሪዎች ነበሩ። ሁሉም ተስፋጽዮን ወደ ቤተ ክርስቲያናቸው እንዲመጣ ገፋፉት። ሁሉም ወደ ቤተ ክርስቲያናቸው እንዲመጣ ለማግባባት፥ «ከሁሉም የሚበልጡ ብዙ ምእመናን አሉን። ቃሉን እናስተምራለን። የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች አሉን» ሲሉ አዋከቡት። ተስፋጽዮን በዚህ ሁኔታ ግራ ተጋባ። «ቤተ ክርስቲያን ምንድን ናት? እንዲህ ቤተ እምነቶች የበዙት ለምንድን ነው? ትክክለኛው ቤተ እምነት የትኛው ነው?» ሲል ራሱን ጠየቀ።
ጥያቄ፡- ሀ) የተለያዩ ቤተ እምነቶች አዳዲስ ክርስቲያኖችንና አማኞች ያልሆኑትን ሰዎች ግራ የሚያጋቡት እንዴት ነው? ለ) ቤተ እምነቶች የበዙት ለምንድን ነው? ሐ) ጤናማ ይመስልሃል? ለምን? መ) በአማርኛ ቋንቋ «ቤተ ክርስቲያን» የሚለው ቃል ምን ትርጉም ይሰጣል?
በአሁኑ ዘመን ብዙ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት የሚገኙ ሲሆን፥ ሌሎች ብዙዎችም እዚሁ ቅርንጫፎችን ለመመሥረት ከምዕራባውያን አገሮች እየጎረፉ ናቸው። እነዚህ ብዙ ቤተ እምነቶች የሚመጡት ከየት ነው? ቤተ እምነቶች የበዙትስ ለምንድን ነው? በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙት አብዛኛዎቹ ቤተ እምነቶች ከሚከተሉት ምንጮች የመጡ ናቸው።
በመጀመሪያ፥ ከምዕራቡ ዓለም የመነጩ ቤተ እምነቶች አሉ። የተለያዩ ሚስዮናውያን ወደ ኢትዮጵያ መጥተው በአገራቸው ያሉትን ዓይነት ቤተ እምነቶች መሥርተዋል። እነዚህ ቤተ እምነቶች ከየት የመጡ ናቸው? አብዛኞቹ የምዕራቡ ዓለም ቤተ እምነቶች በትናንሽ የአስተምህሯዊ ልዩነቶች ምክንያት የተፈጠሩ ናቸው። ከእነዚህ አስተምህሯዊ ልዩነቶች መካከል አንዳንዶቹ የሕፃናት ወይም የአዋቂዎች ጥምቀት፥ የቅዱስ ቁርባን ፍችና የመንፈስ ቅዱስ ቀዳሚ አገልግሎት ምንነትን የሚመለከቱ ናቸው።
ሁለተኛ፥ ሌሎች ቤተ እምነቶች የራሳቸውን ቤተ እምነቶች የጀመሩትን ታላላቅ መሪዎች፥ ሰባኪዎች ወይም የፈውስ አገልጋዮች በመከተል የተመሠረቱ ናቸው። ይህ በኢትዮጵያ ብዙም ያልተለመደ ቢሆንም፥ በሌሎች የአፍሪካ አገሮች ግን በመቶዎች የሚቆጠሩ ቤተ እምነቶች በመሪዎች ስም ተመሥርተዋል።
ሦስተኛ፥ የአንዲት ቤተ ክርስቲያን መእመናን በሰላም ለመኖር ባለመቻላቸው ምክንያት የተጀመሩ ቤተ እምነቶችም አሉ።
ባለመስማማታቸው ምክንያት ተከፋፍለው የየራሳቸውን ቤተ እምነቶች ይመሠርታሉ። ብዙውን ጊዜ የእነዚህ ክፍፍሎች ምክንያቶች፥ ጎሰኝነት በተወሰኑ ልምምዶች ላይ በሚከሰቱ የአመለካከት ልዩነቶች ወይም ሰብአዊ ኩራት ናቸው።
የሚያሳዝነው ከእነዚህ ምክንያቶች አንዳቸውም አዲስ ቤተ እምነት ለመመሥረት የሚያበቁ አለመሆናቸው ነው። ሁልጊዜም በትናንሽ የመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮዎች ላይ የአሳብ ልዩነት የሚያሳዩ ክርስቲያኖች ይኖራሉ። ዓይን ለዓይን እንኳን መተያየት የማይፈልጉ መሪዎችም ይኖራሉ። ሁልጊዜም በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በተወሰኑ ጉዳዮች ወይም ልምምዶች ላይ ውጥረቶች ይኖራሉ። እግዚአብሔር ግን ከእነዚህ ምክንያቶች አንዱም አዲስ ቤተ እምነት ለመጀመር ብቁ መሆናቸውን አያረጋግጥም። ክርስቲያኖች ባለመስማማታቸው ምክንያት መከፋፈል መከሰቱ እጅግ አሳዛኝ ነገር ነው። በዮሐንስ 17 ክርስቶስ ተከታዮቹ አንድነትን እንዲመሠርቱ ጸልዮአል። ጳውሎስ ክርስቲያኖች አንድ አሳብ እንዲኖራቸው ተማጽኗል (ፊልጵ. 2፡1-2)። ነገር ግን ከኃጢአተኝነታችንና ከኩራታችን የተነሣ ክፍፍሎች ይከሰታሉ።
የቤተ እምነቶች መፈጠር ስሕተት ነውን? የተመሠረቱበት ዓላማ ስሕተት ከሆነ፥ እንዲሁም የውድድርና የኩራት መንፈስ የሚታይባቸው ከሆነ፥ የቤተ እምነቶች መፈጠር ትክክል ሊሆን አይችልም። አንዱ ቤተ እምነት ከሌሎች እንደሚበልጥ ሲያስተምርና የተለያዩ ቤተ እምነቶች ተከታዮች እርስ በርሳቸው ቢጣሉ፥ ወይም አንዱ የሌላውን አባላት ለመውሰድ ቢሞክር፥ ይህ የአንድ ቤተሰብ አባላት የሆኑ ወንድማማቾችን ማጣላት ያህል አስከፊ ነው።
በሌላ በኩል፥ የተለያዩ ቤተ እምነቶች መፈጠር እግዚአብሔርን ሊያስከብር ይችላል። የተለያዩ ብዙ ዓይነት ዛፎች ለአንድ አካባቢ ውበትን እንደሚጨምሩ ሁሉ፥ የተለያዩ የአምልኮ ስልቶችና ልምምዶች ያሏቸው ብዙ ቤተ እምነቶች የውበት መገለጫዎች ሊሆኑ ይችላሉ። ነገር ግን ይህ የቤተ እምነቶች ልዩነት የታላቁ የክርስቶስ አካል ክፍሎች የመሆናችንን አንድነት ያገናዘበ ሊሆን ይገባል። በፍጥረት ውስጥ የምንመለከተው በአንድነት ውስጥ ያለ ልዩነት በቤተ ክርስቲያንም ውስጥ ሊንጸባረቅ ይገባል።
የኤፌሶን መልእክት በክርስቶስ አካል ወይም በቤተ ክርስቲያን ላይ ያተኩራል። ቤተ ክርስቲያን ምንድን ናት? በአማርኛ ቋንቋ፥ ቃሉ ሕንፃ ወይም የክርስቲያኖችን መሰብሰቢያ ያመለክታል። አዲስ ኪዳን ግን ሕንፃን ለማመልከት «ቤተ ክርስቲያን» የሚለውን ቃል የተጠቀመበት ስፍራ የለም። እንዲያውም፥ ከሐዋርያት ዘመን ጀምሮ ለብዙ መቶ ዓመታት ክርስቲያኖች ሁነኛ የመሰባሰቢያ ስፍራ አልነበራቸውም። በአዲስ ኪዳን ቤተ ክርስቲያንን የሚለው ቃል በሰዎች ላይ ያተኩራል። በግሪክ ቋንቋ፥ ቃሉ «ጉባኤ»ን ወይም የተወሰኑ ሰዎችን «አብሮ መሰባሰብ» ያመለክታል። የአንዲት ከተማ ነዋሪዎች ለስብሰባ ተጠርተው የሚያካሂዱት ስብሰባ ቤተ ክርስቲያን ይባል ነበር። ስለሆነም ከዓለም ወደ ክርስቶስ አካል የተጠሩት ክርስቲያኖች የሚያካሂዱትም ስብሰባ ቤተ ክርስቲያን ይባላል።
በአዲስ ኪዳን፥ ቤተ ክርስቲያን የሚለው ቃል ሦስት የክርስቲያን ቡድኖችን ሊያመለክት ይችላል። በመጀመሪያ፥ ብዙውን ጊዜ የአጥቢያ ክርስቲያኖችን በአንድ አካባቢ መሰባሰብ ሊያመለክት ይችላል (ሮሜ 16፡5)። አብዛኞቹ የቀድሞዎቹ አብያተ ክርስቲያናት በግለሰቦች ቤቶች ውስጥ ይሰባሰቡ ነበር። ወደ 50 የሚሆኑ ሰዎች በመደበኛነት በግለሰቦች ቤቶች ውስጥ እየተሰባሰቡ ያመልኩና መጽሐፍ ቅዱስ ያጠኑ ነበር። ሁለተኛ ቤተ ክርስቲያን የሚለው ቃል በአንድ መልክዓ ምድራዊ ክልል ውስጥ የሚገኙትን ክርስቲያኖች ሊያመለክት ይችላል። ለምሳሌ ያህል፥ ጳውሎስ ለሮሜ ወይም ለቆሮንቶስ ቤተ ክርስቲያን ጽፎአል። እነዚህ አብያተ ክርስቲያናት ከአንድ ሕንፃ ሥር የሚሰባሰቡ ሳይሆኑ፥ በተለያዩ ቤቶች ውስጥ የሚሰባሰቡ የአንድ አካባቢ ክርስቲያኖች ነበሩ። ዛሬ በተመሳሳይ ሁኔታ «የአፍሪካ ቤተ ክርስቲያን» ወይም «የብሪታኒያ ቤተ ክርስቲያን» ልንል እንችላለን። ሦስተኛ፥ ዓለም አቀፋዊት (ዩኒቨርሳል) ቤተ ክርስቲያን አለች። ይህ የሞቱትንና በሕይወት ያሉትን፥ በሰማይና በምድር ያሉትን ጨምሮ የክርስቶስ አካል የሆኑትን ሁሉ ያጠቃልላል (ዕብ. 12፡23)። ጳውሎስ በኤፌሶን መልእክት ውስጥ ስለ አጽናፈ አቀፉዋ ቤተ ክርስቲያን ደጋግሞ ጠቅሷል።
ሐዋርያው ጳውሎስ፥ እግዚአብሔር በዓለም ውስጥ የሚያከናውነው ታላቁ ሥራ የክርስቶስን አካል መገንባት እንደሆነ ተገንዝቧል። ኢየሱስ ክርስቶስ በእርሱ ያመኑና የሚከተሉት ሰዎች ሁሉ የሚገኙባት ዓለም አቀፋዊት ቤተ ክርስቲያን ራስ ነው። እግዚአብሔር በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ለእያንዳንዱ አማኝ የተለየ ስጦታ ይሰጣል። አማኙ በዚህ ስጦታው ሌሎችን በማገልገል ክርስቶስን ያገለግላል። ይህ የአማኞች አካል በምድር ላይ ክርስቶስን ይወክላል። ወንጌሉን ስንመሰክር አፉ፥ እርስ በርሳችንና ሌሎችን ስንረዳ እጆቹ፥ እንዲሁም ወንጌሉን ወደ ዓለም ሁሉ ስናዳርስ እግሮቹ ሆነን እንሠራለን። ጳውሎስ


💔⚡️Yeroo kana dhaloota miidhaa kan jiru qofummaadha. Qofummaa kara lamaan hiikuu dandeenya. ➡️See More👆👇👆👆💘🥹🥰

➡️ See More
 .    See More


🥰

➡️ Channel jaalatamoo ergaalee ajaaibsiisoo fi barsiisoo ta'an qabu kana irratti gadi tuquudhaan JOIN taasisaa! ➡️ JOIN 📌

1️⃣ 💡💡💡💡💡💡💡

     🚘 'https://t.me/addlist/4e8EfR1mqNFlY2E8' rel='nofollow'>JOIN
    JOIN

2️⃣ 💡💡💡💡💡💡💡

    🚩 MORE JOIN  🚩
   🚩 MORE JOIN 🚩


3️⃣💡💡💡💡💡💡💡
    🍰MORE JOIN  🕯
   🍰 MORE JOIN 🕯


𝙰𝚍𝚍 𝚢𝚘𝚞𝚛 𝙲𝚑𝚊𝚗𝚗𝚎𝚕
➕ ᥲძძ ᥡ᥆ᥙr ᥴһᥲᥒᥒᥱᥣ

📌 Channel keessan tolaan nu waliin beeksifadhaa


Fak. 31
ÂŻÂŻÂŻÂŻÂŻÂŻÂŻÂŻÂŻÂŻ
š⁰ Haadha manaa mana ishee qabuu dandeessu, eenyutu argachuu danda'a ree? Isheen callee gati-jabeessa hundumaa irra guddaa in caalti;
šš abbaan manaa ishee ishee in amanata; qabeenyis isatti hin hir'atu.
š² Bara jireenya ishee hundumaatti, wanta gaarii gootiif malee, wanta hamaa isa irratti hin hojjettu;
š³ isheen rifeensaa fi quncee talbaa barbaaddee, dhimmitees uffata in dhoofti.
š⁴ Markaboonni naggaadotaa, biyya fagoo dhaqanii akkuma mi'a fidan, isheenis biyya fagootii nyaata ishee in fidatti.
š⁾ Isheen ganama utuu lafti hin bari'in kaatee, maatii isheetiif nyaata in kenniti, xomboreewwan isheettis hojii hojii isaanii in argisiifti.
š⁜ Isheen qortee ilaaltee lafa in bitatti; horii itti dadhabdee argatteenis biqiltuu waynii in dhaabbatti.
š⁡ Mudhii ishee jabeessitee in hidhatti, irree ishee cimsattees in hojjetatti.
š⁸ Hojiin ishee bu'aa akka qabu in ilaalti, ibsaan ishees halkan hin dhaamu;
š⁚ muka itti jirbii maran harka isheetti in baatti, qubbeetii isheetiin immoo calii in qabatti.
²⁰ Isheen hiyyeessaaf in arjoomti, dhabaadhaafis garaa in laafti;
²š maatiin ishee uffannaa dhaamocha nama irraa ittisu waan qabaniif, yommuu alaa cabbii buusee roobu maatii isheetiif hin yaaddoftu;
²² isheen uffata siree in dha'atti, uffata calaqqisaa, quncee talbaa ba'eessa irraa dha'ames in uffatti.
²³ Abbaan manaa ishee jaarsolii biyyaa wajjin, yaa'ii karra mandaraa keessa yommuu taa'u ulfina qaba;
²⁴ isheen quncee talbaa irraa uffata dhooftee in gurgurti, naggaadotattis sabbata in gurgurti;
²⁾ humnaa fi ulfina akka uffataatti in uffatti; yeroodhuma dhufuttis in gammaddi.
²⁜ Ogummaadhaan in dubbatti, barsiifni gaariinis afaan ishee keessaa in ba'a.
²⁡ Isheen yeroo hundumaa jireenya maatii isheetii in eegdi, utuu hin hojjetinis akkasumaan buddeena hin nyaattu.
²⁸ Ijoolleen ishee lafaa ka'anii "Eebbifamtuu!" jedhanii ishee in waamu, abbaan manaa ishee immoo ishee jajatee,
²⁚ "Dubartoota baay'eetu wanta ba'eessa hojjeta, ati garuu hunduma isaanii in caalta" isheedhaan in jedha.
³⁰ Simboon nama irraa in darbiti miidhaginnis nama in gowwoomsiti, dubartiin Waaqayyoon sodaattu garuu in jajamti.
³š Gatii ija hojii isheetii isheedhaaf kennaa! Hojiin ishee yaa'ii karra mandaraa keessatti ishee haa jaju!


ጳውሎስ በኤፌሶን ዐቢይ የአገልግሎት መሠረት የጣለው በሦስተኛው የወንጌል መልእክተኝነት ጉዞው ነበር። በኤፌሶን ሲሰብክና ሲያስተምር ለሦስት ዓመታት ቆየ። ይህም በየትኛውም የአገልግሎት ጉዞው ካደረጋቸው ቆይታዎች ሁሉ የበለጠ ነበር። ብዙ ሰዎች የንግድ ማዕከል ወደነበረችው ኤፌሶን የንግድ ተግባራቸውን ለማከናወን ሲመጡ ወንጌሉን ይሰብክላቸው ነበር። እነርሱም ወንጌሉን ይዘው ወደመጡበት አገር ይመለሳሉ። ከዚህም የተነሣ ወንጌሉ በእስያ አገሮች ሁሉ ተስፋፋ (የሐዋ. 19፡10)። ምናልባትም በራእይ ውስጥ የተጠቀሱት ሰባቱ አብያተ ክርስቲያናትና የቆላስይስ ቤተ ክርስቲያን የተመሠረቱት በዚህ ጊዜ ሳይሆን አይቀርም። በኤፌሶን አገልግሎቱ መጨረሻ አካባቢ ተቃውሞ እየተጠናከረ በመሄዱ በከተማይቱ ውስጥ ብጥብጥ ተነሣ። ከዚያ በኋላ ብዙም ሳይቆይ ጳውሎስ የግሪክን አብያተ ክርስቲያናት ጎብኝቶ ወደ ኢየሩሳሌም ተመለሰ።
ጳውሎስ የኤፌሶንን መልእክት የጻፈበት ዘመንና ስፍራ
የውይይት ጥያቄ፡– ኤፌ 3፡1 እና 4፡1 አንብብ። ጳውሎስ መልእክቱን የጻፈው የት ሆኖ ነበር?
ጳውሎስ ይህን መልእክት በጻፈ ጊዜ የሆነ ስፍራ ታስሮ ነበር። ግን የት እንደ ታሰረ? አያሌ ግምቶች አሉ። ቂሣሪያ ወይም ሮም ታስሮ ሊሆን ይችላል። ጳውሎስ ወደ ኢየሩሳሌም ሲደርስ መታሰሩን አስታውሰ። ለጥቂት ጊዜ በኢየሩሳሌም ታስሮ ከቆየ በኋላ ቂሣሪያ ወደተባለችው የሮም የአውራጃ ከተማ ተወስዶ ለሁለት ዓመታት ያህል ታስሯል (የሐዋ. 24፡27)። የእስር ቤት መልእክቶቹን የጻፈው በዚህ ጊዜ ሳይሆን አይቀርም። ከሁለት ዓመታት በኋላ፥ ጳውሎስ በንጉሥ ችሎት ይዳኝ ዘንድ ወደ ሮም ተላከ። እዚያም ለሁለት ተጨማሪ ዓመታት ራሱ በተከራየው ቤት ታስሮ ቆየ (የሐዋ. 28፡30-31)። አብዛኞቹ ምሁራን ጳውሎስ አራቱን የወኅኒ ቤት መልእክቶች ሮም ሆኖ በ60 ወይም 61 ዓ.ም እንደ ጻፈ ያምናሉ።
(ማብራሪያው የተወሰደው በ ኤስ.አይ.ኤም ከታተመውና የአዲስ ኪዳን የጥናት መምሪያና ማብራሪያ፣ ከተሰኘው መጽሐፍ ነው፡፡ እግዚአብሔር አገልግሎታቸውን ይባርክ፡፡)


የኤፌሶን መልእክት ጸሐፊ እና ተቀባይ
የኤፌሶን መልእክት ጸሐፊ
የውይይት ጥያቄ፡– ኤፌሶን 1፡1 አንብብ። ሀ) የኤፌሶን መልእክት ጸሐፊ ማን ነው? ለ) ራሱን እንዴት ገለጸ? ኤፌ. 1፡1ን ከገላ. 1፡1 ጋር አወዳድርና ጸሐፊው ራሱን እንዴት እንደሚገልጽ አብራራ።
እንደ ሌሎች ደብዳቤዎች ሁሉ፥ ጳውሎስ የኤፌሶንን መልእክት የጀመረው ጸሐፊነቱን በመግለጽ ነበር። እንደ ሌሎች ጊዜያት ሁሉ «ሐዋርያ» የሚለውን ማዕረጉንም ጨምሮ ጠቅሷል። ጳውሎስ እንደ እግዚአብሔር ፈቃድ መመረጡንና የኢየሱስ ክርስቶስ ሹም ሆኖ መላኩን አመልክቷል። ጳውሎስ መልእክቱን በዚህ መንገድ የጀመረው በታላቅ ሥልጣኑ ለመመካት ሳይሆን፥ ደብዳቤው ለኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን የተላከ የክርስቶስ መልእክት መሆኑን ለማስረዳት ነው። ይህም አማኞቹ ሰምተው እንዲታዘዙት ነው።
ጳውሎስን መልእክቱን ለማን ጻፈ?
የውይይት ጥያቄ፡- ሀ) ጳውሎስ ይህን መልእክት የጻፈው ለማን ነው? ለ) ጳውሎስ የመልእክቱን ተቀባዮች የገለጸው እንዴት ነው? ሐ) የሐዋ. 18፡18-20፡1 አንብብ። ወንጌሉ መጀመሪያ ወደ ኤፌሶን የደረሰው እንዴት ነው? ጳውሎስ በዚያ ለምን ያህል ጊዜ አገለገለ?
ጳውሎስ መልእክቱን የጻፈው «ለኤፌሶን ቅዱሳን» ነበር። «ቅዱስ» የተለየ የሚል ፍች ሲኖረው፥ እነዚህ ክርስቲያኖች ፍጹም ወይም ኃጢአት እልባ መሆናቸውን አያመለክትም። ነገር ግን ክርስቲያኖች በእግዚአብሔር እንደ ተመረጡና ለእግዚአብሔር ቅዱሳን ይሆኑ ዘንድ እንደ ተለዩ ያሳያል።
ብዙውን ጊዜ ይህ መልእክት ለኤፌሶን እማኞች እንደተጻፈ እናስባለን። ኤፌሶን፥ ጳውሎስ በሦስተኛው የወንጌል መልእክተኝነት ጉዞው ውስጥ ለሦስት ዓመታት ያገለገለባት ቦታ ናት። ስለሆነም፥ ይህ መልእክት ጳውሎስ ወደ መሠረታት ቤተ ክርስቲያን የተጻፈ ይመስላል። ነገር ግን አንዳንድ ምሁራን ይህ መልእክት በቀጥታ ለኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን እንዳልተላከ በመግለጽ አያሌ ምክንያቶችን ይሰነዝራሉ። በመጀመሪያ፥ አንዳንድ ጥንታዊ የኤፌሶን መልእክት ቅጂዎች «ኤፌሶን» የሚል ቃል የለባቸውም። ነገር ግን «በኢየሱስ ክርስቶስ ለታመኑት ቅዱሳን» የሚል ሐረግ ተጽፎባቸዋል። ሁለተኛ፥ ጳውሎስ የሚጽፍላቸውን ሰዎች በአካል የሚያውቅ አይመስልም። በአካል ተገኝቶ እንደ ተመለከተ ሳይሆን፥ ስለ እምነታቸውና ፍቅራቸው እንደ ሰማ ይናገራል (ኤፌ. 1፡15)። በተጨማሪም፥ ጳውሎስ ስለ ክርስቶስ አዳኝነት የሚናገሩትን እውነቶች (ኤፌ. 4፡21፥ ብሎም ስለ አገልግሎቱ መረዳታቸውን እንደሰማ ይናገራል (ኤፌ. 3፡2)። ጳውሎስ መልእክቱን የጻፈው ለሦስት ዓመታት ላገላገላት ለኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን ቢሆን ኖሮ፥ ስለ ኤፌሶን ክርስቲያኖች እምነትና ፍቅር ራሱ ይመሰክር ነበር። ሦስተኛ፥ በተጨማሪም በመልእክቱ ውስጥ የግል ሰላምታም ሆነ ሁነኛ ችግሮች አልተጠቀሱም። ከእነዚህ ምክንያቶች የተነሣ ብዙ ምሁራን ይህ መልእክት ወደ ተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት የሚዟዟር እንደ ነበር ይናገራሉ። ጳውሎስ መልእክቱን መጀመሪያ ዐቢይ ቤተ ክርስቲያን ወደምትገኝባት ኤፌሶን ላከ። እዚያ ከተነበበ በኋላ ደብዳቤው በእስያ ውስጥ ወደሚገኙ ሌሎች አብያተ ክርስቲያናት (ምናልባትም በራእይ ውስጥ የተጠቀሱትን ሰባት አብያተ ክርስቲያናት ጨምሮ) ተላከ (ራእይ 1፡1)። በቆላስይስ 4፡16፣ ጳውሎስ ለሎዶቂያ ክርስቲያኖች ስለተጻፈ ሌላ መልእክት ጠቅሷል። አንዳንድ ምሁራን ይህ ኤፌሶን ብለን የምንጠራው ተዘዋዋሪ መልእክት እንደሆነ ያስባሉ።
ጳውሎስ እነዚህን ክርስቲያኖች «በክርስቶስ የታመኑ» ይላቸዋል። በክርስቶስ ማመን ብቻ ሳይሆን፥ ከእርሱ ጋር ያላቸውን ግንኙነት በማጥበቅ በታማኝነት ይከተሉት ነበር። የሚያሳዝነው የኤፌሶን ሰዎች ለኢየሱስ የነበራቸው ታማኝነት ዘለቄታ አልነበረውም። ከ40 ዓመታት ያህል በኋላ ክርስቶስ ለኤፌሶን ቤተ ክርስቲያን ልዩ መልእክት ልኳል። ለእርሱ የነበራቸውን የመጀመሪያ ፍቅር በማጣታቸው ወቅሷቸዋል። ንስሐ ገብተው ፍቅራቸውን ካላደሱ በፍርድ እንደሚመጣባቸው አስጠንቅቋቸዋል (ራእይ 2፡1-7 አንብብ)። ቤተ ክርስቲያን ዛሬ ታማኝ መሆኗ ብቻ በቂ አይደለም። ለክርስቶስ ያለን ፍቅር በቀጣይነት ሊያድግና ሊጠናከር ይገባል። ብዙ አብያተ ክርስቲያናት በጠንካራ አቋም ጀምረው ከጥቂት ጊዜ በኋላ እየተዳከሙ ሄደዋል።
የውይይት ጥያቄ፡- ስለ ቤተ ክርስቲያንህ አስብ። ሀ) ክርስቶስ ከእርሱ ጋር ያለህን ግንኙነት እንዴት ይገልጻል? ለ) ቤተ ክርስቲያንህ ከዚህ በፊትና አሁን ከእግዚአብሔር ጋር የምታደርገውን ግንኙነቷን አነጻጽር። እየተዳከመች ነው ወይስ እየበረታች? እየተዳከመች ከሆነ፥ የእግዚአብሔር ፍርድ እንዳይደርስባት ግንኙነት ለማደስ ስለ ምን ነገሮች ንስሐ ልትገባ ይገባል?
ጳውሎስ በወንጌል መልእክተኝነት ጉዞው ከየትኛውም ስፍራ በላይ በኤፌሶን ብዙ ጊዜ ቆይቷል። ጳውሎስ በአሁኗ ቱርክ ውስጥ የነበረችውን ኤፌሶንን እንደ ቁልፍ የአገልግሎት ስፍራ ነበረ የተመለከተው። ኤፌሶንን መናኸሪያ አድርጎ በመጠቀሙ ወንጌል በእስያ አውራጃ ውስጥ በፍጥነት ሊሰራጭ ችሏል (የሐዋ. 19፡10)።
የኤፌሶን ከተማ ዋነኛ የወደብ ከተማና የእስያ አውራጃ መዲና ነበረች። አብዛኛው የንግድ እንቅስቃሴ ከምዕራብ ቱርክ ወደ ኤፌሶን ከመጣ በኋላ ከዚያ ወደ ጥንቱ ዓለም ሁሉ ይሰራጭ ነበር። ጳውሎስ በዚያ በሚሠራበት ጊዜ ቢያንስ የ1100 ዓመታት ዕድሜ የነበራት ጥንታዊ የታሪክ ከተማ ነበረች። ብዙ አይሁዶችና ሌሎችም ከ500,000 የሚበልጡ ሰዎች በከተማይቱ ውስጥ ይኖሩ እንደነበር ይገመታል። በዚያ ከነበሩት አይሁዶች አንዳንዶቹ ወደ ክርስትና እምነት ሲመጡ፥ አብዛኞቹ ግን የወንጌሉ ጠላቶች ሆነው ክርስቲያኖችን ያሳድዱ ነበር።
ኤፌሶን ዳያና በተባለች ጣዖት አምልኮም ትታወቅ ነበር። ዳያና የምትመለክበት ቤተ መቅደስና ሐውልቷ እጅግ አስደናቂ በመሆናቸው ከሰባቱ የጥንቱ ዓለም አስደናቂ ነገሮች እንደ አንዱ እንደሆኑ ተደርገው ይቆጠሩ ነበር። ዳያና የሚለው ሮማዊ ስምም ሆነ አርጤምስ የሚለው የግሪክ መጠሪያ የፍሬያማነትን አምላክ የሚያመለክት ነበር። ሴቶች ዳያናን በማምለካቸው ልጅ መውለድ እንደሚችሉ ይታመን ነበር። ከዳያናና ከሌሎች ጣዖታት በተጨማሪ ኤፌሶን ዋነኛ የጥንቆላና የምትሐት ማዕከል ነበረች። የኤፌሶን ሰዎች በክርስቶስ ካመኑ በኋላ ቢያንስ 350,000 ብር የሚገመቱ የምትሐት መጻሕፍት እንዳቃጠሉ ተነግሮናል። በኋላም የሮም ንጉሥ አምልኮ ከተጧጧፈባቸው ከተሞች አንዱ ኤፌሶን ነበረች። በዚህ ሃይማኖት ንጉሡን ለማምለክ ባለመፍቀዳቸው እንደ ዓመፀኞች በታዩት ክርስቲያኖች ላይ ከፍተኛ ስደት ተከስቷል።
ጳውሎስ መጀመሪያ በኤፈሶን ወንጌልን የሰበከው በሁለተኛው የወንጌል መልእክተኝነት ጉዞው መጨረሻ አካባቢ ነበር። ጳውሎስ ወደ ኢየሩሳሌም ሲሄድ እግረ መንገዱን ከጵርስቅላና አቂላ ጋር ወደ ኤፌሶን ጎራ አለ (የሐዋ. 18፡18-19)። አንድ ጊዜ ለአይሁዶች ከሰበከ በኋላ ሰዎች እንዲቆይ ቢፈልጉም ወደ ኢየሩሳሌም አመራ። ጵርስቅላና አቂላ ግን እዚያው ቆዩ። በዚህ ጊዜ ከመጥምቁ ዮሐንስ ደቀ መዛሙርት አንዱ የነበረው አጵሎስ የሚባለው ወደ ኤፌሶን መጥቶ ማስተማር ጀመረ። ጵርስቅላና አቂላ ስለ ክርስቶስ የበለጠ ካስተማሩት በኋላ አጵሎስ በኤፌሶን ወንጌሉን እንዲያስፋፋ እግዚአብሔር በሚገባ ተጠቀመበት። ነገር ግን ብዙም ሳይቆይ ወደ ቆሮንቶስ ለአገልግሎት ሄደ።


ይህንን የአማኞች መሰባሰብ የእግዚአብሔር «ቤተ መቅደስ» ወይም የመንፈስ ቅዱስ ቤተ መቅደስ ይለዋል (ኤፌ. 2፡21)። ምንም እንኳ ክርስቶስ በእያንዳንዱ ክርስቲያን ልብ ውስጥ ቢኖርም፥ ከዚያ በላቀ ሁኔታ በአማኞች ኅብረት ውስጥ ይኖራል።
ዛሬ ትኩረት የሚደረገው በግለሰቦች ድነት (ደኅንነት) ላይ ነው። የሰዎችን መዳን አለመዳን እንጠይቃለን። ብዙ ሰዎች ለማምለክ ለራሳቸው ብቻ ቃሉን ለመማር ወደ ቤተ ክርስቲያን ይመጣሉ። ነገር ግን የአማኞች ኅብረት ንቁ ተሳታፊዎች አይሆኑም። በአዲስ ኪዳን ውስጥ እግዚአብሔር ለራሱ ክብር ለማምጣት በሚሠራበት የአማኞች ኅብረት ላይ ትኩረት ተደርጓል። እግዚአብሔር እያንዳንዱ ክርስቲያን በአጥቢያ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ በንቃት በመሳተፍ የድርሻውን እንዲያበረክት ይፈልጋል።
የውይይት ጥያቄ፡- ሀ) አዲስ ኪዳን «ቤተ ክርስቲያን» ሲል የሚገልጸውን ሃሳብ ዛሬ ብዙ ሰዎች ስለ ቤተ ክርስቲያን ከሚገነዘቡት ጋር አነጻጽር። ለ) «ቤተ ክርስቲያን» የሚለው ቃል በቀዳሚነት ሰዎችን ሳይሆን የቤተ ክርስቲያንን ሕንፃ እንደሚያመለክት ስናስብ፥ ምን ምን ችግሮች ይከሰታሉ? ሐ) በቤተ ክርስቲያንህ ውስጥ የሚያመልኩት አብዛኞቹ ሰዎች መንፈሳዊ ስጦታዎቻቸውን በትጋት ይጠቀማሉ? ለምን? መ) አብዛኛዎቹ ሰዎች በትጋት ሳይሳተፉ እንደ ተመልካች በየጉባኤዎች ላይ ተገኝተው መመለሳቸው ምን ዓይነት አሉታዊ ውጤቶችን ያስከትላል?
የውይይት ጥያቄ፡- ስለ ኤፌሶን ከመጽሐፍ ቅዱስ መዝገበ ቃላት አንብብና ስለ ጸሐፊው፥ ስለ ቤተ ክርስቲያኒቱ፥ ስለ ደብዳቤው ዓላማና ስለ ከተማው፥ ወዘተ... ጠቅለል ያለ አሳብ ጻፍ።
የወኅኒ ቤት መልእክቶች
የውይይት ጥያቄ፡– ኤፌ. 3፡1፤ ፊልጵ. 1፡12-13፤ ቆላ. 1፡24፤ ፊል. 1 አንብብ። ጳውሎስ እነዚህን መልእክቶች በጻፈበት ወቅት የት ነበር?
ምሁራን የኤፌሶንን፥ የፊልጵስዩስን፥ የቆላስይስንና የፊልሞናን መልእክቶች «የወኅኒ ቤት መልእክቶች» ብለው ይጠሯቸዋል። ለዚህም ምክንያቱ ጳውሎስ እስር ቤት (ምናልባትም ሮም) ውስጥ ሆኖ ስለ ጳፋቸው ነው። የጥንት የቤተ ክርስቲያን መሪዎች የጳውሎስን የተለያዩ መልእክቶች ባደራጁ ጊዜ ሦስቱን ረዣዥም የእስር ቤት መልእክቶች (ኤፌሶን፥ ፊልጵስዩስ፥ ቆላስይስ) አንድ ላይ አስቀምጠዋል። ከሁሉም አጭር የሆነው ፊልሞና ከጳውሎስ መልእክቶች የመጨረሻውን ስፍራ ይዟል።
(ማብራሪያው የተወሰደው በ ኤስ.አይ.ኤም ከታተመውና የአዲስ ኪዳን የጥናት መምሪያና ማብራሪያ፣ ከተሰኘው መጽሐፍ ነው፡፡ እግዚአብሔር አገልግሎታቸውን ይባርክ፡፡)


የኤፌሶን መልእክት መግቢያ
ተስፋጽዮን በጀማ የወንጌል ስብከት ላይ ስለ ክርስቶስ ሰምቶ በክርስቶስ አመነ። ከዚያ በኋላ ከተለያዩ አብያተ ክርስቲያናት ተወካዮች ጋር ተገናኘ። በስብሰባው ላይ የቃለ ሕይወት፥ የመካነ ኢየሱስ፥ የሙሉ ወንጌል፥ የመሠረተ ክርስቶስ፥ የሕይወት ብርሃንና የሌሎች ብዙ አብያተ ክርስቲያናት መሪዎች ነበሩ። ሁሉም ተስፋጽዮን ወደ ቤተ ክርስቲያናቸው እንዲመጣ ገፋፉት። ሁሉም ወደ ቤተ ክርስቲያናቸው እንዲመጣ ለማግባባት፥ «ከሁሉም የሚበልጡ ብዙ ምእመናን አሉን። ቃሉን እናስተምራለን። የመንፈስ ቅዱስ ስጦታዎች አሉን» ሲሉ አዋከቡት። ተስፋጽዮን በዚህ ሁኔታ ግራ ተጋባ። «ቤተ ክርስቲያን ምንድን ናት? እንዲህ ቤተ እምነቶች የበዙት ለምንድን ነው? ትክክለኛው ቤተ እምነት የትኛው ነው?» ሲል ራሱን ጠየቀ።
ጥያቄ፡- ሀ) የተለያዩ ቤተ እምነቶች አዳዲስ ክርስቲያኖችንና አማኞች ያልሆኑትን ሰዎች ግራ የሚያጋቡት እንዴት ነው? ለ) ቤተ እምነቶች የበዙት ለምንድን ነው? ሐ) ጤናማ ይመስልሃል? ለምን? መ) በአማርኛ ቋንቋ «ቤተ ክርስቲያን» የሚለው ቃል ምን ትርጉም ይሰጣል?
በአሁኑ ዘመን ብዙ ወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት የሚገኙ ሲሆን፥ ሌሎች ብዙዎችም እዚሁ ቅርንጫፎችን ለመመሥረት ከምዕራባውያን አገሮች እየጎረፉ ናቸው። እነዚህ ብዙ ቤተ እምነቶች የሚመጡት ከየት ነው? ቤተ እምነቶች የበዙትስ ለምንድን ነው? በኢትዮጵያ ውስጥ የሚገኙት አብዛኛዎቹ ቤተ እምነቶች ከሚከተሉት ምንጮች የመጡ ናቸው።
በመጀመሪያ፥ ከምዕራቡ ዓለም የመነጩ ቤተ እምነቶች አሉ። የተለያዩ ሚስዮናውያን ወደ ኢትዮጵያ መጥተው በአገራቸው ያሉትን ዓይነት ቤተ እምነቶች መሥርተዋል። እነዚህ ቤተ እምነቶች ከየት የመጡ ናቸው? አብዛኞቹ የምዕራቡ ዓለም ቤተ እምነቶች በትናንሽ የአስተምህሯዊ ልዩነቶች ምክንያት የተፈጠሩ ናቸው። ከእነዚህ አስተምህሯዊ ልዩነቶች መካከል አንዳንዶቹ የሕፃናት ወይም የአዋቂዎች ጥምቀት፥ የቅዱስ ቁርባን ፍችና የመንፈስ ቅዱስ ቀዳሚ አገልግሎት ምንነትን የሚመለከቱ ናቸው።
ሁለተኛ፥ ሌሎች ቤተ እምነቶች የራሳቸውን ቤተ እምነቶች የጀመሩትን ታላላቅ መሪዎች፥ ሰባኪዎች ወይም የፈውስ አገልጋዮች በመከተል የተመሠረቱ ናቸው። ይህ በኢትዮጵያ ብዙም ያልተለመደ ቢሆንም፥ በሌሎች የአፍሪካ አገሮች ግን በመቶዎች የሚቆጠሩ ቤተ እምነቶች በመሪዎች ስም ተመሥርተዋል።
ሦስተኛ፥ የአንዲት ቤተ ክርስቲያን መእመናን በሰላም ለመኖር ባለመቻላቸው ምክንያት የተጀመሩ ቤተ እምነቶችም አሉ።
ባለመስማማታቸው ምክንያት ተከፋፍለው የየራሳቸውን ቤተ እምነቶች ይመሠርታሉ። ብዙውን ጊዜ የእነዚህ ክፍፍሎች ምክንያቶች፥ ጎሰኝነት በተወሰኑ ልምምዶች ላይ በሚከሰቱ የአመለካከት ልዩነቶች ወይም ሰብአዊ ኩራት ናቸው።
የሚያሳዝነው ከእነዚህ ምክንያቶች አንዳቸውም አዲስ ቤተ እምነት ለመመሥረት የሚያበቁ አለመሆናቸው ነው። ሁልጊዜም በትናንሽ የመጽሐፍ ቅዱስ አስተምህሮዎች ላይ የአሳብ ልዩነት የሚያሳዩ ክርስቲያኖች ይኖራሉ። ዓይን ለዓይን እንኳን መተያየት የማይፈልጉ መሪዎችም ይኖራሉ። ሁልጊዜም በቤተ ክርስቲያን ውስጥ በተወሰኑ ጉዳዮች ወይም ልምምዶች ላይ ውጥረቶች ይኖራሉ። እግዚአብሔር ግን ከእነዚህ ምክንያቶች አንዱም አዲስ ቤተ እምነት ለመጀመር ብቁ መሆናቸውን አያረጋግጥም። ክርስቲያኖች ባለመስማማታቸው ምክንያት መከፋፈል መከሰቱ እጅግ አሳዛኝ ነገር ነው። በዮሐንስ 17 ክርስቶስ ተከታዮቹ አንድነትን እንዲመሠርቱ ጸልዮአል። ጳውሎስ ክርስቲያኖች አንድ አሳብ እንዲኖራቸው ተማጽኗል (ፊልጵ. 2፡1-2)። ነገር ግን ከኃጢአተኝነታችንና ከኩራታችን የተነሣ ክፍፍሎች ይከሰታሉ።
የቤተ እምነቶች መፈጠር ስሕተት ነውን? የተመሠረቱበት ዓላማ ስሕተት ከሆነ፥ እንዲሁም የውድድርና የኩራት መንፈስ የሚታይባቸው ከሆነ፥ የቤተ እምነቶች መፈጠር ትክክል ሊሆን አይችልም። አንዱ ቤተ እምነት ከሌሎች እንደሚበልጥ ሲያስተምርና የተለያዩ ቤተ እምነቶች ተከታዮች እርስ በርሳቸው ቢጣሉ፥ ወይም አንዱ የሌላውን አባላት ለመውሰድ ቢሞክር፥ ይህ የአንድ ቤተሰብ አባላት የሆኑ ወንድማማቾችን ማጣላት ያህል አስከፊ ነው።
በሌላ በኩል፥ የተለያዩ ቤተ እምነቶች መፈጠር እግዚአብሔርን ሊያስከብር ይችላል። የተለያዩ ብዙ ዓይነት ዛፎች ለአንድ አካባቢ ውበትን እንደሚጨምሩ ሁሉ፥ የተለያዩ የአምልኮ ስልቶችና ልምምዶች ያሏቸው ብዙ ቤተ እምነቶች የውበት መገለጫዎች ሊሆኑ ይችላሉ። ነገር ግን ይህ የቤተ እምነቶች ልዩነት የታላቁ የክርስቶስ አካል ክፍሎች የመሆናችንን አንድነት ያገናዘበ ሊሆን ይገባል። በፍጥረት ውስጥ የምንመለከተው በአንድነት ውስጥ ያለ ልዩነት በቤተ ክርስቲያንም ውስጥ ሊንጸባረቅ ይገባል።
የኤፌሶን መልእክት በክርስቶስ አካል ወይም በቤተ ክርስቲያን ላይ ያተኩራል። ቤተ ክርስቲያን ምንድን ናት? በአማርኛ ቋንቋ፥ ቃሉ ሕንፃ ወይም የክርስቲያኖችን መሰብሰቢያ ያመለክታል። አዲስ ኪዳን ግን ሕንፃን ለማመልከት «ቤተ ክርስቲያን» የሚለውን ቃል የተጠቀመበት ስፍራ የለም። እንዲያውም፥ ከሐዋርያት ዘመን ጀምሮ ለብዙ መቶ ዓመታት ክርስቲያኖች ሁነኛ የመሰባሰቢያ ስፍራ አልነበራቸውም። በአዲስ ኪዳን ቤተ ክርስቲያንን የሚለው ቃል በሰዎች ላይ ያተኩራል። በግሪክ ቋንቋ፥ ቃሉ «ጉባኤ»ን ወይም የተወሰኑ ሰዎችን «አብሮ መሰባሰብ» ያመለክታል። የአንዲት ከተማ ነዋሪዎች ለስብሰባ ተጠርተው የሚያካሂዱት ስብሰባ ቤተ ክርስቲያን ይባል ነበር። ስለሆነም ከዓለም ወደ ክርስቶስ አካል የተጠሩት ክርስቲያኖች የሚያካሂዱትም ስብሰባ ቤተ ክርስቲያን ይባላል።
በአዲስ ኪዳን፥ ቤተ ክርስቲያን የሚለው ቃል ሦስት የክርስቲያን ቡድኖችን ሊያመለክት ይችላል። በመጀመሪያ፥ ብዙውን ጊዜ የአጥቢያ ክርስቲያኖችን በአንድ አካባቢ መሰባሰብ ሊያመለክት ይችላል (ሮሜ 16፡5)። አብዛኞቹ የቀድሞዎቹ አብያተ ክርስቲያናት በግለሰቦች ቤቶች ውስጥ ይሰባሰቡ ነበር። ወደ 50 የሚሆኑ ሰዎች በመደበኛነት በግለሰቦች ቤቶች ውስጥ እየተሰባሰቡ ያመልኩና መጽሐፍ ቅዱስ ያጠኑ ነበር። ሁለተኛ ቤተ ክርስቲያን የሚለው ቃል በአንድ መልክዓ ምድራዊ ክልል ውስጥ የሚገኙትን ክርስቲያኖች ሊያመለክት ይችላል። ለምሳሌ ያህል፥ ጳውሎስ ለሮሜ ወይም ለቆሮንቶስ ቤተ ክርስቲያን ጽፎአል። እነዚህ አብያተ ክርስቲያናት ከአንድ ሕንፃ ሥር የሚሰባሰቡ ሳይሆኑ፥ በተለያዩ ቤቶች ውስጥ የሚሰባሰቡ የአንድ አካባቢ ክርስቲያኖች ነበሩ። ዛሬ በተመሳሳይ ሁኔታ «የአፍሪካ ቤተ ክርስቲያን» ወይም «የብሪታኒያ ቤተ ክርስቲያን» ልንል እንችላለን። ሦስተኛ፥ ዓለም አቀፋዊት (ዩኒቨርሳል) ቤተ ክርስቲያን አለች። ይህ የሞቱትንና በሕይወት ያሉትን፥ በሰማይና በምድር ያሉትን ጨምሮ የክርስቶስ አካል የሆኑትን ሁሉ ያጠቃልላል (ዕብ. 12፡23)። ጳውሎስ በኤፌሶን መልእክት ውስጥ ስለ አጽናፈ አቀፉዋ ቤተ ክርስቲያን ደጋግሞ ጠቅሷል።
ሐዋርያው ጳውሎስ፥ እግዚአብሔር በዓለም ውስጥ የሚያከናውነው ታላቁ ሥራ የክርስቶስን አካል መገንባት እንደሆነ ተገንዝቧል። ኢየሱስ ክርስቶስ በእርሱ ያመኑና የሚከተሉት ሰዎች ሁሉ የሚገኙባት ዓለም አቀፋዊት ቤተ ክርስቲያን ራስ ነው። እግዚአብሔር በቤተ ክርስቲያን ውስጥ ለእያንዳንዱ አማኝ የተለየ ስጦታ ይሰጣል። አማኙ በዚህ ስጦታው ሌሎችን በማገልገል ክርስቶስን ያገለግላል። ይህ የአማኞች አካል በምድር ላይ ክርስቶስን ይወክላል። ወንጌሉን ስንመሰክር አፉ፥ እርስ በርሳችንና ሌሎችን ስንረዳ እጆቹ፥ እንዲሁም ወንጌሉን ወደ ዓለም ሁሉ ስናዳርስ እግሮቹ ሆነን እንሠራለን። ጳውሎስ


የመጽሐፈ መክብብ ዓላማ እና ዋና ዋና ትምሕርቶች
የመጽሐፈ መክብብ ዓላማ
የምናጠናው የጥበብ መጻሕፍት በመባል የሚታወቁትን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች እንደሆነ ታስታውሳለህ። መጽሐፈ መክብብ ከጥበብ መጻሕፍት አንዱ ነው። የመጀመሪያው፥ የጥበብ መጽሐፍ የሆነው መጽሐፈ ኢዮብ ጻድቅ ለምን መከራ ይቀበላል? ለሚለው ጥያቄ መልስ ለመስጠት ይሞክራል። መዝሙረ ዳዊት እግዚአብሔርን በማምለክ የሚገኘውን የጥበብ መሠረት ሲሰጠን፥ መጽሐፈ ምሳሌ ደግሞ በሕይወታችን እንዴት መኖር እንዳለብን የሚያሳዩ ተግባራዊ መልሶች በማቅረብ የጥበብን መሠረት ይሰጠናል። መጽሐፈ መክብብ በሕይወት ዓላማ ላይ በማተኮር፥ ያለ እግዚአብሔር ሕይወት ከንቱ እንደሆነ ያስተምረናል። መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን ደግሞ ጥበብ የሞላበት የጋብቻ ግንኙነት የሚመሠረተው በእውነተኛ ፍቅር ላይ እንደሆነ ያስተምረናል።
መጽሐፈ መክብብ የተጻፈው፥ «አንድ ሰው ደስታንና የዓላማን መከናወን በሕይወቱ ውስጥ እንዴት ሊያገኝ ይችላል?» (መክብብ 1፡3) ለሚል ዐቢይ የፍልስፍና ጥያቄ መልስ ለማስገኘት ነበር። «ከፀሐይ በታች» ባለ ነገር ውስጥ ሁሉ የሕይወትን ዓላማ ስለሚፈልግ ሰው የተጻፈ መጽሐፍ ነው። «ከፀሐይ በታች» የሚለው ሐረግ ከእግዚአብሔር ውጭ ላሉ ለማናቸውም ነገሮች የተሰጠ ስም ነው። በመሠረቱ ጸሐፊው «እግዚአብሔር ባይኖር ኖሮ ወይም እኔ የምኖረው እግዚአብሔር እንደሌለ ቆጥሬ ቢሆን ኖሮ፥ ምን እሆን ነበር? ሕይወት ትርጕም ይኖራት ነበርን? » በማለት ይናገራል። ስለዚህ ጸሐፊው በሕይወት ውስጥ ምናልባት ትርጉም ባገኝ ብሉ የተለያዩ ነገሮችን መመልከት ይጀምራል። ምናልባት ሕይወት ያለ እግዚአብሔር ትርጕም ይኖረው እንደሆነ በማለት የተለያዩ የታወቁ የዓለም ፍልስፍናዎችን መርምሯል ለማለት እንችላለን። ማጠቃለያው «ሁሉም ከንቱ ነው» የሚል ነው። (በመጽሐፉ ውስጥ ይህንን ዓረፍተ ነገር 25 ጊዜ ተደጋግሞ እናገኘዋለን)።
1. ጸሐፊው ትኲረቱን ወደ ሳይንስ በማድረግ በምድር ላይ ያሉ ነገሮች ትርጕም ይኖራቸው እንደሆነ ለመረዳት ምርምር አድርጓል። ሳይንስ ማድረግ የሚችለው ችግሮችን ማየት እንጂ መፍትሔ መስጠት አይደለም (መክብብ 1፡4-10።
የውይይት ጥያቄ፥ ለእግዚአብሔር ክብርን ሳይሰጥ ነገሮችን ሁሉ ለማብራራት በሚሞክረው ዘመናዊ ሳይንስ ላይ ከሚገባ በላይ እንዳንደገፍ ይህ እንዴት ሊያስጠነቅቀን ይገባል?
2. ጸሐፊው ዓለማዊ ጥበብ፥ ፍልስፍናና ትምህርት ለሕይወት ትርጕም ይሰጡ እንደሆነ ለማየት ምርመራ አካሄደ፤ ነገር ግን ዓለማዊ ጥበብ እውነተኛ መልሶችን ለመስጠት አይችልም። ጥበበኛውም ሆነ ሞኙም ሳይቀር ሁሉንም ሰው ሞት ይጠባበቀዋል። ችግሮች በሁሉም ስፍራ አሉ።
3. ጸሐፊው፥ ሰው ራሱን ለማስደሰት ሲል ብቻ በራስ ወዳድነት የሚገፋውን የምቾት ሕይወት ተመልክቷል፤ ነገር ግን ያም ደስታ በራሱ ከንቱ መሆኑን ለማየት ጊዜ አልወሰደበትም።
4. ቀጥሎ ጸሐፊው፥ ሰዎች ለሕይወት ደስታና ትርጒም ይሰጣል ብለው የሚያስቡትን አንድ ነገር ይመለከታል። ይህም ሀብት ነው። ሀብት እርካታ ይሰጣልን? ጸሐፊው አይሰጥም ይላል፤ ምክንያቱም ሰው በሚሞትበት ጊዜ የአንድ ሰው ሀብት ወደ ሌላው ስለሚተላለፍ ሰውዬው በሙላት ደስታን አያገኝበትም።
5. ጸሐፊው የሰውን ሕይወት መለወጥ ወደማይችል፥ ሆኖም እግዚአብሔርን የማምለክ ሥርዓት ወደሚታዩበት ሃይማኖት ሳይቀር ተመልክቶ ነበር። ከእግዚአብሔር ጋር እውነተኛ ግንኙነት የሌለበት ሃይማኖትም ከንቱ ነው።
የውይይት ጥያቄ፥ እነዚህን እውነቶች ክርስቲያኖች ያስታውሷቸው ዘንድ አስፈላጊ የሚሆነው ለምንድን ነው?
ጸሐፊው፥ የሰው ልጅ ዋጋ ያለው ነው ብሎ የሚቈጥረውን ነገር ሁሉ በመመርመር፥ የሚከተሉትን ማጠቃለያዎች ይሰጣል፡-
1. ሕይወት ትርጕም እንዲሰጥና ዓላማ እንዲኖረው፥ እግዚአብሔር የነገሮች ሁሉ ማዕከል መሆኑን በመገንዘብ መኖር ይገባናል። ሕይወት የራሱ የሆኑ ስንክሳራዊ ሁኔታዎችና ችግሮች ሲኖሩት የእግዚአብሔርን ዓላማ በማንረዳበት ጊዜ እንኳ እርሱ ዓላማውን በመፈጸም ላይ መሆኑን ማስታወስ ለእኛ ለክርስቲያኖች አስፈላጊ ነው። ያለ እግዚአብሔር፥ ማንኛውም ነገር ትርጕም የሌለው ከንቱ ነገር ነው።
2. የሕይወትን ትርጒም ለማወቅ መሠረታዊው ነገር በእግዚአብሔር መታመን ነው። ነገሮች ሁሉ በእግዚአብሔር ቁጥጥር ሥር መሆናቸውን ማመን አለብን (መክብብ 3፡1-15፤ 6፡1-2፤ 9፡1)።
3. ሕይወት በአብዛኛው ዓላማ ያለው ባይመስልም፥ አስተማማኝ በሆነ ትዕግሥት በእግዚአብሔር ላይ ተደግፈን፥ እርሱ በሰጠን መልካም ነገሮች ሁሉ ደስ እየተሰኘን ልንኖር ይገባል (መክብብ 2፡24-26፤ 11፡8)።
4. ሕይወት ትርጒም የሚኖረው፥ እግዚአብሔርን በመታዘዝና በምናደርገው ነገር ሁሉ እርሱ ፈራጅ እንደሆን በመገንዘብ የምንኖር ስንሆን ነው (መክብብ 8፡8-9፤ 12፡13)። እግዚአብሔር ደስታንና ዓላማን ይሰጣል። የእውነተኛ ጥበብ መሠረት እግዚአብሔርን መፍራት ነው (መክብብ 3፡14፤ 5፡7፤ 7፡18)። ክርስቲያን ባለው ነገር የሚረካ መሆን አለበት (መክብብ 2፡24-25፤ 3፡10-13)።
መጽሐፈ መክብብ የተጻፈው በዓለም የሚኖሩ ሰዎች ሕይወታቸውን እንዲመረምሩና ከንቱ መሆኑን እንዲያዩ ለመገፋፋት ነው። ከዚያም ጸሐፊው ወደ እግዚአብሔር እንዲመለሱና በእርሱ የሕይወትን ትርጒም እንዲሹ ይፈልግ ነበር። ያለ እግዚአብሔር፥ የሕይወት ትርጒምና እውነተኛ ደስታ የለም።
የውይይት ጥያቄ፥ ለእኛ እነዚህን እውነቶች ማስታወስ የሚያስፈልገን ለምንድን ነው?
ዋና ዋና ትምህርቶች፡-
1. እንደ ሌሎቹ የጥበብ መጻሕፍት ሁሉ፥ መጽሐፈ መክብብ ጻድቅ እንደሚባረክና ኃጢአተኛ ሰው እንደሚቀጣ በሚናገረው መመሪያ ላይ ያተኲራል። መጽሐፈ መክብብ ይህንን እውነት የሚደግፍ ቢሆንም እንኳ ሰዎች የሌሎችን ጽድቅ ወይም ክፋት በዚህ መመሪያ በመመዘን እንዳይፈርዱ ያስጠነቅቃል። ጸሐፊው ጻድቃንም ሆኑ ኃጥአን እንደሚሞቱ ይናገራል። ብዙ ጊዜ ጻድቃን በግፍ የገደሉ፥ ድሆች፥ የተጨቆኑና ወዘተ. ናቸው።
2. መጽሐፈ መክብብ መጽሐፍ ቅዱስ በሚያስተምረው መሠረት ዓለምን መመልከት አስፈላጊ እንደሆነ ያስተምራል። ከእግዚአብሔር ውጭ («ከፀሐይ በታች») ያለውን የዓለምን አመለካከት ያቀርባል። በትክክል ስንመዝናቸው ሁሉም ትርጕም አልባና ከንቱዎች ናቸው። ክርስቲያን ስለ ዓለም ያለው አመለካከት አንድን ሰው በእግዚአብሔር ምክንያት ደስ ወደሚሰኝበት ሕይወት እንደሚመራው ያስተምራል። እግዚአብሔር መልካም ነገሮችን ይሰጠናል። ለምናደርገው ነገር ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት ተጠያቂዎች ስለሆንን እርሱን በመፍራትና በመታዘዝ መኖር ይገባናል።
የውይይት ጥያቄ፥ ሀ) እነዚህ ሁለት ትምህርቶች በቤተ ክርስቲያንህ ውስጥ የሚያስፈልጉት ለምንድን ነው? ለ) ክርስቲያኖች ብዙ ጊዜ በዓለም አስተሳሰብ የሚሳቡባቸው መንገዶች ምንድን ናቸው? ሐ) እነዚህ እውነቶች ክርስቲያኖች ለእግዚአብሔር ከመኖር ውጭ፥ የዓለም ነገሮች ሁሉ ጥቅም የሌላቸው ከንቱዎች እንደሆኑ እንዲያውቁ እንዴት ይረዷቸዋል? መ) እነዚህን እውነቶች በቤተ ክርስቲያንህ ውስጥ ለሚገኙ ሰዎች እንዴት ልታስተምራቸው ትችላለህ?
(ማብራሪያው የተወሰደው በ ኤስ.አይ.ኤም ከታተመውና የብሉይ ኪዳን የጥናት መምሪያና ማብራሪያ፣ ከተሰኘው መጽሐፍ ነው፡፡ እግዚአብሔር አገልግሎታቸውን ይባርክ፡፡)


SPEAK ENGLISH dan repost
❤️ ✍️ "Miira jaalalaa namatti dhaga'amu parsantiin 70% maal akka ta'e beektuu?...." ➡️ As tuquun dubbisaa.

🔜 See More
See More


🥰

➡️ Channel jaalatamoo ergaalee ajaaibsiisoo fi barsiisoo ta'an qabu kana irratti gadi tuquudhaan JOIN taasisaa! ➡️ JOIN 📌

1️⃣ 💡💡💡💡💡💡💡

     🚘 'https://t.me/addlist/4e8EfR1mqNFlY2E8' rel='nofollow'>JOIN
    JOIN

2️⃣ 💡💡💡💡💡💡💡

    🚩 MORE JOIN  🚩
   🚩 MORE JOIN 🚩


3️⃣💡💡💡💡💡💡💡
    🍰MORE JOIN  🕯
   🍰 MORE JOIN 🕯


𝙰𝚍𝚍 𝚢𝚘𝚞𝚛 𝙲𝚑𝚊𝚗𝚗𝚎𝚕
➕ ᥲძძ ᥡ᥆ᥙr ᥴһᥲᥒᥒᥱᥣ

📌 Channel keessan tolaan nu waliin beeksifadhaa


Hope Promotion dan repost
❤️🟢 Sababiilee jaalala dhugaa booressuu danda'an (5) kanneen irraa fagaadhu. ➡️ See More

↪️  See More
      See More


Fedhii fi hawwiin kee yeroo hundumaa murtoo qajeelaa akka murteessitu waan si taasisaniif, fedhii fi hawwii kee adda baafattee qajeelummaatti eeggachuuf➡️See More


🥰

➡️ Channel jaalatamoo ergaalee ajaaibsiisoo fi barsiisoo ta'an qabu kana irratti gadi tuquudhaan JOIN taasisaa! ➡️ JOIN 📌

1️⃣ 💡💡💡💡💡💡💡

     🚘 'https://t.me/addlist/4e8EfR1mqNFlY2E8' rel='nofollow'>JOIN
    JOIN

2️⃣ 💡💡💡💡💡💡💡

    🚩 MORE JOIN  🚩
   🚩 MORE JOIN 🚩


3️⃣💡💡💡💡💡💡💡
    🍰MORE JOIN  🕯
   🍰 MORE JOIN 🕯


𝙰𝚍𝚍 𝚢𝚘𝚞𝚛 𝙲𝚑𝚊𝚗𝚗𝚎𝚕
➕ ᥲძძ ᥡ᥆ᥙr ᥴһᥲᥒᥒᥱᥣ

📌 Channel keessan tolaan nu waliin beeksifadhaa


የመጽሐፈ መክብብ ዓላማ እና ዋና ዋና ትምሕርቶች
የመጽሐፈ መክብብ ዓላማ
የምናጠናው የጥበብ መጻሕፍት በመባል የሚታወቁትን የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች እንደሆነ ታስታውሳለህ። መጽሐፈ መክብብ ከጥበብ መጻሕፍት አንዱ ነው። የመጀመሪያው፥ የጥበብ መጽሐፍ የሆነው መጽሐፈ ኢዮብ ጻድቅ ለምን መከራ ይቀበላል? ለሚለው ጥያቄ መልስ ለመስጠት ይሞክራል። መዝሙረ ዳዊት እግዚአብሔርን በማምለክ የሚገኘውን የጥበብ መሠረት ሲሰጠን፥ መጽሐፈ ምሳሌ ደግሞ በሕይወታችን እንዴት መኖር እንዳለብን የሚያሳዩ ተግባራዊ መልሶች በማቅረብ የጥበብን መሠረት ይሰጠናል። መጽሐፈ መክብብ በሕይወት ዓላማ ላይ በማተኮር፥ ያለ እግዚአብሔር ሕይወት ከንቱ እንደሆነ ያስተምረናል። መኃልየ መኃልይ ዘሰሎሞን ደግሞ ጥበብ የሞላበት የጋብቻ ግንኙነት የሚመሠረተው በእውነተኛ ፍቅር ላይ እንደሆነ ያስተምረናል።
መጽሐፈ መክብብ የተጻፈው፥ «አንድ ሰው ደስታንና የዓላማን መከናወን በሕይወቱ ውስጥ እንዴት ሊያገኝ ይችላል?» (መክብብ 1፡3) ለሚል ዐቢይ የፍልስፍና ጥያቄ መልስ ለማስገኘት ነበር። «ከፀሐይ በታች» ባለ ነገር ውስጥ ሁሉ የሕይወትን ዓላማ ስለሚፈልግ ሰው የተጻፈ መጽሐፍ ነው። «ከፀሐይ በታች» የሚለው ሐረግ ከእግዚአብሔር ውጭ ላሉ ለማናቸውም ነገሮች የተሰጠ ስም ነው። በመሠረቱ ጸሐፊው «እግዚአብሔር ባይኖር ኖሮ ወይም እኔ የምኖረው እግዚአብሔር እንደሌለ ቆጥሬ ቢሆን ኖሮ፥ ምን እሆን ነበር? ሕይወት ትርጕም ይኖራት ነበርን? » በማለት ይናገራል። ስለዚህ ጸሐፊው በሕይወት ውስጥ ምናልባት ትርጉም ባገኝ ብሉ የተለያዩ ነገሮችን መመልከት ይጀምራል። ምናልባት ሕይወት ያለ እግዚአብሔር ትርጕም ይኖረው እንደሆነ በማለት የተለያዩ የታወቁ የዓለም ፍልስፍናዎችን መርምሯል ለማለት እንችላለን። ማጠቃለያው «ሁሉም ከንቱ ነው» የሚል ነው። (በመጽሐፉ ውስጥ ይህንን ዓረፍተ ነገር 25 ጊዜ ተደጋግሞ እናገኘዋለን)።
1. ጸሐፊው ትኲረቱን ወደ ሳይንስ በማድረግ በምድር ላይ ያሉ ነገሮች ትርጕም ይኖራቸው እንደሆነ ለመረዳት ምርምር አድርጓል። ሳይንስ ማድረግ የሚችለው ችግሮችን ማየት እንጂ መፍትሔ መስጠት አይደለም (መክብብ 1፡4-10።
የውይይት ጥያቄ፥ ለእግዚአብሔር ክብርን ሳይሰጥ ነገሮችን ሁሉ ለማብራራት በሚሞክረው ዘመናዊ ሳይንስ ላይ ከሚገባ በላይ እንዳንደገፍ ይህ እንዴት ሊያስጠነቅቀን ይገባል?
2. ጸሐፊው ዓለማዊ ጥበብ፥ ፍልስፍናና ትምህርት ለሕይወት ትርጕም ይሰጡ እንደሆነ ለማየት ምርመራ አካሄደ፤ ነገር ግን ዓለማዊ ጥበብ እውነተኛ መልሶችን ለመስጠት አይችልም። ጥበበኛውም ሆነ ሞኙም ሳይቀር ሁሉንም ሰው ሞት ይጠባበቀዋል። ችግሮች በሁሉም ስፍራ አሉ።
3. ጸሐፊው፥ ሰው ራሱን ለማስደሰት ሲል ብቻ በራስ ወዳድነት የሚገፋውን የምቾት ሕይወት ተመልክቷል፤ ነገር ግን ያም ደስታ በራሱ ከንቱ መሆኑን ለማየት ጊዜ አልወሰደበትም።
4. ቀጥሎ ጸሐፊው፥ ሰዎች ለሕይወት ደስታና ትርጒም ይሰጣል ብለው የሚያስቡትን አንድ ነገር ይመለከታል። ይህም ሀብት ነው። ሀብት እርካታ ይሰጣልን? ጸሐፊው አይሰጥም ይላል፤ ምክንያቱም ሰው በሚሞትበት ጊዜ የአንድ ሰው ሀብት ወደ ሌላው ስለሚተላለፍ ሰውዬው በሙላት ደስታን አያገኝበትም።
5. ጸሐፊው የሰውን ሕይወት መለወጥ ወደማይችል፥ ሆኖም እግዚአብሔርን የማምለክ ሥርዓት ወደሚታዩበት ሃይማኖት ሳይቀር ተመልክቶ ነበር። ከእግዚአብሔር ጋር እውነተኛ ግንኙነት የሌለበት ሃይማኖትም ከንቱ ነው።
የውይይት ጥያቄ፥ እነዚህን እውነቶች ክርስቲያኖች ያስታውሷቸው ዘንድ አስፈላጊ የሚሆነው ለምንድን ነው?
ጸሐፊው፥ የሰው ልጅ ዋጋ ያለው ነው ብሎ የሚቈጥረውን ነገር ሁሉ በመመርመር፥ የሚከተሉትን ማጠቃለያዎች ይሰጣል፡-
1. ሕይወት ትርጕም እንዲሰጥና ዓላማ እንዲኖረው፥ እግዚአብሔር የነገሮች ሁሉ ማዕከል መሆኑን በመገንዘብ መኖር ይገባናል። ሕይወት የራሱ የሆኑ ስንክሳራዊ ሁኔታዎችና ችግሮች ሲኖሩት የእግዚአብሔርን ዓላማ በማንረዳበት ጊዜ እንኳ እርሱ ዓላማውን በመፈጸም ላይ መሆኑን ማስታወስ ለእኛ ለክርስቲያኖች አስፈላጊ ነው። ያለ እግዚአብሔር፥ ማንኛውም ነገር ትርጕም የሌለው ከንቱ ነገር ነው።
2. የሕይወትን ትርጒም ለማወቅ መሠረታዊው ነገር በእግዚአብሔር መታመን ነው። ነገሮች ሁሉ በእግዚአብሔር ቁጥጥር ሥር መሆናቸውን ማመን አለብን (መክብብ 3፡1-15፤ 6፡1-2፤ 9፡1)።
3. ሕይወት በአብዛኛው ዓላማ ያለው ባይመስልም፥ አስተማማኝ በሆነ ትዕግሥት በእግዚአብሔር ላይ ተደግፈን፥ እርሱ በሰጠን መልካም ነገሮች ሁሉ ደስ እየተሰኘን ልንኖር ይገባል (መክብብ 2፡24-26፤ 11፡8)።
4. ሕይወት ትርጒም የሚኖረው፥ እግዚአብሔርን በመታዘዝና በምናደርገው ነገር ሁሉ እርሱ ፈራጅ እንደሆን በመገንዘብ የምንኖር ስንሆን ነው (መክብብ 8፡8-9፤ 12፡13)። እግዚአብሔር ደስታንና ዓላማን ይሰጣል። የእውነተኛ ጥበብ መሠረት እግዚአብሔርን መፍራት ነው (መክብብ 3፡14፤ 5፡7፤ 7፡18)። ክርስቲያን ባለው ነገር የሚረካ መሆን አለበት (መክብብ 2፡24-25፤ 3፡10-13)።
መጽሐፈ መክብብ የተጻፈው በዓለም የሚኖሩ ሰዎች ሕይወታቸውን እንዲመረምሩና ከንቱ መሆኑን እንዲያዩ ለመገፋፋት ነው። ከዚያም ጸሐፊው ወደ እግዚአብሔር እንዲመለሱና በእርሱ የሕይወትን ትርጒም እንዲሹ ይፈልግ ነበር። ያለ እግዚአብሔር፥ የሕይወት ትርጒምና እውነተኛ ደስታ የለም።
የውይይት ጥያቄ፥ ለእኛ እነዚህን እውነቶች ማስታወስ የሚያስፈልገን ለምንድን ነው?
ዋና ዋና ትምህርቶች፡-
1. እንደ ሌሎቹ የጥበብ መጻሕፍት ሁሉ፥ መጽሐፈ መክብብ ጻድቅ እንደሚባረክና ኃጢአተኛ ሰው እንደሚቀጣ በሚናገረው መመሪያ ላይ ያተኲራል። መጽሐፈ መክብብ ይህንን እውነት የሚደግፍ ቢሆንም እንኳ ሰዎች የሌሎችን ጽድቅ ወይም ክፋት በዚህ መመሪያ በመመዘን እንዳይፈርዱ ያስጠነቅቃል። ጸሐፊው ጻድቃንም ሆኑ ኃጥአን እንደሚሞቱ ይናገራል። ብዙ ጊዜ ጻድቃን በግፍ የገደሉ፥ ድሆች፥ የተጨቆኑና ወዘተ. ናቸው።
2. መጽሐፈ መክብብ መጽሐፍ ቅዱስ በሚያስተምረው መሠረት ዓለምን መመልከት አስፈላጊ እንደሆነ ያስተምራል። ከእግዚአብሔር ውጭ («ከፀሐይ በታች») ያለውን የዓለምን አመለካከት ያቀርባል። በትክክል ስንመዝናቸው ሁሉም ትርጕም አልባና ከንቱዎች ናቸው። ክርስቲያን ስለ ዓለም ያለው አመለካከት አንድን ሰው በእግዚአብሔር ምክንያት ደስ ወደሚሰኝበት ሕይወት እንደሚመራው ያስተምራል። እግዚአብሔር መልካም ነገሮችን ይሰጠናል። ለምናደርገው ነገር ሁሉ በእግዚአብሔር ፊት ተጠያቂዎች ስለሆንን እርሱን በመፍራትና በመታዘዝ መኖር ይገባናል።
የውይይት ጥያቄ፥ ሀ) እነዚህ ሁለት ትምህርቶች በቤተ ክርስቲያንህ ውስጥ የሚያስፈልጉት ለምንድን ነው? ለ) ክርስቲያኖች ብዙ ጊዜ በዓለም አስተሳሰብ የሚሳቡባቸው መንገዶች ምንድን ናቸው? ሐ) እነዚህ እውነቶች ክርስቲያኖች ለእግዚአብሔር ከመኖር ውጭ፥ የዓለም ነገሮች ሁሉ ጥቅም የሌላቸው ከንቱዎች እንደሆኑ እንዲያውቁ እንዴት ይረዷቸዋል? መ) እነዚህን እውነቶች በቤተ ክርስቲያንህ ውስጥ ለሚገኙ ሰዎች እንዴት ልታስተምራቸው ትችላለህ?
(ማብራሪያው የተወሰደው በ ኤስ.አይ.ኤም ከታተመውና የብሉይ ኪዳን የጥናት መምሪያና ማብራሪያ፣ ከተሰኘው መጽሐፍ ነው፡፡ እግዚአብሔር አገልግሎታቸውን ይባርክ፡፡)

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.