" ለፍትሃዊ ጥያቄያችን ፍትሃዊ ምላሽ እንሻለን !! "
የመቐለ 70 ካሬ የቤት ግንባታ ማህበራት አመራርና አባላት " ጥያቄያችን ላለፉት 6 ዓመታት ሰሚ ጀሮ አጥቷል " በማለት በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የፕሬዜዳንት ፅ/ቤት በሰላማዊ ሰልፍ ምሬታቸውን ገልፀዋል።
ከ6 ዓመታት በፊት ለአንድ አባወራ 70 ካሬ ሜትር የመኖሪያ የቤት ግንባታ መሬት ለመሰጠት በሚፈቅድ መመሪያ መደራጀታቸው ገልጸው ከጦርነት በኋላ ነባሩ መመሪያ በመጣስ በአፓርታማ ነው የምትስተናገዱት መባላቸው ኢፍትሃዊ እንደሆነ ገልጸዋል።
በትግራይ ደረጃ የተደራጁት እነዚህ 60 ሺህ የ70 ካሬ የቤት ግንባታ ማህበር ጥያቄ አቅራቢዎች የመኖሪያ ቤት የግንባታ መሬት አሰጣጥ አስመልክቶ በክልሉ ከተሞች የሚታየው ወጥ ያልሆነ አሰራር እንዲታረም ድምፃቸውን አስምተዋል።
በሌሎች ከተሞች ተፈቅዶ በመቐለ ከተማ ለ70 ካሬ የቤት መኖሪያ ግንባታ " መሬት አይሰጥም " መባሉ አጅግ እንዳስገረማቸውና እንዳሰዘናቸው ገልፀዋል።
ጥያቄያቸው የተደረጁበት መመሪያ በሚፈቅደው መሰረት የመኖሪያ የቤት ግንባታ መሬት ከማግኘት የዘለለ ፓለቲካዊ ተልእኮና ዓላማ እንደሌለው አስረድተዋል።
ከቤት ኪራይ ስቃይና ሰቆቃ እንዲገላገሉ የሚያስችል መንግስታዊ መፍትሄ እንደሚሹ ተናግረዋል።
ማህበራቱ ዛሬ ሚያዝያ 16/2017 ዓ.ም በፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት አከባቢ የተለያዩ የመብት ጥያቄዎችና መፈክሮች እያሰሙ አስከ እኩለ ቀን ቢጠብቁም ጥያቄዎቻቸው ሰምቶ ምላሽ የሚሰጥ የመንግስት ሃላፊ እንዳልተገኘ የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ከቦታው ሆኖ መረጃውን ልኳል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMkelle
@tikvahethiopia
የመቐለ 70 ካሬ የቤት ግንባታ ማህበራት አመራርና አባላት " ጥያቄያችን ላለፉት 6 ዓመታት ሰሚ ጀሮ አጥቷል " በማለት በትግራይ ጊዚያዊ አስተዳደር የፕሬዜዳንት ፅ/ቤት በሰላማዊ ሰልፍ ምሬታቸውን ገልፀዋል።
ከ6 ዓመታት በፊት ለአንድ አባወራ 70 ካሬ ሜትር የመኖሪያ የቤት ግንባታ መሬት ለመሰጠት በሚፈቅድ መመሪያ መደራጀታቸው ገልጸው ከጦርነት በኋላ ነባሩ መመሪያ በመጣስ በአፓርታማ ነው የምትስተናገዱት መባላቸው ኢፍትሃዊ እንደሆነ ገልጸዋል።
በትግራይ ደረጃ የተደራጁት እነዚህ 60 ሺህ የ70 ካሬ የቤት ግንባታ ማህበር ጥያቄ አቅራቢዎች የመኖሪያ ቤት የግንባታ መሬት አሰጣጥ አስመልክቶ በክልሉ ከተሞች የሚታየው ወጥ ያልሆነ አሰራር እንዲታረም ድምፃቸውን አስምተዋል።
በሌሎች ከተሞች ተፈቅዶ በመቐለ ከተማ ለ70 ካሬ የቤት መኖሪያ ግንባታ " መሬት አይሰጥም " መባሉ አጅግ እንዳስገረማቸውና እንዳሰዘናቸው ገልፀዋል።
ጥያቄያቸው የተደረጁበት መመሪያ በሚፈቅደው መሰረት የመኖሪያ የቤት ግንባታ መሬት ከማግኘት የዘለለ ፓለቲካዊ ተልእኮና ዓላማ እንደሌለው አስረድተዋል።
ከቤት ኪራይ ስቃይና ሰቆቃ እንዲገላገሉ የሚያስችል መንግስታዊ መፍትሄ እንደሚሹ ተናግረዋል።
ማህበራቱ ዛሬ ሚያዝያ 16/2017 ዓ.ም በፕሬዜዳንት ፅህፈት ቤት አከባቢ የተለያዩ የመብት ጥያቄዎችና መፈክሮች እያሰሙ አስከ እኩለ ቀን ቢጠብቁም ጥያቄዎቻቸው ሰምቶ ምላሽ የሚሰጥ የመንግስት ሃላፊ እንዳልተገኘ የቲክቫህ ኢትዮጵያ የመቐለ ቤተሰብ አባል ከቦታው ሆኖ መረጃውን ልኳል።
ቲክቫህ ኢትዮጵያ
መቐለ
#TikvahEthiopiaFamilyMkelle
@tikvahethiopia