የብሔራዊ ባንክ ውሳኔን ተከትሎ ንግድ ባንክ የዶላር መሸጫ ዋጋውን በ8 ብር ቀነሰ!
ንግድ ባንክ ዛሬ ጥቅምት 5/2017 ዓ.ም. ባወጣው ዕለታዊ የውጭ ምንዛሬ ግብይት የዋጋ ዝርዝር ላይ የዶላር የመሸጫ ዋጋው ከትናንቱ ጋር ሲነጻጸር የስምንት ብር ቅናሽ አሳይቷል። ባንኩ ያደረገው ይህ ማስተካከያ በአንድ ዶላር መሸጫ እና መግዣ ዋጋ መካከል ያለውን ልዩነት ወደ ሁለት በመቶ አውርዶታል።
ንግድ ባንክ ሰኞ ጥቅምት 4/2017 ዓ.ም. የዶላር የመሸጫ ዋጋው 123.63 የነበረ ሲሆን መግዣው ደግሞ 112.39 ነበር። ይህም በሁለቱ ዋጋዋች መካከል የነበረው ልዩነት የ9.2 በመቶ ነበር።
የብሔራዊ ባንክ ውሳኔን ተከትሎ ንግድ ባንክ ዛሬ ማክሰኞ ባደረገው የውጭ ምንዛሪ ግብይት ዋጋ ማስተካካየ የዶላር መግዣ 113.13 ተደርጓል።መሸጫውን ደግሞ ወደ 115.39 በመውረድ የስምንት ብር ቅናሽ ታይቶበታል።ይህ የባንኩ እርምጃ ብሔራዊ ባንክ ባስቀመጠው የሁለት በመቶ ልዩነት ውስጥ የሚገኝ ነው።
ብሔራዊ ባንክ አዲሱን መመሪያ በተመለከተ በአገሪቱ ለሚገኙ ሁሉም ባንኮች በደብዳቤ ያሳወቀ ሲሆን እስከ ረቡዕ ድረስ ውሳኔውን ተግባራዊ እንዲያደርጉ አዟል።
@YeneTube @FikerAssefa
ንግድ ባንክ ዛሬ ጥቅምት 5/2017 ዓ.ም. ባወጣው ዕለታዊ የውጭ ምንዛሬ ግብይት የዋጋ ዝርዝር ላይ የዶላር የመሸጫ ዋጋው ከትናንቱ ጋር ሲነጻጸር የስምንት ብር ቅናሽ አሳይቷል። ባንኩ ያደረገው ይህ ማስተካከያ በአንድ ዶላር መሸጫ እና መግዣ ዋጋ መካከል ያለውን ልዩነት ወደ ሁለት በመቶ አውርዶታል።
ንግድ ባንክ ሰኞ ጥቅምት 4/2017 ዓ.ም. የዶላር የመሸጫ ዋጋው 123.63 የነበረ ሲሆን መግዣው ደግሞ 112.39 ነበር። ይህም በሁለቱ ዋጋዋች መካከል የነበረው ልዩነት የ9.2 በመቶ ነበር።
የብሔራዊ ባንክ ውሳኔን ተከትሎ ንግድ ባንክ ዛሬ ማክሰኞ ባደረገው የውጭ ምንዛሪ ግብይት ዋጋ ማስተካካየ የዶላር መግዣ 113.13 ተደርጓል።መሸጫውን ደግሞ ወደ 115.39 በመውረድ የስምንት ብር ቅናሽ ታይቶበታል።ይህ የባንኩ እርምጃ ብሔራዊ ባንክ ባስቀመጠው የሁለት በመቶ ልዩነት ውስጥ የሚገኝ ነው።
ብሔራዊ ባንክ አዲሱን መመሪያ በተመለከተ በአገሪቱ ለሚገኙ ሁሉም ባንኮች በደብዳቤ ያሳወቀ ሲሆን እስከ ረቡዕ ድረስ ውሳኔውን ተግባራዊ እንዲያደርጉ አዟል።
@YeneTube @FikerAssefa