የእግዚአብሔር ሕግ ንጹሕ ነው ነፍስንም ይመለሳል፤ የእግዚአብሔር ምስክር የታመነ ነው ሕጻናትንም ጠቢባን ያደርጋል። የእግዚአብሔር ሥርዓት ቅን ነው ፤ልብን ደስ ያሰኛል ።የእግዚአብሔር ትእዛዝ ብሩህ ነው፤ አይኖችንም ያበራል ::እግዚአብሔርን መፍራት ንጹሕ ነው ለዘለዓለም ያኖራል የእግዚአብሔር ፍርድ እውነት እና ቅንነት በአንድነት ነው ::ከወርቅ እና ከክቡር እንቁ ይልቅ ይወደዳል ፤ከማርና ከማር ወለላም ይልቅ ይጣፍጣል:: ባርያህ ደግሞ ይጠብቀዋል በመጠበቁም ብዙ ዋጋ ይቀበላል ::
(መዝሙር ፲፰፥፯-፲፩)
(መዝሙር ፲፰፥፯-፲፩)