የአረብ መሪዎች የትራምፕን የጋዛ እቅድ ለመቃወም በዛሬዉ እለት ይመክራሉ
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዩናይትድ ስቴትስ የጋዛ ሰርጥ ለመቆጣጠር እና ህዝቦቿን ለማባረር ያቀዱትን እቅድ ለመቃወም ዛሬ አርብ በሳዑዲ አረቢያ የአረብ ሀገራት መሪዎች ተገናኝተዉ ሊመክሩ ነዉ ሲሉ የዲፕሎማቲክ እና የመንግስት ምንጮች አስታዉቀዋል።የሳውዲው አልጋ ወራሽ ልዑል መሀመድ ቢን ሳልማን የባህረ ሰላጤው አረብ ሀገራት፣ ግብፅ እና ዮርዳኖስን መሪዎች በመዲናይቱ ሪያድ ለስብሰባ መጋበዛቸውን የሳዑዲ አረቢያ መንግስት የዜና ወኪል ኤስፒኤ ዘግቧል።
ስብሰባው መደበኛ ያልሆነ እና "መሪዎቹን በሚያገናኝ የቅርብ ወንድማማችነት ግንኙነት ማዕቀፍ" ውስጥ ይካሄዳል ሲል ኤስፒኤ አክሏል፡፡የትራምፕ እቅድ የአረብ ሀገራትን አንድ አድርጎታል፣ ነገር ግን ክልሉን ማን ማስተዳደር እንዳለበት እና መልሶ ግንባታውን እንዴት መደገፍ እንዳለበት ላይ አለመግባባቶች አሉ።የሳዑዲ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ኤክስፐርት የሆኑት ኡመር ከሪም ጉባኤውን ባለፉት አሥርተ ዓመታት ለሰፊው አረብ ዓለም እና ለፍልስጤማዉያን “በጣም አስፈላጊ ነዉ” ብለውታል።
ትራምፕ ዩናይትድ ስቴትስ "የጋዛን ሰርጥ ትቆጣጠራለች" እንዲሁም 2.4 ሚሊዮን ህዝቦቿ ወደ ጎረቤት ግብፅ እና ዮርዳኖስ እንዲዛወሩ ባቀረቡት ጥሪ አለም አቀፋዊ ቁጣ ቀስቅሷል።"የአረብ የጋራ ዕርምጃን በተመለከተ እና በጉዳዩ ላይ የወጡትን ውሳኔዎች በግብፅ ሪፐብሊክ ውስጥ በሚካሄደው የመጪው የአረቦች አስቸኳይ ጉባኤ አጀንዳ ይሆናል" ሲል ኤስፒኤ በመጥቀስ በእስራኤል እና ፍልስጤም ላይ ለመወያየት በመጋቢት 4 ለሚደረገው አስቸኳይ ጉባኤ ዕቅዶች ይያዛሉ ብሏል።
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዚዳንት ዶናልድ ትራምፕ ዩናይትድ ስቴትስ የጋዛ ሰርጥ ለመቆጣጠር እና ህዝቦቿን ለማባረር ያቀዱትን እቅድ ለመቃወም ዛሬ አርብ በሳዑዲ አረቢያ የአረብ ሀገራት መሪዎች ተገናኝተዉ ሊመክሩ ነዉ ሲሉ የዲፕሎማቲክ እና የመንግስት ምንጮች አስታዉቀዋል።የሳውዲው አልጋ ወራሽ ልዑል መሀመድ ቢን ሳልማን የባህረ ሰላጤው አረብ ሀገራት፣ ግብፅ እና ዮርዳኖስን መሪዎች በመዲናይቱ ሪያድ ለስብሰባ መጋበዛቸውን የሳዑዲ አረቢያ መንግስት የዜና ወኪል ኤስፒኤ ዘግቧል።
ስብሰባው መደበኛ ያልሆነ እና "መሪዎቹን በሚያገናኝ የቅርብ ወንድማማችነት ግንኙነት ማዕቀፍ" ውስጥ ይካሄዳል ሲል ኤስፒኤ አክሏል፡፡የትራምፕ እቅድ የአረብ ሀገራትን አንድ አድርጎታል፣ ነገር ግን ክልሉን ማን ማስተዳደር እንዳለበት እና መልሶ ግንባታውን እንዴት መደገፍ እንዳለበት ላይ አለመግባባቶች አሉ።የሳዑዲ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ ኤክስፐርት የሆኑት ኡመር ከሪም ጉባኤውን ባለፉት አሥርተ ዓመታት ለሰፊው አረብ ዓለም እና ለፍልስጤማዉያን “በጣም አስፈላጊ ነዉ” ብለውታል።
ትራምፕ ዩናይትድ ስቴትስ "የጋዛን ሰርጥ ትቆጣጠራለች" እንዲሁም 2.4 ሚሊዮን ህዝቦቿ ወደ ጎረቤት ግብፅ እና ዮርዳኖስ እንዲዛወሩ ባቀረቡት ጥሪ አለም አቀፋዊ ቁጣ ቀስቅሷል።"የአረብ የጋራ ዕርምጃን በተመለከተ እና በጉዳዩ ላይ የወጡትን ውሳኔዎች በግብፅ ሪፐብሊክ ውስጥ በሚካሄደው የመጪው የአረቦች አስቸኳይ ጉባኤ አጀንዳ ይሆናል" ሲል ኤስፒኤ በመጥቀስ በእስራኤል እና ፍልስጤም ላይ ለመወያየት በመጋቢት 4 ለሚደረገው አስቸኳይ ጉባኤ ዕቅዶች ይያዛሉ ብሏል።
በስምኦን ደረጄ
#ዳጉ_ጆርናል