ከሦስት እስከ አምስት ዓመቷ ድረስ በራስ ተነሳሽነት የመሥራት አልያም በተቃራኒው የጥፋተኝነት ስሜትን የምታዳብርበት ወቅት ነው። የብላቴና ዘመን ዕቅዶቿን ለማሳካት በምታደርገው መውተርተር የሚሰጣት ምላሽ ይሄንን ስሜት እንዲገነባ ያደርጋል። እዚህ ጋር ሎዛ የምትባለው ገጸባሕርይ ከልጅነቷ ጀምሮ መሥራት የምትፈልገውን ነገር ያለማንም ከልካይ ትከውን እንደ ነበር በታሪኳ መሐል ተሰንጎ እናገኛለን። ሎዛ ከጥፋተኝነት ስሜት የራቀ ማንነት የገነባችው በአባቷ ምክንያት ነው። በራስ ተነሳሽነት አንዳች ነገር ስትጀምር ከአባቷ ዘንድ ቅቡልነት ታገኝ ስለነበር ከአደገች በኋላም ይሄን የማኅበራዊ ልቦናዊ ጡብ የምናገኘው በአዎንታዊው ኩርባ ነው።
ከስድስት እስከ ዐሥራ አንድ ዓመቷ ደግሞ የተወዳዳሪነት ስሜትን ወይም የበታችነት ስሜትን በማንነቷ ላይ የሚገነባበት ወቅት ነው። እዚህ ደረጃ ላይ መምህራን ወሳኝ ናቸው። ማምሻ የሞት ሞቷን እስከ ዘጠነኛ ክፍል ብትጓዝም ቀለም ግን ፈጽሞ ሊዘልቃት አልቻለም። በሠራችው ሥራ የበላይነት ስሜትን እንዳትጎናጸፍ ተደርጋ ይኾን? አብርሽ የተባለው ተራኪው ገጸባሕርይ ስለማምሻ ሥነ ልቦናዊ ጫና እንዲህ ይላል፡- “በፌዝ - ከእኩዮቿ ጋር እኩል የማትቆም - በልጅነቷ የማኅበረሰቡ ግፍ ከብዷት የጎበጠች ወጣት ተፈጠረች።” የተወዳዳሪነት ስሜቷን በየቀኑ ማኅበረሰቡ እየቸረቸፈባት እንዴት ቀና ያለች ሴት ትፈጠር?
ከ12 - 18 ዓመቷ ደግሞ ጥንቅቅቀ ያለ ማንነት የምትገነባበት አልያም ግራ መጋባት የሚሠለጥንባት ወቅት ሲኾኑ ራስን ለመቻል፣ ከጥገኘነት ለመላቀቅ በሚሞክሩት ሙከራ በሚሰጣቸው ምላሽ ላይ ይመሠረታል። ትምህርት አልሆን ሲላት ከድር የተባለው ጫታም ደላላ ጋር ሄዳ፣ ሻይ ቤት እንዲስያስቀጥራት ስትነግረው፣ “ማምሻ … በዚህ ፊት አስተናጋጅነት…” ብሎ ተዘባበተባት። ቆየት ብላ የቦኖ ውኃ ቀጂነት ሥራ አገኘች። ግን እምብዛም አልቆየች። “ውኃ አታፍስሱ!” ብትላቸው እያሸሞሩባት ቁጡ አደረጓት። አንድ ቀን አንዷ ላይ ተከምራባት እልኋን ተወጣችባትና ከሥራ ተባረረች። ቤቷ ተከተተች። ጥንቅቅ ያለ ማንነት በሚገነባበት ዘመኗ የግራ መጋባት አስኬማ ደፍታ መነነች።
እስኪ ደግሞ ለንጽጽር ሎዛ ጋር እንሂድ። ሎዛ በአባቷ ምክንያት የተወዳዳሪነት ስሜቷ ላቅ ያለ ስለኾነ ባለጽኑ ማንነት ሆና እናገኛታለን። በዐሥራ-ቤቴ ዘመኗ ዩኒቨርስቲ ስትገባ የተፈጠረው ክስተት ለዚህ ትልቅ አስረጅ ነው። “እብደትን አትማሪያትም!” በሚል ንግግር እናቷን ጨምሮ ከሁሉም ሰው ዘንድ ተቃውሞ ገጠማት። “ሁሉም ተቃውመውኝ እኔ ብቻ ልክ ልኾን አልችልም” የሚል ግራ መጋባት ውስጥ ሳትገባ በጽኑ አቋም የመረጠችውን የፍልስፍና ትምህርት እንደተማረች ከታሪኩ ውስጥ እናገኛለን። የአባቷ ምላሽም እሷን የሚደግፍ ስለኾነ ከመደናበር (Role Confusion) ተሻግራ ወደ ሌላኛው እርከን ትሄዳለች። ወደ መወዳጀት መቻል። በአንጻሩ ግን ማምሻ ለዚህ አልታደለችም። ሎዛ በአባቷ ዘንድ ያላት ቅቡልነት ማምሻን ታህል በማኅበረሰቡ የተገፋችን ሴት ወደ መቀበል አሳደጋት። ግፋ ሲልም ሚዜዋ እስከማድረግ። ከዳግም ጋር ደግሞ ትዳር እስከ መመሥረት።
ከ19 -40 ባለው ዕድሜ ውስጥ የመቀራረብ ስሜት ወይም ራስን የመነጠል ስሜት የሚደረጅበት ነው። ከቅርብ ዘመድ ውጭ ከኾነ ሰዎች ጋር በሚደረግ ዘለቄታ ያለው መስተጋብር ውስጥ በሚኖረው የመሳካት ዕድል የሚወሰን ነገር ነው። ማምሻ የመቀራረብ ስሜት ለመገንባት ዕድሉን አላገኘችም። ከሁሉ ወጥታ፣ ራሷን ነጥላ ቤቷ ተከተተች። ወላጅ እናቷ የሰው ቤት ሠርታ በምታመጣው ፍራንክ የሰቀቀን ኑሮውን ተያያዘችው። ነገር ግን ባቀረቀረችበት ኪሮሽና ክር አንስታ ውብ ዳንቴሎችን፣ አልጋ ልብሶችን፣ የመጋረጃዎችን ጥልፍ ማምረት ጀመረች። ማኅበረሰቡ የማምሻን የእጅ ሥራ ውጤቶች ይሸምት ጀመር። የማምሻን አስቀያሚነት ውብ የእጅ ሥራዋ የዋጠው መሰለ። እናቷን በየሰው ቤት ከመንከራተት አዳነች። ነገር ግን ብዙም ሳይቆይ ዘመናዊ የጥልፍ መኪናዎች መጡና የማምሻን እጅ ሰበሩ። ዳግም ወደ ማቀርቀሩ ተመለሰች። እናቷም ወደ ቀደመ ሥራዋ ተመለሰች። ማምሻ በቀቢጸ ተስፋ ዛጎል ተከተተች። እንግዲህ ሎዛ ከዚህ ሁሉ አሉታዊ የማኅበራዊ ልቦናዊ ማጥ ውስጥ ነው ማምሻን መንጭቃ እንድትወጣ የረዳቻት።
በዚህ ታሪክ ውስጥ የኤሪክሰንን ሰባተኛ እና ስምንተኛ ደረጃ እርከኖችን ለማተት ስለሚቸግር በዚህ እናበቃለን።
የዳሰሳው አቅራቢ - © ቢኒያም አቡራ is an associate editor at © Think Ethiopia (biniyamforsido@gmail.com)
ጥር 13፣ 2017 ዓ.ም
ከስድስት እስከ ዐሥራ አንድ ዓመቷ ደግሞ የተወዳዳሪነት ስሜትን ወይም የበታችነት ስሜትን በማንነቷ ላይ የሚገነባበት ወቅት ነው። እዚህ ደረጃ ላይ መምህራን ወሳኝ ናቸው። ማምሻ የሞት ሞቷን እስከ ዘጠነኛ ክፍል ብትጓዝም ቀለም ግን ፈጽሞ ሊዘልቃት አልቻለም። በሠራችው ሥራ የበላይነት ስሜትን እንዳትጎናጸፍ ተደርጋ ይኾን? አብርሽ የተባለው ተራኪው ገጸባሕርይ ስለማምሻ ሥነ ልቦናዊ ጫና እንዲህ ይላል፡- “በፌዝ - ከእኩዮቿ ጋር እኩል የማትቆም - በልጅነቷ የማኅበረሰቡ ግፍ ከብዷት የጎበጠች ወጣት ተፈጠረች።” የተወዳዳሪነት ስሜቷን በየቀኑ ማኅበረሰቡ እየቸረቸፈባት እንዴት ቀና ያለች ሴት ትፈጠር?
ከ12 - 18 ዓመቷ ደግሞ ጥንቅቅቀ ያለ ማንነት የምትገነባበት አልያም ግራ መጋባት የሚሠለጥንባት ወቅት ሲኾኑ ራስን ለመቻል፣ ከጥገኘነት ለመላቀቅ በሚሞክሩት ሙከራ በሚሰጣቸው ምላሽ ላይ ይመሠረታል። ትምህርት አልሆን ሲላት ከድር የተባለው ጫታም ደላላ ጋር ሄዳ፣ ሻይ ቤት እንዲስያስቀጥራት ስትነግረው፣ “ማምሻ … በዚህ ፊት አስተናጋጅነት…” ብሎ ተዘባበተባት። ቆየት ብላ የቦኖ ውኃ ቀጂነት ሥራ አገኘች። ግን እምብዛም አልቆየች። “ውኃ አታፍስሱ!” ብትላቸው እያሸሞሩባት ቁጡ አደረጓት። አንድ ቀን አንዷ ላይ ተከምራባት እልኋን ተወጣችባትና ከሥራ ተባረረች። ቤቷ ተከተተች። ጥንቅቅ ያለ ማንነት በሚገነባበት ዘመኗ የግራ መጋባት አስኬማ ደፍታ መነነች።
እስኪ ደግሞ ለንጽጽር ሎዛ ጋር እንሂድ። ሎዛ በአባቷ ምክንያት የተወዳዳሪነት ስሜቷ ላቅ ያለ ስለኾነ ባለጽኑ ማንነት ሆና እናገኛታለን። በዐሥራ-ቤቴ ዘመኗ ዩኒቨርስቲ ስትገባ የተፈጠረው ክስተት ለዚህ ትልቅ አስረጅ ነው። “እብደትን አትማሪያትም!” በሚል ንግግር እናቷን ጨምሮ ከሁሉም ሰው ዘንድ ተቃውሞ ገጠማት። “ሁሉም ተቃውመውኝ እኔ ብቻ ልክ ልኾን አልችልም” የሚል ግራ መጋባት ውስጥ ሳትገባ በጽኑ አቋም የመረጠችውን የፍልስፍና ትምህርት እንደተማረች ከታሪኩ ውስጥ እናገኛለን። የአባቷ ምላሽም እሷን የሚደግፍ ስለኾነ ከመደናበር (Role Confusion) ተሻግራ ወደ ሌላኛው እርከን ትሄዳለች። ወደ መወዳጀት መቻል። በአንጻሩ ግን ማምሻ ለዚህ አልታደለችም። ሎዛ በአባቷ ዘንድ ያላት ቅቡልነት ማምሻን ታህል በማኅበረሰቡ የተገፋችን ሴት ወደ መቀበል አሳደጋት። ግፋ ሲልም ሚዜዋ እስከማድረግ። ከዳግም ጋር ደግሞ ትዳር እስከ መመሥረት።
ከ19 -40 ባለው ዕድሜ ውስጥ የመቀራረብ ስሜት ወይም ራስን የመነጠል ስሜት የሚደረጅበት ነው። ከቅርብ ዘመድ ውጭ ከኾነ ሰዎች ጋር በሚደረግ ዘለቄታ ያለው መስተጋብር ውስጥ በሚኖረው የመሳካት ዕድል የሚወሰን ነገር ነው። ማምሻ የመቀራረብ ስሜት ለመገንባት ዕድሉን አላገኘችም። ከሁሉ ወጥታ፣ ራሷን ነጥላ ቤቷ ተከተተች። ወላጅ እናቷ የሰው ቤት ሠርታ በምታመጣው ፍራንክ የሰቀቀን ኑሮውን ተያያዘችው። ነገር ግን ባቀረቀረችበት ኪሮሽና ክር አንስታ ውብ ዳንቴሎችን፣ አልጋ ልብሶችን፣ የመጋረጃዎችን ጥልፍ ማምረት ጀመረች። ማኅበረሰቡ የማምሻን የእጅ ሥራ ውጤቶች ይሸምት ጀመር። የማምሻን አስቀያሚነት ውብ የእጅ ሥራዋ የዋጠው መሰለ። እናቷን በየሰው ቤት ከመንከራተት አዳነች። ነገር ግን ብዙም ሳይቆይ ዘመናዊ የጥልፍ መኪናዎች መጡና የማምሻን እጅ ሰበሩ። ዳግም ወደ ማቀርቀሩ ተመለሰች። እናቷም ወደ ቀደመ ሥራዋ ተመለሰች። ማምሻ በቀቢጸ ተስፋ ዛጎል ተከተተች። እንግዲህ ሎዛ ከዚህ ሁሉ አሉታዊ የማኅበራዊ ልቦናዊ ማጥ ውስጥ ነው ማምሻን መንጭቃ እንድትወጣ የረዳቻት።
በዚህ ታሪክ ውስጥ የኤሪክሰንን ሰባተኛ እና ስምንተኛ ደረጃ እርከኖችን ለማተት ስለሚቸግር በዚህ እናበቃለን።
የዳሰሳው አቅራቢ - © ቢኒያም አቡራ is an associate editor at © Think Ethiopia (biniyamforsido@gmail.com)
ጥር 13፣ 2017 ዓ.ም