ከ 48 ዓመት በፊት ጥር 26 ቀን 1969 ዓ.ም የኢህአፓ ደጋፊዎች ተብለው የተፈረጀባቸው የኢትዮጵያ ርዕሰ ብሔር የነበሩት ጀነራል ተፈሪ በንቲ እና ሌሎች 6 ግለሰቦች ላይ በደርግ ዘመቻና ጥበቃ ኃላፊ በሌ/ኮሎኔል ዳንኤል አስፋው አማካኝነት ድምፅ ማፈኚያ (Silencer) በተገጠመለት መሳሪያ ሽጉጥ የተገደሉበት ዕለት ነበር።
⩩ በወቅቱ በሰባቱ ግለሰቦች ላይ የተወሰደው እርምጃ በብሔራዊ ራዲዮና የተላለፈው እና በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ የወጣው ፅሁፍ
"....በመለዮ ለባሹ መሀከል መከፋፈል በመለዮ ለባሹና በሰፊው ሕዝብ መካ ልከ መቃቃርን እያስፋፉ በሔዱት በኢሕአፓና በኢዲዩ የውስጥ አርበኞች ላይ አብዮቱ ከመጠቃት ወደ አጥቂነት በመሸጋገር ዛሬ የማያዳግም አብዮታዊ ርምጃ ወስዶባቸዋል።
በዚህም መሠረት በጊዜያዊ ወታ ደራዊ አስተዳደር ደርግ ውስጥ ለኢ አፓና ለኢዲዩ በውስጥ አርበኝነት ብዮቱን ለመቀልበስ ተራማጅ የደርግ አባላትንና የሕዝብ ድርጅት ጉዳይ ጊዜያዊ ጽ/ቤት ታጋዮችን ለማፈን ሲያሴሩ እጅ ከፍንጅ በተ ያዙት በሚከተሉት የውስጥ አርበበኞች ላይ በትናንቱ ዕለት አብዮታዊ ርምጃ ተወስዶባቸዋል። እነርሱም:-
፩. ብ/ጀነራል ተፈሪ በንቲ :- የደርግ ሊቀምንበር
፪. ሌ/ኮ አስራት ደስታ :- የማስታወቂያ ጉዳይ ም/ኃላፊ
፫. ሌ/ኮሎኔል ህሩይ ኃ/ስላሴ :- የህዝብ ደህንነትና መረጃ ዘርፍ ሃላፊ)
፬. ሻምበል ሞገስ ወ/ሚካኤል :- የውጭ ጉዳይና የህዝ ብ ማደራጃ ዘርፍ ሃላፊ)
፭. ሻምበል አለማየሁ ሃይሌ :- የደርጉ ዋና ፀሃፊ
፮. ፲ አለቃ ሃይሉ በላይ :- የውጭ ጉዳይና የህዝብ ማደራጃ ዘርፍ ምክትል ሃላፊ)
፯. ሻምበል ተፈራ ደነቀ:- የደርግ አባል
*****
መጀመርያ አካባቢ ደርግ በህዝብ ዘንድ ተቀባይነትን ለማግኘት ህዝብ የሚያውቃቸውን ጄነራሎች በአመራርነት ይሾም ነበር። በዚህም መሰረት ጄነራል ተፈሪ በንቲ የደርጉ ሁለተኛ ዋና ሊቀመንበር ነበሩ (ከጄነራል አማን አንዶም በመቀጠል)። ምንም እንኳን በጊዜው የደርጉ ሊቀመንበር ጄነራል ተፈሪ በንቲ ቢሆኑም፤ እውነተኛ የስልጣን ባለቤት የነበሩት ግን ምክትል ሊቀመንበሩ ኮሎኔል መንግስቱ ሃይለማሪም ነበሩ።
የደርጉ ሁለተኛ ሰው የነበሩት ሻምበል ፍቅረስላሴ ወግደረስ እንደሚተርኩልን ከሆነ በደርግ የመጀመርያ ጊዜያቶች አካባቢ የኢህአፓ አባሎች በደርግ ውስጥ ሰርገው ገብተው ነበረ። ኢህአፓ እነዚህን አባላ ት በመጠቀም፣ ከደርግ ስልጣን ለምንጠቅ ካካሄዷቸው በርካታ እንቅስቃሴዎች መካከል በደርጉ ሊቀመንበር በኮሎኔል መንግስቱ ሃይለማሪያም ላይ የተቃጣው የግድያ ሙከራ አንዱ ነው። የግድያ ሙከራው ሳይሳካ በመቅረቱ ምንክያት ኢህአፓ ሌላ የስልጣን መጨበጫ መንገድ መፈለግ ነበረበት። ይህም መንገድ ደግሞ ደርግ ውስጥ ባሉት አባላት አማካኝነት ስልጣንን በሰላማዊ መንገድ መቀበል ነበር።
⩩ ከመስከረም ፲፱፻፷፱ ዓ.ም ጀምሮ በተካሄዱ ተከታታይስብሰባዎች አማካኝነት ኢህአፓ
አባሎቹን በመጠቀም የደርግን ስልጣን ሙሉ በሙሉ በሚባል መልኩ ለመቆጣጠር ችሎ ነበር... በመሆኑም ስ ልጣን ለመጀመርያ ጊዜ ከኮሎኔል መንግስቱ እጅ ወጥታ በጄነራል ተፈሪ ፤ በሻምበል ሞገስና በመቶ አለቃ አለማየሁ እጅ ዉስጥ የገባች መስላ ነበር። ኮሎኔል መንግ ስቱ ስልጣን ከጃቸው በመውጣቱ ምክንያት እና ስልጣን ላይ በነበሩበት ጊዜ ብዙ ጠላቶች አፍርተው ስለነበር ሁ ኔታዎችን በጊዜው ለሳቸው በሚመች መልኩ ካላስተካከሉ ለህልውናቸውም ጭምር አስጊ እንደሆነ አመኑ። በመሆኑም ኮሎኔል መንግስቱ ከእጃቸው የወጣችውን ስልጣን ለማስመለስ በጥር 26 ቀን 1969 ዓ.ም አንድ እርምጃ ወሰዱ።
⩩ ሻምበል ፍቅረስላሴ ወግደረስ ሁኔታውን በሚከተለው መልክ ገልፀውታል።
"... የቛሚ ኮሚቴ አባላት ግራና ቀኝ ቦታቸውን እንደያዙ ጄነራል ተፈሪ ኮሎኔል መንግስቱን አስከትለው በስተኋላ ባለው በር በኩል ገቡ፡፡ ሁላችንም ከመቀመጫችን ተነሳን፡፡ "እንደምን አደራቹ?" ብለው ሲቀመጡ እኛም ተቀመጥን።
በሊቀመንበርንት ስብሰባውን የሚመሩት ጄነራል ተፈሪ "የቛሚ ኮሚቴው በዛሬው ቀን የሚወያይበትን ጉዳይ አስ መልክቶ የመቶ አለቃ አለማየሁ የደርጉ ዋና ፀሃፊ ይገልፅልናል" ብለው ስብሰባው መጀመሩን ካበሰሩ በኋላ አለማየሁ ባጀንዳው ላይ ኣጭር ገለፃ ማድረግ ሲጀምር ስልክ ተደወለ። ስልኩ ኮሎኔል መንግስቱ አጠገብ ስለነበርወዲያው ቅጭል እንዳለ መነጋገሪያውን በማንሳት ሃሎ አሉ። ከሌላው ጫፍ ማን እንደደወለ አላወቅንም። በኋላ እንደታወቀው ሌ/ ኮሎኔል ዳንዔል ነበር የደወለው፡፡ ምን እንደተነጋገሩ አልተሰማንም። ኮሎኔል መንግስቱ ብቻ "እሺ እሺ" ብለው ስልኩን ዘጉት። "ይቅርታ ስልኩ የተደወለው ከጎንደር ነው፡፡ ጎንደር ውስጥ ችግር አለ። እናንተ ቀጥሉ'' ብለው ከጀርባቸው ባለው በር በኩል ውልቅ አሉ። በዚያን ጊዜ አለማየሁ እና ሞገስ ጥርጣሬ የገባቸው መ ሰሉ።
አለማየሁ ንግግሩን አቛርቶ በመስኮት ውጭ ውጭውን መመልከት ጀመረ፡፡ አይኖቹ አላርፍ አሉ። ግራና ቀኝ ይመ ለከታል። አጠገቡ ያሉትን ሰዎች ሁሉ በጥርጣሬ ተመለከተ። ሻምበል ሞገስም በር በሩን ይመለከታል። ከአሁን አሁን አንድ ችግር ይከሰታል የሚል ፍርሃት ያደረበት ይመስላል። ሁሉም የኢህአፓ አባላት እና ደጋፊዎች ፈርተዋል። እንደፈሩት አልቀረም ኮሎኔል መንግስቱ ከወጡ ሁለት ደቂቃ እንኳን አልሞላም ከበስተጀርባ ባለው ኮሪደር የወታደሮች እርምጃ ሰማን። ወታደሮቹ ሲንቀሳቀሱ በፊት ለፊታችን ባሉት ምስኮቶች በኩል ተመለከትን። በዚህን ጊዜ ፍ ስሃ ደስታ "ተከበናል" አለ። ወዲያው ሁለቱም በሮች በሃይል ተበረገዱ። ሁላችንም ደነገጥን ፤ ቀልባችን ተገፈፈ። ድርቅ ብለን በተቀመጥንበት ቀረን።
በአስፈሪ ሁኔታ ጠመንጃቸውን ወድረው በርካታ ወታደሮች ወደ ውስጥ በመግባት ዙሪያችንን ከበቡን። አንድም ሰው አልተንቀሳቀሰም። ሻምበል ገብሩ ተሰማ የኦፐሬሽኑ ሃላፊ ወደ ውስጥ ገባ ብሎ "ወንድሞቼ አትደንግጡ ምንም አትሆኑም! የሚፈለጉት ጥቂት ሰዎች ብቻ ናቸው ስለዚህ ምንም ችግር ሳትፈጥሩ ጥትቃቹን እያስረከባቹ አንድ ባንድ እንድትወጡልን ብቻ ነው የምንፈልገው" አለ።
ወታደሮቹ ሰገቡ ጄነራል ተፈሪ ከመቀመጫቸው ተነስተው በጀርባቸው ባለው በር በኩል ለመውጣት ፊታቸውን ወደዚያ ሲያዞሩ ወታደሮቹ ጠመንጃ ደገኑባቸው፡፡ እንደገና በፊት ለፊታቸው ባለው በር በኩል ለመውጣት ሲሞክሩ ወታደሮቹ ጠመንጃ ወድረው ካዳራሹ ኣስወጧቸው፡፡ የቀረነው ታጋቾች ሻምበል ገብሩ በሰጠን ትዛዝ መሰረት ከ ተቀመጥንበት ተነስተን ቆምን። ከሌ/ ኮሎኔል ተስፋዬ ገ/ኪዳን በስተቀር ሁላችንም ሳናንገራግር ሸጉጣችንን እየመዘዝን አስረከብን።
... ማን ወዴት መሄድ እንዳለበት ለወታደሮቹ በተሰጠው መመርያ መሰረት ከፊሎቹ ወደ ግራ የቀሩት ደግሞ ወደ ቀኝ እንዲያመሩ ወታደሮቹ ተቆሟቸው፡፡ ወደ ግራ እንዲሄ ዱ የተደረጉት የነአለማየሁ ቡድን ሲሆን ወደ ቀኝ ደግሞ እንዲሄዱ የተደረጉት ደግሞ የኮሎኔል መንግስቱ ደጋፊዎ ች የተባሉና አቆማቸውን በግልፅ ያላሳዩ ናቸው፡፡ የነ አለማየሁ ቡድን አባላት ጠመንጃ ተወድሮባቸው ለማረፊያ ወደ ተመደበላቸው ቦታ ተወሰዱ። ይህ ቦታ ከኮሎኔል መንግስቱ ቢሮ ስር የሚገኝ የመኪና ጋራዥ ነው። ይህ ቦታ ቀድሞ የ ንጉሱ መኪና ማቆሚያ ቦታ ስለነበር መዝጊያ አለው፡፡ የዚህ ቡድን አባላት በሙሉ በዚህ ጋራዥ ውስጥ ተቆለፈባቸው። ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ቀንደኛ የኢህአፓ ደጋፊዎችና የኮሎኔል መንግስቱ ባላጋራዎች ናቸው የተባሉት ሰባቱ የደርግ አባላት ብቻ በጋራዡ ውስጥ መገኘታቸው እንደተረጋገጠ ድምፅ የሚያፍን
⩩ በወቅቱ በሰባቱ ግለሰቦች ላይ የተወሰደው እርምጃ በብሔራዊ ራዲዮና የተላለፈው እና በአዲስ ዘመን ጋዜጣ ታትሞ የወጣው ፅሁፍ
"....በመለዮ ለባሹ መሀከል መከፋፈል በመለዮ ለባሹና በሰፊው ሕዝብ መካ ልከ መቃቃርን እያስፋፉ በሔዱት በኢሕአፓና በኢዲዩ የውስጥ አርበኞች ላይ አብዮቱ ከመጠቃት ወደ አጥቂነት በመሸጋገር ዛሬ የማያዳግም አብዮታዊ ርምጃ ወስዶባቸዋል።
በዚህም መሠረት በጊዜያዊ ወታ ደራዊ አስተዳደር ደርግ ውስጥ ለኢ አፓና ለኢዲዩ በውስጥ አርበኝነት ብዮቱን ለመቀልበስ ተራማጅ የደርግ አባላትንና የሕዝብ ድርጅት ጉዳይ ጊዜያዊ ጽ/ቤት ታጋዮችን ለማፈን ሲያሴሩ እጅ ከፍንጅ በተ ያዙት በሚከተሉት የውስጥ አርበበኞች ላይ በትናንቱ ዕለት አብዮታዊ ርምጃ ተወስዶባቸዋል። እነርሱም:-
፩. ብ/ጀነራል ተፈሪ በንቲ :- የደርግ ሊቀምንበር
፪. ሌ/ኮ አስራት ደስታ :- የማስታወቂያ ጉዳይ ም/ኃላፊ
፫. ሌ/ኮሎኔል ህሩይ ኃ/ስላሴ :- የህዝብ ደህንነትና መረጃ ዘርፍ ሃላፊ)
፬. ሻምበል ሞገስ ወ/ሚካኤል :- የውጭ ጉዳይና የህዝ ብ ማደራጃ ዘርፍ ሃላፊ)
፭. ሻምበል አለማየሁ ሃይሌ :- የደርጉ ዋና ፀሃፊ
፮. ፲ አለቃ ሃይሉ በላይ :- የውጭ ጉዳይና የህዝብ ማደራጃ ዘርፍ ምክትል ሃላፊ)
፯. ሻምበል ተፈራ ደነቀ:- የደርግ አባል
*****
መጀመርያ አካባቢ ደርግ በህዝብ ዘንድ ተቀባይነትን ለማግኘት ህዝብ የሚያውቃቸውን ጄነራሎች በአመራርነት ይሾም ነበር። በዚህም መሰረት ጄነራል ተፈሪ በንቲ የደርጉ ሁለተኛ ዋና ሊቀመንበር ነበሩ (ከጄነራል አማን አንዶም በመቀጠል)። ምንም እንኳን በጊዜው የደርጉ ሊቀመንበር ጄነራል ተፈሪ በንቲ ቢሆኑም፤ እውነተኛ የስልጣን ባለቤት የነበሩት ግን ምክትል ሊቀመንበሩ ኮሎኔል መንግስቱ ሃይለማሪም ነበሩ።
የደርጉ ሁለተኛ ሰው የነበሩት ሻምበል ፍቅረስላሴ ወግደረስ እንደሚተርኩልን ከሆነ በደርግ የመጀመርያ ጊዜያቶች አካባቢ የኢህአፓ አባሎች በደርግ ውስጥ ሰርገው ገብተው ነበረ። ኢህአፓ እነዚህን አባላ ት በመጠቀም፣ ከደርግ ስልጣን ለምንጠቅ ካካሄዷቸው በርካታ እንቅስቃሴዎች መካከል በደርጉ ሊቀመንበር በኮሎኔል መንግስቱ ሃይለማሪያም ላይ የተቃጣው የግድያ ሙከራ አንዱ ነው። የግድያ ሙከራው ሳይሳካ በመቅረቱ ምንክያት ኢህአፓ ሌላ የስልጣን መጨበጫ መንገድ መፈለግ ነበረበት። ይህም መንገድ ደግሞ ደርግ ውስጥ ባሉት አባላት አማካኝነት ስልጣንን በሰላማዊ መንገድ መቀበል ነበር።
⩩ ከመስከረም ፲፱፻፷፱ ዓ.ም ጀምሮ በተካሄዱ ተከታታይስብሰባዎች አማካኝነት ኢህአፓ
አባሎቹን በመጠቀም የደርግን ስልጣን ሙሉ በሙሉ በሚባል መልኩ ለመቆጣጠር ችሎ ነበር... በመሆኑም ስ ልጣን ለመጀመርያ ጊዜ ከኮሎኔል መንግስቱ እጅ ወጥታ በጄነራል ተፈሪ ፤ በሻምበል ሞገስና በመቶ አለቃ አለማየሁ እጅ ዉስጥ የገባች መስላ ነበር። ኮሎኔል መንግ ስቱ ስልጣን ከጃቸው በመውጣቱ ምክንያት እና ስልጣን ላይ በነበሩበት ጊዜ ብዙ ጠላቶች አፍርተው ስለነበር ሁ ኔታዎችን በጊዜው ለሳቸው በሚመች መልኩ ካላስተካከሉ ለህልውናቸውም ጭምር አስጊ እንደሆነ አመኑ። በመሆኑም ኮሎኔል መንግስቱ ከእጃቸው የወጣችውን ስልጣን ለማስመለስ በጥር 26 ቀን 1969 ዓ.ም አንድ እርምጃ ወሰዱ።
⩩ ሻምበል ፍቅረስላሴ ወግደረስ ሁኔታውን በሚከተለው መልክ ገልፀውታል።
"... የቛሚ ኮሚቴ አባላት ግራና ቀኝ ቦታቸውን እንደያዙ ጄነራል ተፈሪ ኮሎኔል መንግስቱን አስከትለው በስተኋላ ባለው በር በኩል ገቡ፡፡ ሁላችንም ከመቀመጫችን ተነሳን፡፡ "እንደምን አደራቹ?" ብለው ሲቀመጡ እኛም ተቀመጥን።
በሊቀመንበርንት ስብሰባውን የሚመሩት ጄነራል ተፈሪ "የቛሚ ኮሚቴው በዛሬው ቀን የሚወያይበትን ጉዳይ አስ መልክቶ የመቶ አለቃ አለማየሁ የደርጉ ዋና ፀሃፊ ይገልፅልናል" ብለው ስብሰባው መጀመሩን ካበሰሩ በኋላ አለማየሁ ባጀንዳው ላይ ኣጭር ገለፃ ማድረግ ሲጀምር ስልክ ተደወለ። ስልኩ ኮሎኔል መንግስቱ አጠገብ ስለነበርወዲያው ቅጭል እንዳለ መነጋገሪያውን በማንሳት ሃሎ አሉ። ከሌላው ጫፍ ማን እንደደወለ አላወቅንም። በኋላ እንደታወቀው ሌ/ ኮሎኔል ዳንዔል ነበር የደወለው፡፡ ምን እንደተነጋገሩ አልተሰማንም። ኮሎኔል መንግስቱ ብቻ "እሺ እሺ" ብለው ስልኩን ዘጉት። "ይቅርታ ስልኩ የተደወለው ከጎንደር ነው፡፡ ጎንደር ውስጥ ችግር አለ። እናንተ ቀጥሉ'' ብለው ከጀርባቸው ባለው በር በኩል ውልቅ አሉ። በዚያን ጊዜ አለማየሁ እና ሞገስ ጥርጣሬ የገባቸው መ ሰሉ።
አለማየሁ ንግግሩን አቛርቶ በመስኮት ውጭ ውጭውን መመልከት ጀመረ፡፡ አይኖቹ አላርፍ አሉ። ግራና ቀኝ ይመ ለከታል። አጠገቡ ያሉትን ሰዎች ሁሉ በጥርጣሬ ተመለከተ። ሻምበል ሞገስም በር በሩን ይመለከታል። ከአሁን አሁን አንድ ችግር ይከሰታል የሚል ፍርሃት ያደረበት ይመስላል። ሁሉም የኢህአፓ አባላት እና ደጋፊዎች ፈርተዋል። እንደፈሩት አልቀረም ኮሎኔል መንግስቱ ከወጡ ሁለት ደቂቃ እንኳን አልሞላም ከበስተጀርባ ባለው ኮሪደር የወታደሮች እርምጃ ሰማን። ወታደሮቹ ሲንቀሳቀሱ በፊት ለፊታችን ባሉት ምስኮቶች በኩል ተመለከትን። በዚህን ጊዜ ፍ ስሃ ደስታ "ተከበናል" አለ። ወዲያው ሁለቱም በሮች በሃይል ተበረገዱ። ሁላችንም ደነገጥን ፤ ቀልባችን ተገፈፈ። ድርቅ ብለን በተቀመጥንበት ቀረን።
በአስፈሪ ሁኔታ ጠመንጃቸውን ወድረው በርካታ ወታደሮች ወደ ውስጥ በመግባት ዙሪያችንን ከበቡን። አንድም ሰው አልተንቀሳቀሰም። ሻምበል ገብሩ ተሰማ የኦፐሬሽኑ ሃላፊ ወደ ውስጥ ገባ ብሎ "ወንድሞቼ አትደንግጡ ምንም አትሆኑም! የሚፈለጉት ጥቂት ሰዎች ብቻ ናቸው ስለዚህ ምንም ችግር ሳትፈጥሩ ጥትቃቹን እያስረከባቹ አንድ ባንድ እንድትወጡልን ብቻ ነው የምንፈልገው" አለ።
ወታደሮቹ ሰገቡ ጄነራል ተፈሪ ከመቀመጫቸው ተነስተው በጀርባቸው ባለው በር በኩል ለመውጣት ፊታቸውን ወደዚያ ሲያዞሩ ወታደሮቹ ጠመንጃ ደገኑባቸው፡፡ እንደገና በፊት ለፊታቸው ባለው በር በኩል ለመውጣት ሲሞክሩ ወታደሮቹ ጠመንጃ ወድረው ካዳራሹ ኣስወጧቸው፡፡ የቀረነው ታጋቾች ሻምበል ገብሩ በሰጠን ትዛዝ መሰረት ከ ተቀመጥንበት ተነስተን ቆምን። ከሌ/ ኮሎኔል ተስፋዬ ገ/ኪዳን በስተቀር ሁላችንም ሳናንገራግር ሸጉጣችንን እየመዘዝን አስረከብን።
... ማን ወዴት መሄድ እንዳለበት ለወታደሮቹ በተሰጠው መመርያ መሰረት ከፊሎቹ ወደ ግራ የቀሩት ደግሞ ወደ ቀኝ እንዲያመሩ ወታደሮቹ ተቆሟቸው፡፡ ወደ ግራ እንዲሄ ዱ የተደረጉት የነአለማየሁ ቡድን ሲሆን ወደ ቀኝ ደግሞ እንዲሄዱ የተደረጉት ደግሞ የኮሎኔል መንግስቱ ደጋፊዎ ች የተባሉና አቆማቸውን በግልፅ ያላሳዩ ናቸው፡፡ የነ አለማየሁ ቡድን አባላት ጠመንጃ ተወድሮባቸው ለማረፊያ ወደ ተመደበላቸው ቦታ ተወሰዱ። ይህ ቦታ ከኮሎኔል መንግስቱ ቢሮ ስር የሚገኝ የመኪና ጋራዥ ነው። ይህ ቦታ ቀድሞ የ ንጉሱ መኪና ማቆሚያ ቦታ ስለነበር መዝጊያ አለው፡፡ የዚህ ቡድን አባላት በሙሉ በዚህ ጋራዥ ውስጥ ተቆለፈባቸው። ከጥቂት ደቂቃዎች በኋላ ቀንደኛ የኢህአፓ ደጋፊዎችና የኮሎኔል መንግስቱ ባላጋራዎች ናቸው የተባሉት ሰባቱ የደርግ አባላት ብቻ በጋራዡ ውስጥ መገኘታቸው እንደተረጋገጠ ድምፅ የሚያፍን