1. የአርሞንዔም ተራራ
ይህ ተራራ የእስራኤል ሰሜናዊ ወሰን ክልል ነው። እርሱም ክርስቶስ ወደ ብሩህነት የተለወጠበት ተራራ ይሆናል ።
2. የሊባኖስ ተራራ
በዚህ ተራራ ላይ ታላቅ የጥድ ዛፍ ደን ነበር። በኢየሩሳሌም ውስጥ ለተሠራው ለቤተ መቅደሱ የሚሆን እንጨት የተወሰደው ከዚሁ ተራራ ነው ።
3.የዔባል ተራራ
ሙሴ እስራኤላውያንን ወደ ከነዓን አገር ከመግባታቸው በፊት በዚሁ ተራራ ላይ እንደደረሱ የእግዚአብሔርን መሠውያ እንዲሠሩና ቃላተ ኦሪቱን በድንጋዮች ላይ እንዲጽፉ አዘዛኛው።
4. ደብረ ዘይት
ይህ ተራራ የሚገኘው በኢየሩሳሌም አጠገብ ነው። ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተያዘው በዚሁ ተራራ ላይ ነበር ።
5. የገልዓድ ተራራ
ያዕቆብና ላባን የሰላም ኪዳን የተስማሙትና ለኪዳኑም ምልክት የድንጋይ ካብ ያቆሙት እዚሁ ተራራ ላይ ነበር።
6. ደብረ ታቦር
ሢሣራን ያሸነፈው የባርቅ ጦር ሠራዊት የተሰበሰበው እዚህ ተራራ ላይ ነበር።
7. የቀርሜሎስ ተራራ
ኤልያስ ያቀረበውን መሥዋዕት እንዲበላለት ከሰማይ እሳት ያወረደውና የበዓልን ነቢያት ከንቱ መሆናቸውን ያሳፈራቸው እዚህ ተራራ ላይ ነበር ።
8. የጊልቦዓ ተራራ
የፍልስጥኤም ሰዎች የእስራኤልን ሰዎች ድል ያደረጉበትና ሳኦልና ዮናታን የተገደሉበት ቦታ እዚህ ነበር።
JOIN
➢
@ChristianDocምንጭ -
https://t.me/awdesibket ❣️