"ሁሌ ባገኝህ አይሰለቸኝም" አለችው
"እውነትሽ ነው"
"አዎ ገና መተዋወቃችን ቢሆንም ደጋግሜ ላገኝህ እፈልጋለሁ"
ዝም ተባባሉ ረጅም ሰዓት።
"እኔ ምልህ ህይወት ላንተ ምንድነው አለችው?"
"ቀይሮ መድገም ነው" አላት
"ማለት"
"አሁን የሆነች ተራ ካፌ ቡና ትጠጪያለሽ ሲኖርሽ ሸራተን ነው ራሱን ቡና
አሁን አንድ ክፍል ቤትሽ ውሰጥ ትተኛለሽ
ሲኖርሽ አስር ክፍል ያለው ግን አንዱ ክፍል ብቻ ራሱን እንቅልፍ ትተኛለሽ
ደሀ ሆነሽ አረቄ ነው
ሀብታም ስትሆኚ ውስኪ ነው ቀይሮ መድገም
ሰው ለምን ይመስለሻል አንድ ደብር ደጋግሞ ከመሳለም ደብር የሚቀያይረው ቦታ ቀይሮ ጸሎት ለመድገም ነው።
በፊት የሆነ ልጅ ትወጃለሽ ስትለያይ
ልጅ የሆነ ትወጃለሽ
ያንኑ መውደድ ቀይሮ ነው መድገም ነው
የሆነ ዘፈን በሌላ ዘፈን ዘፋኝ ቀይሮ መድገም
የምታውቂውን ስብከት በሌላ ሰባኪ ወይም ቄስ ቀይሮ መድገም
በኢኮኖሚ ክላስ መሄድ ዝነኛ ስትሆኚ እዛው ፕሌን ውስጥ ቢዝነስ ክላስ ሆኖ ወንበር ቀይሮ በረራ መድገም
ሰው ሁሉ ገንዘብ የሚፈልገው የነበረውን ነገር ቀይሮ ለመድገም ነው።"
የሆነ ነገሯ ተዛባባት።
"በቃ የዘመኑን ከቨር ሙዚቃ ታውቂያለሽ?"
"አዎ" አለችው
"የኛ ሰው ህይወት እንደዛ ነው
የህይወት ከቨር በይው።
የሆነ የሆነ ነገር ቀንጭጮቦ መምጣት ቀጣጥሎ ማዜም
ቀያይሮ መድገም..."
"የሚቀጥለው አመት እደውልልሀለሁ" አለችው
(ኤልያስ ሽታሁን)
"እውነትሽ ነው"
"አዎ ገና መተዋወቃችን ቢሆንም ደጋግሜ ላገኝህ እፈልጋለሁ"
ዝም ተባባሉ ረጅም ሰዓት።
"እኔ ምልህ ህይወት ላንተ ምንድነው አለችው?"
"ቀይሮ መድገም ነው" አላት
"ማለት"
"አሁን የሆነች ተራ ካፌ ቡና ትጠጪያለሽ ሲኖርሽ ሸራተን ነው ራሱን ቡና
አሁን አንድ ክፍል ቤትሽ ውሰጥ ትተኛለሽ
ሲኖርሽ አስር ክፍል ያለው ግን አንዱ ክፍል ብቻ ራሱን እንቅልፍ ትተኛለሽ
ደሀ ሆነሽ አረቄ ነው
ሀብታም ስትሆኚ ውስኪ ነው ቀይሮ መድገም
ሰው ለምን ይመስለሻል አንድ ደብር ደጋግሞ ከመሳለም ደብር የሚቀያይረው ቦታ ቀይሮ ጸሎት ለመድገም ነው።
በፊት የሆነ ልጅ ትወጃለሽ ስትለያይ
ልጅ የሆነ ትወጃለሽ
ያንኑ መውደድ ቀይሮ ነው መድገም ነው
የሆነ ዘፈን በሌላ ዘፈን ዘፋኝ ቀይሮ መድገም
የምታውቂውን ስብከት በሌላ ሰባኪ ወይም ቄስ ቀይሮ መድገም
በኢኮኖሚ ክላስ መሄድ ዝነኛ ስትሆኚ እዛው ፕሌን ውስጥ ቢዝነስ ክላስ ሆኖ ወንበር ቀይሮ በረራ መድገም
ሰው ሁሉ ገንዘብ የሚፈልገው የነበረውን ነገር ቀይሮ ለመድገም ነው።"
የሆነ ነገሯ ተዛባባት።
"በቃ የዘመኑን ከቨር ሙዚቃ ታውቂያለሽ?"
"አዎ" አለችው
"የኛ ሰው ህይወት እንደዛ ነው
የህይወት ከቨር በይው።
የሆነ የሆነ ነገር ቀንጭጮቦ መምጣት ቀጣጥሎ ማዜም
ቀያይሮ መድገም..."
"የሚቀጥለው አመት እደውልልሀለሁ" አለችው
(ኤልያስ ሽታሁን)