👆👆👆👆👆👆
ከባለፈው የቀጠለ
✅#_የነብያት_ታሪክ✅
🌲#_ነብዩሏህ_ዳውድ_ዐለይሂ_ሰላም🌲
ክፍል 4⃣6⃣
...በዚህ መሀል ነበር የዚህ ታሪክ ባለቤት እና የበጎች እረኛ የሆነው ዳዉድ ኢብን
ኢሻ ኢብን ዑወይድ ኢብን ዓቢር ኢብን ሰልሙን ኢብን ናህሹን ኢብን
ዑወይናዚብ ኢብን ኢረም ኢብን ሀስሩን ኢብን ፋሪስ ኢብን የሁዳ ኢብን
ያዕቁብ ኢብን ኢስሀቅ ኢብም ኢብራሂም......ሰልፉን እየሰነጠቀ ወደ ጃሉት
ወጣ።ይሁን እንጂ ንግስናንም ሆነ የጣሉትን ልጅ ማግባት ፈልጎ አይደለም።
እስራኢላውያንም ይሄ ደካማ እረኛ ምንም አይነት ጦርም ይሁን ጋሻ ሳይዝ ያን
ተራራ ሚያህል ሰውዬ ሊገጥም ሲወጣ በግርምት ይመለከቱት ነበር።
ዳዉድ እረኞች የሚይዙትን በትር በአንድ እጁ ይዞ በሌላው እጆ ድንጋይ
ይዟል።ጃሉት ለፍልሚያ የቆመበትን ቦታ ዳዉድ ልክ እንደደረሰ ፊት ለፊቱ ቆመ።
ጃሉት ይህን ልጅ እግር እረኛ ሲመለከት እያሾፈ፦"አንተ ልጅ ሞትን ፈልገኸው
ትመጣለህ እንዴ!!! በል ሂድ'ና ከወታደሮቹ እኔን የሚገጥም ትልቅ ሰው
ጥራ።እኔ አንተን ልገድልህ አልፈልግም" አለው።
ዳዉድም፦"እኔ ግን አንተን መግደል እፈልጋለሁ" አለው።
ጃሉትም፦"እሺ ጦርህ፣ ሰይፍህ፣ ጋሻህ፣ ቀስትህ....የታለ? በምንድነው
ምትጋደለው? አለው።
ዳዉድም፦"የኔ ጦር ኢማን ነው።የምጋደልህም በአላህ ስም ነው" አለው።
ይህን ሲሰማ ጃሉት ቁጣ ገነፈለ።ዳዉድንም ሊገድለው ሰይፉን ገትሮ
እየተንደረደረ ሲመጣ፤ዳዉድም ዋዛ አልነበረም'ና በያዘው ድንጋይ አልሞ
ጭንቅላቱን በተነለት።ጃሉትም በዚያች ምት ወድቁ ሞተ።
ጦርነቱም ተጀመረ...ብዙ ከተፋለሙ በኋላም እስራኢላውያን በአላህ ፍቃድ
የጦርነቱን ድል ተቀዳጁ።
ጦነቱ በኢስራኢላውያን አሸናፊነት ሲጠናቀቅ ኢስራኢላውያኑ የቀድሞዋን
ሀገራቸውን ፊለስጢንን ዳግም ሄደው በድል ገቡባት።የጃሉትን ገዳይ የሆነውን
ዳዉድንም ንጉስ አድርገው ሾሙት።
ዳዉድ ምንም እንኳም ንጉስ ቢሆንም በዙፋኑ ቁጭ ብሎ ሳይሆን በእጁ
የሰራውን እና የላቡን ነበር የሚበላው።
ዳዉድ አላህን ሲያወድስ ድምፁ እጅጉን ይማርካል። አላህም ለሱ ዘቡር
የተባለን መፅሀፍ አውርዶለት ነበር።
ዳዉድ ዘቡርን ሲቀራ (ሲያዜም) ድምፁ ከማማሩ የተነሳ፦
፦ተራራዎች አብረውት አላህን ያወድሱ ነበር።
፦ወፎችም አብረውት አላህን ያወድሱ ነበር።
፦የሰዎችም ልብ ይንሰፈሰፍ ነበር።
ዳዉድ ዘቡርን እየቀራ ሲያዜም ጂኖች፣ ሰዎች፣ ወፎች፣ እንስሳቶች በድምፁ
ተማርከው እራሳቸውን በመሳት በረሀብ ይሞቱ ነበር።
ከእለታት አንድ ቀን ዳዉድ በሚህራቡ(ግላዊ የአምልኮ ቦታ) ገብቶ
ወታደሮቹን፦" ማንም ሊገባ እንዳትፈቅዱ" ብሎ በሩን ዘጋ።በዚህ ሁኔታ ላይ
ጌታውን እያመለከ ሳለ ሁለት ሰዎችን ሚህራብ ውስጥ ቆመው
ተመለከታቸው።በሩን ሲያይ በሩ ዝግ ነው....ሰዎቹ ከየት እንደመጡ ግራ
በመጋባት ሲመለከታቸው ሁለቱ ሰዎችም ጠጋ ብለው፦"ዳዉድ ሆይ! አትፍራ።
እኛ ተካሰን እንድትፈርደን ነው የመጣነው።ይህ ወንድሜ 99 በጎች ሲኖሩት ለኔ
ደግሞ 1 በግ ናት ያለችኝ። እሷን ስጠኝ'ና መቶ ሙላልኝ ብሎ እያስገደደኝ
ነው" በማለት አንደኛው አስረዳው።
ዳዉድም የተከሳሹን ቃል ሳይሰማ፦"አይ!! ይሄ እንኳን አንዷን በግህን ስጠኝ
ብሎ በማስገደዱ በርግጥ በድሎሀል" አለው።
ይሄን ግዜ ሁለቱም ሰዎች ተሰወሩ።ዳዉድም አላህ የሁለት ተካሳሾችን ቃል
ሳይሰማ መፍረድ እንደሌለበት ሊያስተምረው መሆኑን በመረዳት ሱጁድ አድርጎ
አላህን ይቅርታ ጠየቀው።
አላህ ለዳዉድ ሱለይማን የተባለን ብልህ እና ሳሊህ ልጅ ረዝቆት ነበር'ና
ከእለታት አንድ ቀን ዳዉድ ልጁን ከጎኑ አስቀምጦ ፍርድ ችሎት ላይ ሳለ ሁለት
ሰዎች መጡ።
ከሳሹ፦"የዚህ ሰውዬ በጎች ማሳዬን ገብተው ያለውን አታክልት በሙሉ
አወደሙብኝ" ብሎ ክሱን አቀረበ።
ዳዉድም ወደተከሳሹ በመዞር፦"ከሳሽህ የሚለው ትክክል ነውን?" በማለት
ጠየቀው።
ተከሳሹም፦"አዎን" ብሎ መለሰለት።
ዳዉድም ከሳሹ በወደመበት ማሳ ምትክ የተከሳሹን በጎች እንዲወስድ ፈረደ።
ይህን ሲከታተል የነበረውም የዳዉድ ልጅ ሱለይማን፦"አባቴ አንድ ግዜ
እንድናገር ፍቀድልኝ" አለው። ዳዉድም ፈቀደለት....
ሱለይማንም፦"እኔ ለየት ያለ ፍርድ አለኝ...እሱም የበጎቹ ባለቤት የከሳሹን
ማሳ ያልማለት። የማሳው ባለቤት ደግሞ ማሳው እስኪለማለት ድረስ
በተከሳሽ በጎች ይጠቀም። የበጎቹ ባለቤት ማሳውን አልምቶ ሲጨርስ
ለማሳው ባለቤት በማስረከብ በጎቹን ከከሳሹ መልሶ ይውሰድ" በማለት
ተናገረ።
ዳዉድም፦"ይህ ጥበባዊ ፍርድ ነው።ጥበብን የሰጠህ ጌታ ምስጋና ይገባው"
አለ
(አደራ ሲረዝም እንዳትሰላቹ።በክፍል እየከፋፈልኩ ከማደነጋግራችሁ በነካ
እጃችሁ ጨርሷት ብዬ ነው።አይሰለቻችሁም አይደል!!!")
ዳዉድ በተፈጥሮው ትንሽ ሲሪየስ ነገር ነው፤ከቤት ሲወጣ ማንም ቤት
እንዳይገባ ሚስቱ ላይ ዘግቶ ነበር የሚወጣው።
ከእለታት አንድ ቀን ዳዉድ እንደልማዱ ቤቱን ዘግቶ ወጣ።ሚስቱም ዝም ብላ
እቤቱን እየተዟዟረች ሳለ አንድ ሰውዬ እቤቱ መሀል ላይ ፀጥ ብሎ ቆሞ
ተመለከተችው'ና፦"አንተ ማን ነህ? ቤት በኩል ገብተህ ነው? ወላሂ ዛሬ ዳዉድ
ይምጣ እና አዋርድሀለሁ" አለችው።
በዚህ ሁኔታ ላይ ሳሉ ዳዉድ እቤቱን ከፍቶ ገባ።ሰውዬው ግን ንቅንቅ
አላለም...ዳዉድም በቁጣ፦"ማን ነህ?" አለው።
ሰውዬውም፦"እኔ ያ ንጉሱችን የማልፈራ...ያ ግርዶሾችም የማያግዱኝ የሆንኩ
ነኝ" አለው።
ዳዉድም፦"አሀ...መለከል መውት ነሃ !! እንኳን ደህና መጣህ የአላህ
መልዐክ" ብሎ ከተቀበለው በኋላ ዳዉድ በተወለደ በ100 አመቱ በእለተ
ቅዳሜ ከሟች ነቢያት ነፍሱ ተቀላቀለች።
ማታውን ጀናዛው ታጥቦ ካደረ በኋላ በነጋታው ለቀብር ብዙ ህዝብ
ተሰበሰበ።ያን ቀን 40.000 (አርባ ሺህ) ባህታዊያንም በቀብሩ ስነ ስርዐት ላይ
ተገኝተዋል።
ህዝቡ ቀብር ቦታ ላይ ሳለ ከፍተኛ የፀሀይ ሀሩር መውረድ ሲጀምር ሱለይማን
ዘንድ ሄደው፦"ፀሀዩን አልቻልንም አንድ ነገር አድርግ" አሉት።
ሱለይማንም አዕዋፍን ሁሉ ጠርቶ ህዝቡን ከፀሀይ እንዲያስጠልሉ አዘዛቸው'ና
በጣም ብዙ ቁጥር ያላቸው አዕዋፍ መጥተው ሰማዩን እንዳይታይ አድርገው
ህዋ ላይ በመንሳፈፍ ሞሉት።
ወፎቹ ህዝቡን ለማስጠለል ሰማዩን ሙሉ በሙሉ ሲከልሉት ሰው ትንፋሽ
ያጥረው ጀመር።
አሁንም ሰዉ መላ በለን ብለው ሱለይማንን ሲያናግሩት ሱለይማንም ወፎችን
ፀሀይዋ ካለችበት አቅጣጫ ብቻ እንዲሆኑ አዘዛቸው።
በዚህ ሁኔታ ነበር እንግዲህ የዳዉድ ቀብር ስነስርዐት የተፈፀመው።
(የአላህ ሰላም እና እዝነት #በዳዉድ ላይ ይሁን።)
_______________________
ምንጮች፦
ﺍﻟﻘﺮﺀﺍﻥ ﺍﻟﻜﺮﻳﻢ
ﺍﻟﺒﺪﺍﻳﺔ ﻭﺍﻟﻨﻬﺎﻳﺔ / ﺍﻟﺠﺰﺀ ﺍﻷﻭﻝ/
ﻗﺼﺺ ﺍﻻﻧﺒﻴﺎﺀ ﻟﻠﺸﻴﺦ ﺍﻟﺸﻌﺮﺍﻭﻯ
ﻗﺼﺺ ﺍﻷﻧﺒﻴﺎﺀ ﻟﻺﻣﺎﻡ ﺍﻟﺤﺎﻓﻆ ﺍﺑﻦ ﻛﺜﻴﺮ
__________
🌲#_የነብዩሏህ_ሱለይማን_ዐለይሂ_ሰላም_ታሪክ🌲
__________
ክፍል 4⃣7⃣ኢንሽዓሏህ
ይ.......ቀ.....ጥ.......ላ.......ል፡፡
የነብያት ታሪኮችንና የሰሀቦችን ታሪክ ከፈለጉ እዚህ👇 ቡት ውስጥ ያገኛሉ
✍@Adem_Ahmed_bot
ከባለፈው የቀጠለ
✅#_የነብያት_ታሪክ✅
🌲#_ነብዩሏህ_ዳውድ_ዐለይሂ_ሰላም🌲
ክፍል 4⃣6⃣
...በዚህ መሀል ነበር የዚህ ታሪክ ባለቤት እና የበጎች እረኛ የሆነው ዳዉድ ኢብን
ኢሻ ኢብን ዑወይድ ኢብን ዓቢር ኢብን ሰልሙን ኢብን ናህሹን ኢብን
ዑወይናዚብ ኢብን ኢረም ኢብን ሀስሩን ኢብን ፋሪስ ኢብን የሁዳ ኢብን
ያዕቁብ ኢብን ኢስሀቅ ኢብም ኢብራሂም......ሰልፉን እየሰነጠቀ ወደ ጃሉት
ወጣ።ይሁን እንጂ ንግስናንም ሆነ የጣሉትን ልጅ ማግባት ፈልጎ አይደለም።
እስራኢላውያንም ይሄ ደካማ እረኛ ምንም አይነት ጦርም ይሁን ጋሻ ሳይዝ ያን
ተራራ ሚያህል ሰውዬ ሊገጥም ሲወጣ በግርምት ይመለከቱት ነበር።
ዳዉድ እረኞች የሚይዙትን በትር በአንድ እጁ ይዞ በሌላው እጆ ድንጋይ
ይዟል።ጃሉት ለፍልሚያ የቆመበትን ቦታ ዳዉድ ልክ እንደደረሰ ፊት ለፊቱ ቆመ።
ጃሉት ይህን ልጅ እግር እረኛ ሲመለከት እያሾፈ፦"አንተ ልጅ ሞትን ፈልገኸው
ትመጣለህ እንዴ!!! በል ሂድ'ና ከወታደሮቹ እኔን የሚገጥም ትልቅ ሰው
ጥራ።እኔ አንተን ልገድልህ አልፈልግም" አለው።
ዳዉድም፦"እኔ ግን አንተን መግደል እፈልጋለሁ" አለው።
ጃሉትም፦"እሺ ጦርህ፣ ሰይፍህ፣ ጋሻህ፣ ቀስትህ....የታለ? በምንድነው
ምትጋደለው? አለው።
ዳዉድም፦"የኔ ጦር ኢማን ነው።የምጋደልህም በአላህ ስም ነው" አለው።
ይህን ሲሰማ ጃሉት ቁጣ ገነፈለ።ዳዉድንም ሊገድለው ሰይፉን ገትሮ
እየተንደረደረ ሲመጣ፤ዳዉድም ዋዛ አልነበረም'ና በያዘው ድንጋይ አልሞ
ጭንቅላቱን በተነለት።ጃሉትም በዚያች ምት ወድቁ ሞተ።
ጦርነቱም ተጀመረ...ብዙ ከተፋለሙ በኋላም እስራኢላውያን በአላህ ፍቃድ
የጦርነቱን ድል ተቀዳጁ።
ጦነቱ በኢስራኢላውያን አሸናፊነት ሲጠናቀቅ ኢስራኢላውያኑ የቀድሞዋን
ሀገራቸውን ፊለስጢንን ዳግም ሄደው በድል ገቡባት።የጃሉትን ገዳይ የሆነውን
ዳዉድንም ንጉስ አድርገው ሾሙት።
ዳዉድ ምንም እንኳም ንጉስ ቢሆንም በዙፋኑ ቁጭ ብሎ ሳይሆን በእጁ
የሰራውን እና የላቡን ነበር የሚበላው።
ዳዉድ አላህን ሲያወድስ ድምፁ እጅጉን ይማርካል። አላህም ለሱ ዘቡር
የተባለን መፅሀፍ አውርዶለት ነበር።
ዳዉድ ዘቡርን ሲቀራ (ሲያዜም) ድምፁ ከማማሩ የተነሳ፦
፦ተራራዎች አብረውት አላህን ያወድሱ ነበር።
፦ወፎችም አብረውት አላህን ያወድሱ ነበር።
፦የሰዎችም ልብ ይንሰፈሰፍ ነበር።
ዳዉድ ዘቡርን እየቀራ ሲያዜም ጂኖች፣ ሰዎች፣ ወፎች፣ እንስሳቶች በድምፁ
ተማርከው እራሳቸውን በመሳት በረሀብ ይሞቱ ነበር።
ከእለታት አንድ ቀን ዳዉድ በሚህራቡ(ግላዊ የአምልኮ ቦታ) ገብቶ
ወታደሮቹን፦" ማንም ሊገባ እንዳትፈቅዱ" ብሎ በሩን ዘጋ።በዚህ ሁኔታ ላይ
ጌታውን እያመለከ ሳለ ሁለት ሰዎችን ሚህራብ ውስጥ ቆመው
ተመለከታቸው።በሩን ሲያይ በሩ ዝግ ነው....ሰዎቹ ከየት እንደመጡ ግራ
በመጋባት ሲመለከታቸው ሁለቱ ሰዎችም ጠጋ ብለው፦"ዳዉድ ሆይ! አትፍራ።
እኛ ተካሰን እንድትፈርደን ነው የመጣነው።ይህ ወንድሜ 99 በጎች ሲኖሩት ለኔ
ደግሞ 1 በግ ናት ያለችኝ። እሷን ስጠኝ'ና መቶ ሙላልኝ ብሎ እያስገደደኝ
ነው" በማለት አንደኛው አስረዳው።
ዳዉድም የተከሳሹን ቃል ሳይሰማ፦"አይ!! ይሄ እንኳን አንዷን በግህን ስጠኝ
ብሎ በማስገደዱ በርግጥ በድሎሀል" አለው።
ይሄን ግዜ ሁለቱም ሰዎች ተሰወሩ።ዳዉድም አላህ የሁለት ተካሳሾችን ቃል
ሳይሰማ መፍረድ እንደሌለበት ሊያስተምረው መሆኑን በመረዳት ሱጁድ አድርጎ
አላህን ይቅርታ ጠየቀው።
አላህ ለዳዉድ ሱለይማን የተባለን ብልህ እና ሳሊህ ልጅ ረዝቆት ነበር'ና
ከእለታት አንድ ቀን ዳዉድ ልጁን ከጎኑ አስቀምጦ ፍርድ ችሎት ላይ ሳለ ሁለት
ሰዎች መጡ።
ከሳሹ፦"የዚህ ሰውዬ በጎች ማሳዬን ገብተው ያለውን አታክልት በሙሉ
አወደሙብኝ" ብሎ ክሱን አቀረበ።
ዳዉድም ወደተከሳሹ በመዞር፦"ከሳሽህ የሚለው ትክክል ነውን?" በማለት
ጠየቀው።
ተከሳሹም፦"አዎን" ብሎ መለሰለት።
ዳዉድም ከሳሹ በወደመበት ማሳ ምትክ የተከሳሹን በጎች እንዲወስድ ፈረደ።
ይህን ሲከታተል የነበረውም የዳዉድ ልጅ ሱለይማን፦"አባቴ አንድ ግዜ
እንድናገር ፍቀድልኝ" አለው። ዳዉድም ፈቀደለት....
ሱለይማንም፦"እኔ ለየት ያለ ፍርድ አለኝ...እሱም የበጎቹ ባለቤት የከሳሹን
ማሳ ያልማለት። የማሳው ባለቤት ደግሞ ማሳው እስኪለማለት ድረስ
በተከሳሽ በጎች ይጠቀም። የበጎቹ ባለቤት ማሳውን አልምቶ ሲጨርስ
ለማሳው ባለቤት በማስረከብ በጎቹን ከከሳሹ መልሶ ይውሰድ" በማለት
ተናገረ።
ዳዉድም፦"ይህ ጥበባዊ ፍርድ ነው።ጥበብን የሰጠህ ጌታ ምስጋና ይገባው"
አለ
(አደራ ሲረዝም እንዳትሰላቹ።በክፍል እየከፋፈልኩ ከማደነጋግራችሁ በነካ
እጃችሁ ጨርሷት ብዬ ነው።አይሰለቻችሁም አይደል!!!")
ዳዉድ በተፈጥሮው ትንሽ ሲሪየስ ነገር ነው፤ከቤት ሲወጣ ማንም ቤት
እንዳይገባ ሚስቱ ላይ ዘግቶ ነበር የሚወጣው።
ከእለታት አንድ ቀን ዳዉድ እንደልማዱ ቤቱን ዘግቶ ወጣ።ሚስቱም ዝም ብላ
እቤቱን እየተዟዟረች ሳለ አንድ ሰውዬ እቤቱ መሀል ላይ ፀጥ ብሎ ቆሞ
ተመለከተችው'ና፦"አንተ ማን ነህ? ቤት በኩል ገብተህ ነው? ወላሂ ዛሬ ዳዉድ
ይምጣ እና አዋርድሀለሁ" አለችው።
በዚህ ሁኔታ ላይ ሳሉ ዳዉድ እቤቱን ከፍቶ ገባ።ሰውዬው ግን ንቅንቅ
አላለም...ዳዉድም በቁጣ፦"ማን ነህ?" አለው።
ሰውዬውም፦"እኔ ያ ንጉሱችን የማልፈራ...ያ ግርዶሾችም የማያግዱኝ የሆንኩ
ነኝ" አለው።
ዳዉድም፦"አሀ...መለከል መውት ነሃ !! እንኳን ደህና መጣህ የአላህ
መልዐክ" ብሎ ከተቀበለው በኋላ ዳዉድ በተወለደ በ100 አመቱ በእለተ
ቅዳሜ ከሟች ነቢያት ነፍሱ ተቀላቀለች።
ማታውን ጀናዛው ታጥቦ ካደረ በኋላ በነጋታው ለቀብር ብዙ ህዝብ
ተሰበሰበ።ያን ቀን 40.000 (አርባ ሺህ) ባህታዊያንም በቀብሩ ስነ ስርዐት ላይ
ተገኝተዋል።
ህዝቡ ቀብር ቦታ ላይ ሳለ ከፍተኛ የፀሀይ ሀሩር መውረድ ሲጀምር ሱለይማን
ዘንድ ሄደው፦"ፀሀዩን አልቻልንም አንድ ነገር አድርግ" አሉት።
ሱለይማንም አዕዋፍን ሁሉ ጠርቶ ህዝቡን ከፀሀይ እንዲያስጠልሉ አዘዛቸው'ና
በጣም ብዙ ቁጥር ያላቸው አዕዋፍ መጥተው ሰማዩን እንዳይታይ አድርገው
ህዋ ላይ በመንሳፈፍ ሞሉት።
ወፎቹ ህዝቡን ለማስጠለል ሰማዩን ሙሉ በሙሉ ሲከልሉት ሰው ትንፋሽ
ያጥረው ጀመር።
አሁንም ሰዉ መላ በለን ብለው ሱለይማንን ሲያናግሩት ሱለይማንም ወፎችን
ፀሀይዋ ካለችበት አቅጣጫ ብቻ እንዲሆኑ አዘዛቸው።
በዚህ ሁኔታ ነበር እንግዲህ የዳዉድ ቀብር ስነስርዐት የተፈፀመው።
(የአላህ ሰላም እና እዝነት #በዳዉድ ላይ ይሁን።)
_______________________
ምንጮች፦
ﺍﻟﻘﺮﺀﺍﻥ ﺍﻟﻜﺮﻳﻢ
ﺍﻟﺒﺪﺍﻳﺔ ﻭﺍﻟﻨﻬﺎﻳﺔ / ﺍﻟﺠﺰﺀ ﺍﻷﻭﻝ/
ﻗﺼﺺ ﺍﻻﻧﺒﻴﺎﺀ ﻟﻠﺸﻴﺦ ﺍﻟﺸﻌﺮﺍﻭﻯ
ﻗﺼﺺ ﺍﻷﻧﺒﻴﺎﺀ ﻟﻺﻣﺎﻡ ﺍﻟﺤﺎﻓﻆ ﺍﺑﻦ ﻛﺜﻴﺮ
__________
🌲#_የነብዩሏህ_ሱለይማን_ዐለይሂ_ሰላም_ታሪክ🌲
__________
ክፍል 4⃣7⃣ኢንሽዓሏህ
ይ.......ቀ.....ጥ.......ላ.......ል፡፡
የነብያት ታሪኮችንና የሰሀቦችን ታሪክ ከፈለጉ እዚህ👇 ቡት ውስጥ ያገኛሉ
✍@Adem_Ahmed_bot