📍ስለ ህይወት
💡አንድ አባባል አለ በጣም የምወደው ''ቁም ነገሩ ምን ያህል እድሜ ኖረሀል ሳይሆን ምን አይነት ህይወት አሳልፈሀል'' ብዙዎቻችን ካለፍንባቸውን ህይወቶች የምንማረው እሩጫችንን ከጨረስን በኋላ በእርጅና ትናንትን ስንመለከት ነው። በወጣትነታችን ያለፍንባቸውን የህይወት ዱካዎች አስተውለን ማጥናት ምንችል ቢሆን ግን ነጋችንን ብሩህ የማድረግ ትልቅ እድል ይኖረናል።
"የኋላው ከሌለ የለም የፊቱ" እንዲል ያገሬ ሰው... የዛሬው ህይወታችን ያለፍንባቸው የህይወት ውጣ ውረዶቻችን ቅጂዎች ናቸው ። እናም ስለ ህይወት የገባኝን ከትናንቶቼ የተማርኳቸውን እንደ አባት ልንገራቹህ.
💡በዚህ አለም ላይ ቋሚ ነገር የለም።
ዛሬ የወደዱህ ነገ ይጠሉሀል ዛሬ ያከብሩህ ነገ ይንቁሀል ዛሬ እንደ አስፈላጊ የተመለከቱህ ነገ አንተን ረስተው ሌላ ህይወትን ሲጀምሩ ታያለህ አየህ ሁሌም ቢሆን ለሰዎች አብዝተህ መጨነቅ የለብህም! ከሰዎች አብዝተህ መጠበቅ የለብህም! በዚህ አለም ቋሚ ነገር የለምና ያለህባትን ህይወት እና ግዜ ብቻ በተገቢው ማጣጣም እወቅበት!
📍ሰዎች ደስታ እና ሀዘንህን የሚፅፉልህ የህይወትህ ደራሲ እንዲሆኑ አትፍቀድላቸው! እነግርሀለው አሁንም ያለኸው አንተ እና አንተ ብቻ ናቹህ ስትሞትም የሚወዱህ ቀብረውህ ህይወትን ይቀጥላሉ... ሁሉም የመጣው ለህይወት እንጂ ለአንተ እንዳልሆነ ተረዳ!
ስለዚህም ለራስህ ክብርን ግዜን ፍቅርን መስጠት እወቅበት ከህይወት ጋር ተዛመድ!
አንድ እውነትን ተረዳ ማንም ሚወድህም ሆነ ሚንቅህ አንተ ላይ ካየው ነገር ተነስቶ ብቻ ነው ሰዎችን አብዝተህ ከማመንህ በላይ ራስህን እመን! ራስህ ላይ ስራ! ሌላው ከሰዎች የሚሰጡህን መልካም ነገሮችን ውደድላቸው አክብርላቸው ነገር ግን ይሄ የመጣው ለራስህ ካለህ ጥልቅ ክብር እንደሆነ ማስተዋል መቻል አለበህ!
♦️ስለዚህም የምትወዳቸውን ሰዎች እንዳታጣ የምትደውን ማንነትህን አትጣለው! ሌሎች ሰዎች ደግሞ ለአንተ ያሰቡ በመምሰል እነሱ በሚፈልጉት ልክ እንድትራመድ መንገድ ሊያመቻቹልህ ይችላሉ ይህ ማለት በሌላ ቋንቋ
(የግል ባርያዬ ላደርግህ እያሰብኩ ነው) እንደማለት ነው ። አንተም ስለምትወዳቸው ውለታም ስለዋሉልህ እነሱን ካለማጣት እና ለማስደሰት የራስህን ማንነት ትተዋለህ ሰዎችም ዙሪያህን እንደተቆጣጠሩ ሲሰማቸው ጥለውህ ይሄዳሉ ! አየህ በማንነትህ አትደራደር ማንም እንዲ ሁን ሊልህ ቢሞክር ከመስመሩ እንዳታሳልፈው! ሰዎች የአንተን ነገር ማክበር ሚጀምሩት ለራስህ ካለህ ፅኑ እምነት ተነስተው ነው።
💎ይቺን እወቅልኝ ማንም በዚህ አለም ያለምክኒያት አብሮህ ሊሆን አይችልም ''ማንም" ካላመንክ ይወዱኛል ብለህ ያሰብካቸውን ሰዎች ''ለምን ከኔ ጋር ሆንክ/ሽ?" በላቸው የሀገር ምክኒያቶችን ሲደረድሩልህ ትሰማለህ
💡ያለ አንዳች ምክኒያት አንተን የሚወድህ ፈጣሪህ ብቻ ነው። ሰዎች ሁኔታዊ እንደሆኑ እወቅ የቱንም ያህል ቢወዱህ እነሱ ሊያዩህ ከሚፈልጉበት ቦታ ወርደህ ካዩህ ይለዩሀል በቃ ይሄ የሰዎች ተፈጥሮ ነው። ከነፍስህ ጋር መፋቀርን ልመድ ሰዎች ሳይኖሩ ሙሉ መሆንን ልመድ ሁሉም ትቶህ ሄዶ መፈንደቅን ልመድ በህይወት ጭለማህ ውስጥ ብቻህን መሳቅን ልመድ! ለህይወት ቁስሎችህ ሁነኛ ዶ/ር መሆንን ልመድ!
📍ራስህን በወደድክ ቁጥር ህይወት አንተን በጥልቅ መንፈስ ማፍቀር ትጀምራለች... ሰዎችም የህይወት አንዷ አካል ስለሆኑ ወደ በአንተው መሳብ ይጀምራሉ። በሰዎች አትደገፍ ! በራስህ መቆም እስኪሳንህ ድረስ ለሰዎች ራስህን አሳልፈህ አትስጥ ሰዎችን ውደድ ግን በሰዎች አትደገፍ ዘወር ቢሉ መቆም እንደምትችል አሳያቸው!
💡ስትወድቅ አይቶ ሚያነሳህ ፈጣሪ እንጂ ሰዎች አይደሉም። ሰዎች ሁሌም የተሻለን ነገር በተፈጥሮዋቸው ይፈልጋሉ ስለዚህ አንተ ከነሱ ግዜ ጥሎህ አንሰህ ከተገኘህ ጥለውህ ይሄዳሉ እንዳትረሳ! በመጨረሻም አምላክህን ህይወትህን እና ራስህን አጥብቀህ አፍቅር ! ህይወት ያን ያህል ቀላል ትሆናለች ጀግናው!
✍Dîž Âb
ውብ አሁን❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✍@EthioHumanityBot
💡አንድ አባባል አለ በጣም የምወደው ''ቁም ነገሩ ምን ያህል እድሜ ኖረሀል ሳይሆን ምን አይነት ህይወት አሳልፈሀል'' ብዙዎቻችን ካለፍንባቸውን ህይወቶች የምንማረው እሩጫችንን ከጨረስን በኋላ በእርጅና ትናንትን ስንመለከት ነው። በወጣትነታችን ያለፍንባቸውን የህይወት ዱካዎች አስተውለን ማጥናት ምንችል ቢሆን ግን ነጋችንን ብሩህ የማድረግ ትልቅ እድል ይኖረናል።
"የኋላው ከሌለ የለም የፊቱ" እንዲል ያገሬ ሰው... የዛሬው ህይወታችን ያለፍንባቸው የህይወት ውጣ ውረዶቻችን ቅጂዎች ናቸው ። እናም ስለ ህይወት የገባኝን ከትናንቶቼ የተማርኳቸውን እንደ አባት ልንገራቹህ.
💡በዚህ አለም ላይ ቋሚ ነገር የለም።
ዛሬ የወደዱህ ነገ ይጠሉሀል ዛሬ ያከብሩህ ነገ ይንቁሀል ዛሬ እንደ አስፈላጊ የተመለከቱህ ነገ አንተን ረስተው ሌላ ህይወትን ሲጀምሩ ታያለህ አየህ ሁሌም ቢሆን ለሰዎች አብዝተህ መጨነቅ የለብህም! ከሰዎች አብዝተህ መጠበቅ የለብህም! በዚህ አለም ቋሚ ነገር የለምና ያለህባትን ህይወት እና ግዜ ብቻ በተገቢው ማጣጣም እወቅበት!
📍ሰዎች ደስታ እና ሀዘንህን የሚፅፉልህ የህይወትህ ደራሲ እንዲሆኑ አትፍቀድላቸው! እነግርሀለው አሁንም ያለኸው አንተ እና አንተ ብቻ ናቹህ ስትሞትም የሚወዱህ ቀብረውህ ህይወትን ይቀጥላሉ... ሁሉም የመጣው ለህይወት እንጂ ለአንተ እንዳልሆነ ተረዳ!
ስለዚህም ለራስህ ክብርን ግዜን ፍቅርን መስጠት እወቅበት ከህይወት ጋር ተዛመድ!
አንድ እውነትን ተረዳ ማንም ሚወድህም ሆነ ሚንቅህ አንተ ላይ ካየው ነገር ተነስቶ ብቻ ነው ሰዎችን አብዝተህ ከማመንህ በላይ ራስህን እመን! ራስህ ላይ ስራ! ሌላው ከሰዎች የሚሰጡህን መልካም ነገሮችን ውደድላቸው አክብርላቸው ነገር ግን ይሄ የመጣው ለራስህ ካለህ ጥልቅ ክብር እንደሆነ ማስተዋል መቻል አለበህ!
♦️ስለዚህም የምትወዳቸውን ሰዎች እንዳታጣ የምትደውን ማንነትህን አትጣለው! ሌሎች ሰዎች ደግሞ ለአንተ ያሰቡ በመምሰል እነሱ በሚፈልጉት ልክ እንድትራመድ መንገድ ሊያመቻቹልህ ይችላሉ ይህ ማለት በሌላ ቋንቋ
(የግል ባርያዬ ላደርግህ እያሰብኩ ነው) እንደማለት ነው ። አንተም ስለምትወዳቸው ውለታም ስለዋሉልህ እነሱን ካለማጣት እና ለማስደሰት የራስህን ማንነት ትተዋለህ ሰዎችም ዙሪያህን እንደተቆጣጠሩ ሲሰማቸው ጥለውህ ይሄዳሉ ! አየህ በማንነትህ አትደራደር ማንም እንዲ ሁን ሊልህ ቢሞክር ከመስመሩ እንዳታሳልፈው! ሰዎች የአንተን ነገር ማክበር ሚጀምሩት ለራስህ ካለህ ፅኑ እምነት ተነስተው ነው።
💎ይቺን እወቅልኝ ማንም በዚህ አለም ያለምክኒያት አብሮህ ሊሆን አይችልም ''ማንም" ካላመንክ ይወዱኛል ብለህ ያሰብካቸውን ሰዎች ''ለምን ከኔ ጋር ሆንክ/ሽ?" በላቸው የሀገር ምክኒያቶችን ሲደረድሩልህ ትሰማለህ
💡ያለ አንዳች ምክኒያት አንተን የሚወድህ ፈጣሪህ ብቻ ነው። ሰዎች ሁኔታዊ እንደሆኑ እወቅ የቱንም ያህል ቢወዱህ እነሱ ሊያዩህ ከሚፈልጉበት ቦታ ወርደህ ካዩህ ይለዩሀል በቃ ይሄ የሰዎች ተፈጥሮ ነው። ከነፍስህ ጋር መፋቀርን ልመድ ሰዎች ሳይኖሩ ሙሉ መሆንን ልመድ ሁሉም ትቶህ ሄዶ መፈንደቅን ልመድ በህይወት ጭለማህ ውስጥ ብቻህን መሳቅን ልመድ! ለህይወት ቁስሎችህ ሁነኛ ዶ/ር መሆንን ልመድ!
📍ራስህን በወደድክ ቁጥር ህይወት አንተን በጥልቅ መንፈስ ማፍቀር ትጀምራለች... ሰዎችም የህይወት አንዷ አካል ስለሆኑ ወደ በአንተው መሳብ ይጀምራሉ። በሰዎች አትደገፍ ! በራስህ መቆም እስኪሳንህ ድረስ ለሰዎች ራስህን አሳልፈህ አትስጥ ሰዎችን ውደድ ግን በሰዎች አትደገፍ ዘወር ቢሉ መቆም እንደምትችል አሳያቸው!
💡ስትወድቅ አይቶ ሚያነሳህ ፈጣሪ እንጂ ሰዎች አይደሉም። ሰዎች ሁሌም የተሻለን ነገር በተፈጥሮዋቸው ይፈልጋሉ ስለዚህ አንተ ከነሱ ግዜ ጥሎህ አንሰህ ከተገኘህ ጥለውህ ይሄዳሉ እንዳትረሳ! በመጨረሻም አምላክህን ህይወትህን እና ራስህን አጥብቀህ አፍቅር ! ህይወት ያን ያህል ቀላል ትሆናለች ጀግናው!
✍Dîž Âb
ውብ አሁን❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✍@EthioHumanityBot