💡አንድ ወጣት ሰው ስለአርምሞ ሊቀስም ከZen መምህር ዘንድ መጥቶ ቢጠይቅ "ታግሰህ መጠብቅ ይቻልሃል ወይ?" አሉት ።
ወጣቱ "ምን ያህል ጊዜ?" መልሶ ጠየቀ።
መምህሩ "አንተን ለማባረር ይሄ መልስህ ብቻ በቂ ነበር። 'ምን ያህል ጊዜ' ብሎ መጠየቅ ማለት ለመጠበቅ ዝግጁ አይደለህም ማለት ነው። ከቻልክ 'ምን ያህል ጊዜ' ብለህ ሳትጠይቅ ዝም ብለህ ከጠብቅክ መጠበቅን ትችላለህ" አሉት።
📍ወጣቱ ነገሩ ገባውና እጅ ነስቶ ከመምህሩ ዘንድ ከረመ። ያለምንም ቀለም ዓመቱ ነጎደ። ሁለተኛው ተከተለ። ሶስተኛውም ተደገመ። 'አሁንስ በዛ! ምንም አልተጀመረም ፤ አንድ ክፍል እንኳን። ሰው ምን ያህል ጊዜ ነው መጠበቅ ያለበት?' ድጋሚ ጥያቄዎች ከአዕምሮው ቦታ ይዘው 'እስከ መቼ?' ብሎ ከመምህሩ ዘንድ አቅንቶ "ሶስት ዓመት ጠበኩኝኮ" ሲል ጠየቃቸው።
💡መምህሩ "እየቆጠርክ ነበር? በቀላሉ ይሄ የሚያሳየው እንዴት መጠበቅ እንዳለብህ አለማወቅህን ነው። መቁጠር? ከኔ ጋር ቀናትን መቁጠር? ላንተ ቀናቶች ዘላለም ሆነው ይሆናል፤ ለኔ ደግሞ ዘላለም ቀናት ሊመስሉ ይችላሉ። አንተ ከንቱ መጠበቅ አለብህ። መጠበቅ ማለት ምን እንደሆነ መማር ይኖርብሃል። ብቻ ተዘጋጅ ከነገ ጀምሮ ትምህርቱን እንጀምራለን" አሉት።
📍ትምህርቱ እንግዳ ነገር ነበር። ወጣቱ ወለል እያጸዳ እያለ መምህሩ ከጀርባው መጥቶ በያዘው ነገር ኋላውን ነረተው። ወጣቱ በርግጎ "ከሶስት ዓመት መጠበቅ በኋላ ይሄ ነው የአርምሞ መግቢያ?" አለው። መምህሩ "በሚገባ። አሁን ንቁ ሁን። በየትኛው ጊዜ፣ በየትኛው ወቅት ስለምጠልዝህ ንቁ ሁን። የራስህ ጠባቂ ሁን" አሉት።
ምቱ እና ንረታው ለወራት ቀጠለ። ምክንያቱም ሽማግሌው ቢያረጅም ኮቴ ቢስ ነበር፤ ድንገት ብቅ ይሉና ወጣቱን ያቀምሱታል። ይሄም በዝቶ ስለተደጋገመ የገላው ሕመም ምሽት ላይ ይጠዘጥዘው ነበር።
📍ሆኖም ቀስ በቀስ የወጣቱ ደመ-ነፍስ ነቃ። ከኋላም ቢሆን መምህሩ ሊመቱት ተቃርበው እያሉ ያመልጥ ጀመር። በሥራ ቢጠመድ እንኳ ቆሌው ይነግረዋል። የሕመሙ ሥቃይ የንቃት ግዴታ ጥሎበት ነበር።
💎ሕመም ለእድገት ግድ ነው። ሥቃይ ለማደግ ፍፁም አስፈላጊ ነው። ካልተሰቃየህ በስተቀር ንቃትህ ሊደምቅ አይችልም። ሥቃይ ልቦናን ያስገዛል፤ ፍቃደ-ስቃይም እልፍ አስተውሎትን ያሸምታል። [ Pain is a must for growth, suffering is absolutely necessary for growth. Unless you suffer you cannot be aware. Suffering brings awareness, and voluntary suffering brings tremendous awareness.]።
🔆ወጣቱ ማምለጥ ይችል ነበር፤ ማንም አላገደውም። ግን ሥቃዩን ፈቀደ። መምህሩን አስቀደመ። ምርጫው ሆነ። ለምን እንደሆነ አሁን ይገለጥለት ጀመር ለወጣቱ። "ይሄ የመምህሩ አስተምህሮ ነው። እንደዚህ ነው አርምሞን የሚያስተምረው" ከልቦናው ጣፈው። አብዝቶ አመሰገነ።
መምህሩ ከጀርባው እያደቡ መጥተው ሳይነርቱት በፊት ወጣቱ ተስፈንጥሮ ገሸሽ ቢል ዱላው ከመሬት ሲወድቅ በጣም ተደሰቱ። በወጣቱ ልቦና አዲስ አስተውሎት ፈነጠቀ፤ እናም መምህሩ ባረኩለት።
💡ዳሩ ግን ከዛን ዕለት ወዲህ ነገሮች ከበዱ። መምህሩ በውድቅት ጨለማ ወጣቱ ሲያሸልብ ይቆጉት ጀመር። 'አሁን ልኩን አለፈ። በጨለማ! ለዛውም በየትኛውም ሰዓት!' እንደውነቱ መምህሩ ስለጃጁ እምብዛም ማንቀላፋት አይችሉም። በየትኛው ጊዜ የነቃ ሲመስላቸው ሄደው ወጣቱን ይነርቱታል። 'ይሄ ቅጥ-አንባሩ የጠፋ ጅልነት ነው። ራሴን ቀን መከላከል አያዳግተኝም፤ መሮጥ፣ ማምለጥ፣ ዞር ማለት እችላለሁ። ግን ሳንቀላፋ ምን ማድረግ ይቻለኝ ይሆን?' አላለም፤ አልጠየቀም አሁን። ዝም ብሎ ተረዳ። 'ሒደቱ ላይገባኝ ይችላል ቢሆንም እነዛ የቀን ዱላዎች ብዙ ትሩፋት ስለነበራቸው ነው ይሄን ልውጠት (transformation) በኔ ላይ ያመጡት። ካለምንም ጥያቄ ይሄንንም እቀበለዋለሁ' አለ።
መምህሩም "ይሄ ጥሩ ምልክት ነው። ለመጀመሪያ ጊዜ እምነት ጥለህ ጥያቄ አላነሳህም። ሁለት ወይም ሶስት ወራት ሲደበደብ ገላው በየቀኑ ቁስል ቢሰማውም አንድ ዕለት ሆነለት፤ በፅልመት ራሱን መከላከል ቻለ። መምህሩም እክፍሉ ሲዘልቁ "ተረጋጉ…ነቅቻለሁ" አላቸው። እንደዚሁ ደጋግሞም ተከሰተ።
🔷 ወጣቱን መነረት የሚቻል አልሆነም። መምህሩ እክፍሉ እንደጠለቁ፣ ፈጽሞ የማይተኛ ይመስል አይኖቹ ፈጠዋል። ግን እንደዛ አልነበረም፤ ወጣቱ ሲያሸልብ በጣም ችኩል ነበር። ሆኖም እውስጥ እንደቀንዲል የበራች ትንሽ የበረዶ ግግር ጫፍ የመሰለች አለላ ንቃት ለቅኝት (watching)፣ ለጥበቃ (waiting) ከሽልብታ ዓለም አምልጣ ወጥታ ስለነበረ ነው ቀድማ ምታባንነው።
📍መምህሩ ተደሰቱ። በበነጋው ማለዳ መምህሩ ከአንድ ዛፍ ስር አርፈው ጥንታዊ መጻሕፍ ያነባሉ። ወጣቱ ያትክልት ሥፍራውን እያጸዳ 'ይሄ ሽማግሌ ለዓመት ያህል ጠዋት፣ ማታ ሲነርተኝ ነበር። እሱን አንዴ ብቻ ብደልቀው እንዴት ይሆናል? ባየው ደስ ይለኛል እንዴት እንደሚሆን?' የሚል ሐሳብ ብልጭ አለበት።
መምህሩም በዛው ቅፅበት መጻሕፉን ከደኑና "አንተ ቂል! ይሄ ከንቱ ሐሳብ ይቅርብህ፤ እኔ ለራሴ አቅመ ደካማ ነኝ" ብለው ለወጣቱ መለሱለት ....
❤️ውብ አሁን ለሁላችን😊
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✍ @EthioHumanityBot
ወጣቱ "ምን ያህል ጊዜ?" መልሶ ጠየቀ።
መምህሩ "አንተን ለማባረር ይሄ መልስህ ብቻ በቂ ነበር። 'ምን ያህል ጊዜ' ብሎ መጠየቅ ማለት ለመጠበቅ ዝግጁ አይደለህም ማለት ነው። ከቻልክ 'ምን ያህል ጊዜ' ብለህ ሳትጠይቅ ዝም ብለህ ከጠብቅክ መጠበቅን ትችላለህ" አሉት።
📍ወጣቱ ነገሩ ገባውና እጅ ነስቶ ከመምህሩ ዘንድ ከረመ። ያለምንም ቀለም ዓመቱ ነጎደ። ሁለተኛው ተከተለ። ሶስተኛውም ተደገመ። 'አሁንስ በዛ! ምንም አልተጀመረም ፤ አንድ ክፍል እንኳን። ሰው ምን ያህል ጊዜ ነው መጠበቅ ያለበት?' ድጋሚ ጥያቄዎች ከአዕምሮው ቦታ ይዘው 'እስከ መቼ?' ብሎ ከመምህሩ ዘንድ አቅንቶ "ሶስት ዓመት ጠበኩኝኮ" ሲል ጠየቃቸው።
💡መምህሩ "እየቆጠርክ ነበር? በቀላሉ ይሄ የሚያሳየው እንዴት መጠበቅ እንዳለብህ አለማወቅህን ነው። መቁጠር? ከኔ ጋር ቀናትን መቁጠር? ላንተ ቀናቶች ዘላለም ሆነው ይሆናል፤ ለኔ ደግሞ ዘላለም ቀናት ሊመስሉ ይችላሉ። አንተ ከንቱ መጠበቅ አለብህ። መጠበቅ ማለት ምን እንደሆነ መማር ይኖርብሃል። ብቻ ተዘጋጅ ከነገ ጀምሮ ትምህርቱን እንጀምራለን" አሉት።
📍ትምህርቱ እንግዳ ነገር ነበር። ወጣቱ ወለል እያጸዳ እያለ መምህሩ ከጀርባው መጥቶ በያዘው ነገር ኋላውን ነረተው። ወጣቱ በርግጎ "ከሶስት ዓመት መጠበቅ በኋላ ይሄ ነው የአርምሞ መግቢያ?" አለው። መምህሩ "በሚገባ። አሁን ንቁ ሁን። በየትኛው ጊዜ፣ በየትኛው ወቅት ስለምጠልዝህ ንቁ ሁን። የራስህ ጠባቂ ሁን" አሉት።
ምቱ እና ንረታው ለወራት ቀጠለ። ምክንያቱም ሽማግሌው ቢያረጅም ኮቴ ቢስ ነበር፤ ድንገት ብቅ ይሉና ወጣቱን ያቀምሱታል። ይሄም በዝቶ ስለተደጋገመ የገላው ሕመም ምሽት ላይ ይጠዘጥዘው ነበር።
📍ሆኖም ቀስ በቀስ የወጣቱ ደመ-ነፍስ ነቃ። ከኋላም ቢሆን መምህሩ ሊመቱት ተቃርበው እያሉ ያመልጥ ጀመር። በሥራ ቢጠመድ እንኳ ቆሌው ይነግረዋል። የሕመሙ ሥቃይ የንቃት ግዴታ ጥሎበት ነበር።
💎ሕመም ለእድገት ግድ ነው። ሥቃይ ለማደግ ፍፁም አስፈላጊ ነው። ካልተሰቃየህ በስተቀር ንቃትህ ሊደምቅ አይችልም። ሥቃይ ልቦናን ያስገዛል፤ ፍቃደ-ስቃይም እልፍ አስተውሎትን ያሸምታል። [ Pain is a must for growth, suffering is absolutely necessary for growth. Unless you suffer you cannot be aware. Suffering brings awareness, and voluntary suffering brings tremendous awareness.]።
🔆ወጣቱ ማምለጥ ይችል ነበር፤ ማንም አላገደውም። ግን ሥቃዩን ፈቀደ። መምህሩን አስቀደመ። ምርጫው ሆነ። ለምን እንደሆነ አሁን ይገለጥለት ጀመር ለወጣቱ። "ይሄ የመምህሩ አስተምህሮ ነው። እንደዚህ ነው አርምሞን የሚያስተምረው" ከልቦናው ጣፈው። አብዝቶ አመሰገነ።
መምህሩ ከጀርባው እያደቡ መጥተው ሳይነርቱት በፊት ወጣቱ ተስፈንጥሮ ገሸሽ ቢል ዱላው ከመሬት ሲወድቅ በጣም ተደሰቱ። በወጣቱ ልቦና አዲስ አስተውሎት ፈነጠቀ፤ እናም መምህሩ ባረኩለት።
💡ዳሩ ግን ከዛን ዕለት ወዲህ ነገሮች ከበዱ። መምህሩ በውድቅት ጨለማ ወጣቱ ሲያሸልብ ይቆጉት ጀመር። 'አሁን ልኩን አለፈ። በጨለማ! ለዛውም በየትኛውም ሰዓት!' እንደውነቱ መምህሩ ስለጃጁ እምብዛም ማንቀላፋት አይችሉም። በየትኛው ጊዜ የነቃ ሲመስላቸው ሄደው ወጣቱን ይነርቱታል። 'ይሄ ቅጥ-አንባሩ የጠፋ ጅልነት ነው። ራሴን ቀን መከላከል አያዳግተኝም፤ መሮጥ፣ ማምለጥ፣ ዞር ማለት እችላለሁ። ግን ሳንቀላፋ ምን ማድረግ ይቻለኝ ይሆን?' አላለም፤ አልጠየቀም አሁን። ዝም ብሎ ተረዳ። 'ሒደቱ ላይገባኝ ይችላል ቢሆንም እነዛ የቀን ዱላዎች ብዙ ትሩፋት ስለነበራቸው ነው ይሄን ልውጠት (transformation) በኔ ላይ ያመጡት። ካለምንም ጥያቄ ይሄንንም እቀበለዋለሁ' አለ።
መምህሩም "ይሄ ጥሩ ምልክት ነው። ለመጀመሪያ ጊዜ እምነት ጥለህ ጥያቄ አላነሳህም። ሁለት ወይም ሶስት ወራት ሲደበደብ ገላው በየቀኑ ቁስል ቢሰማውም አንድ ዕለት ሆነለት፤ በፅልመት ራሱን መከላከል ቻለ። መምህሩም እክፍሉ ሲዘልቁ "ተረጋጉ…ነቅቻለሁ" አላቸው። እንደዚሁ ደጋግሞም ተከሰተ።
🔷 ወጣቱን መነረት የሚቻል አልሆነም። መምህሩ እክፍሉ እንደጠለቁ፣ ፈጽሞ የማይተኛ ይመስል አይኖቹ ፈጠዋል። ግን እንደዛ አልነበረም፤ ወጣቱ ሲያሸልብ በጣም ችኩል ነበር። ሆኖም እውስጥ እንደቀንዲል የበራች ትንሽ የበረዶ ግግር ጫፍ የመሰለች አለላ ንቃት ለቅኝት (watching)፣ ለጥበቃ (waiting) ከሽልብታ ዓለም አምልጣ ወጥታ ስለነበረ ነው ቀድማ ምታባንነው።
📍መምህሩ ተደሰቱ። በበነጋው ማለዳ መምህሩ ከአንድ ዛፍ ስር አርፈው ጥንታዊ መጻሕፍ ያነባሉ። ወጣቱ ያትክልት ሥፍራውን እያጸዳ 'ይሄ ሽማግሌ ለዓመት ያህል ጠዋት፣ ማታ ሲነርተኝ ነበር። እሱን አንዴ ብቻ ብደልቀው እንዴት ይሆናል? ባየው ደስ ይለኛል እንዴት እንደሚሆን?' የሚል ሐሳብ ብልጭ አለበት።
መምህሩም በዛው ቅፅበት መጻሕፉን ከደኑና "አንተ ቂል! ይሄ ከንቱ ሐሳብ ይቅርብህ፤ እኔ ለራሴ አቅመ ደካማ ነኝ" ብለው ለወጣቱ መለሱለት ....
❤️ውብ አሁን ለሁላችን😊
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✍ @EthioHumanityBot