💡ቀስ እያለ ነጋ!
🔷አንዳንድ ቀን በጣም ከባድ ነው ሁሉም ነገር ይሰለቻል ከአልጋ ላይ ራሱ መነሳት ያስጠላል በጣም ደክሞኛል ስትል እንኳን ምን ለማለት ፈልገህ እንደሆነ ማንም አይረዳህም
በቃ............... ሁሉም ነገር ጭልምልም ይልብሀል ምን መስራት እንዳለብህ የት መሄድ እንዳለብህ ራሱ ግራ ይገባሀል ያስደስትህ የነበረዉ ሁሉ ያስጠላሀል በቃ መሀል ላይ ራስህን ታጣዋለህ፣ ሕይወት እንደ ደራሽ ማዕበል ይሆንብሃል፡፡ በሰላም ይሄዱ የነበሩ ነገሮች ልክ የተመካከሩ ይመስል በአንድ ላይ ይናጋሉ፡፡ የሁኔታዎች አልሳካ ማለት፣ ድንገተኛ ወጪዎች፣ የጉዳዮች መጥመም፣ የሰዎች ክህደት፣ስጋትን የሚፈጥሩ ሁኔታዎች መከሰት፣ ልክ እንደ ማዕበል በአንድ ላይ ይመጣሉ፡፡
💎ህይወት ሁሌ ሙሉ አይደለችም ፣ ማጣት ማግኘት መደሰት ማዘን መጫወት መከፋት ማዉራት ዝም ማለት መሳቅ ማልቀስ ብዙ ብዙ ነገር ይገጥመናል ሰው ይፈተንበት ዘንድ የተሰጠው ፈተና ሺ ነው፡፡ እስትንፋሱ እስካለች ድረስ ፈተናው አያልቅም፡፡ ተረጋጋሁ ሲል የሚረበሽ፤አረፍኩ ሲል እንከን የማያጣው ጥቂት አይደለም፡፡
📍ጥያቄው ግን እኛ ሰዎች በጎ በጎዉን ትተን መጥፎው ላይ ብቻ ለምን እንከርማለን ነው??
አንድ እውነታ የሚመሰረተው እውነታ ካልሆነው ነገር ጋር ተነፃፅሮ ነው። ካልሆነ ግን እውነት ሚባል ስያሜም አይኖረውም። ጥሩ መጥፎ ከሌለ ሊኖር አይችልም። ጥንካሬ ድክመት ካሌለ ሊታወቅ አይችልም።ስለዚህም መከራን አትጥላው። የመከራ ዘር በውስጡ የማንነት እድገትን ይዟልና። ያሰብከው እና ያገኘህው ነገር ሊለያይ ይችላል። ነገር ግን የቱም ሁኔታ ትምህርትን ይዞ ይመጣል፣ የምንኖረው በአንፃራዊ አለም ውስጥ ነውና።
💡ለማንም ሰው ህይወት ስህተት ወይም ትክክል መሆኑን የሚያውቀው ሲፈተን ነው። ጫጩት ለማግኘት የእንቁላሉ ቅርፊት ማስወገድ ሽፋኑን መግለጥ ያስፈልጋል፣ ወርቅ የሚወጣው ከጭቃ ውስጥ ነው። ዝናብ ሊዘንብ ሲል ነጎድጓድና የመብረቅ ብልጭታ ቀድመው መታየት ይጀምራሉ። ሌቱ ሊነጋጋ ሲል በጣም ይጨልማል። ከከባድ ምጥ በኋላ ልጅ ይወለዳል። ይህ የተለመደ የሕይወት አካል የሆነ ክስተት በእኛም ላይ ሲደርስ መረጋጋት ወሳኝ ነው፡፡
እናም ወዳጄ
🔑ህይወት ሁሌም ለማንም የትም ሙሉ አይደለችም፡፡ ቀን አለና ቀና በል፣ አስብ ባሰብከው ሀሳብ ተፅናና በተፅናናህበትም ቃል ሌሎችን አፅናና!! በሕይወት ሩጫዎችህ መሀል ያለውን ውስብስብ የሕይወት ገፅ ጠንቅቀው የሚያውቁት ጥቂቶች ናቸው። ስለሆነም ባልተረዱህ ብዙ ሰዎች እየተናደድክ ሳይሆን በተገነዘቡህ ጥቂት ሰዎች እየተደሰትክ ኑር። አልሞላ ያለው ነገር ሁሉ ፈጣሪ በራሱ ግዜ አስተካክሎ ጨምሮ ያመጣዋል ።
ዛሬን ባለህ ነገር አመስግነህ ደስ ብሎህ ኑር። ባለህ የማትረካ ከሆንክ ሩጫህ ሁሌ ሌላ ነገር ፍለጋ ብቻ የሆናል፡፡ የሌለህን ነገር ብቻ ካሰብክ በማማረርህ ውስጥ ያለህንም ታጣዋለህ፡፡ ያለህን ነገር ካሰብክ ግን በምስጋናህ ውስጥ የሌለህንም ታገኘዋለህ፡፡
ውብ አሁን❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✍ @EthioHumanityBot
🔷አንዳንድ ቀን በጣም ከባድ ነው ሁሉም ነገር ይሰለቻል ከአልጋ ላይ ራሱ መነሳት ያስጠላል በጣም ደክሞኛል ስትል እንኳን ምን ለማለት ፈልገህ እንደሆነ ማንም አይረዳህም
በቃ............... ሁሉም ነገር ጭልምልም ይልብሀል ምን መስራት እንዳለብህ የት መሄድ እንዳለብህ ራሱ ግራ ይገባሀል ያስደስትህ የነበረዉ ሁሉ ያስጠላሀል በቃ መሀል ላይ ራስህን ታጣዋለህ፣ ሕይወት እንደ ደራሽ ማዕበል ይሆንብሃል፡፡ በሰላም ይሄዱ የነበሩ ነገሮች ልክ የተመካከሩ ይመስል በአንድ ላይ ይናጋሉ፡፡ የሁኔታዎች አልሳካ ማለት፣ ድንገተኛ ወጪዎች፣ የጉዳዮች መጥመም፣ የሰዎች ክህደት፣ስጋትን የሚፈጥሩ ሁኔታዎች መከሰት፣ ልክ እንደ ማዕበል በአንድ ላይ ይመጣሉ፡፡
💎ህይወት ሁሌ ሙሉ አይደለችም ፣ ማጣት ማግኘት መደሰት ማዘን መጫወት መከፋት ማዉራት ዝም ማለት መሳቅ ማልቀስ ብዙ ብዙ ነገር ይገጥመናል ሰው ይፈተንበት ዘንድ የተሰጠው ፈተና ሺ ነው፡፡ እስትንፋሱ እስካለች ድረስ ፈተናው አያልቅም፡፡ ተረጋጋሁ ሲል የሚረበሽ፤አረፍኩ ሲል እንከን የማያጣው ጥቂት አይደለም፡፡
📍ጥያቄው ግን እኛ ሰዎች በጎ በጎዉን ትተን መጥፎው ላይ ብቻ ለምን እንከርማለን ነው??
አንድ እውነታ የሚመሰረተው እውነታ ካልሆነው ነገር ጋር ተነፃፅሮ ነው። ካልሆነ ግን እውነት ሚባል ስያሜም አይኖረውም። ጥሩ መጥፎ ከሌለ ሊኖር አይችልም። ጥንካሬ ድክመት ካሌለ ሊታወቅ አይችልም።ስለዚህም መከራን አትጥላው። የመከራ ዘር በውስጡ የማንነት እድገትን ይዟልና። ያሰብከው እና ያገኘህው ነገር ሊለያይ ይችላል። ነገር ግን የቱም ሁኔታ ትምህርትን ይዞ ይመጣል፣ የምንኖረው በአንፃራዊ አለም ውስጥ ነውና።
💡ለማንም ሰው ህይወት ስህተት ወይም ትክክል መሆኑን የሚያውቀው ሲፈተን ነው። ጫጩት ለማግኘት የእንቁላሉ ቅርፊት ማስወገድ ሽፋኑን መግለጥ ያስፈልጋል፣ ወርቅ የሚወጣው ከጭቃ ውስጥ ነው። ዝናብ ሊዘንብ ሲል ነጎድጓድና የመብረቅ ብልጭታ ቀድመው መታየት ይጀምራሉ። ሌቱ ሊነጋጋ ሲል በጣም ይጨልማል። ከከባድ ምጥ በኋላ ልጅ ይወለዳል። ይህ የተለመደ የሕይወት አካል የሆነ ክስተት በእኛም ላይ ሲደርስ መረጋጋት ወሳኝ ነው፡፡
እናም ወዳጄ
🔑ህይወት ሁሌም ለማንም የትም ሙሉ አይደለችም፡፡ ቀን አለና ቀና በል፣ አስብ ባሰብከው ሀሳብ ተፅናና በተፅናናህበትም ቃል ሌሎችን አፅናና!! በሕይወት ሩጫዎችህ መሀል ያለውን ውስብስብ የሕይወት ገፅ ጠንቅቀው የሚያውቁት ጥቂቶች ናቸው። ስለሆነም ባልተረዱህ ብዙ ሰዎች እየተናደድክ ሳይሆን በተገነዘቡህ ጥቂት ሰዎች እየተደሰትክ ኑር። አልሞላ ያለው ነገር ሁሉ ፈጣሪ በራሱ ግዜ አስተካክሎ ጨምሮ ያመጣዋል ።
ዛሬን ባለህ ነገር አመስግነህ ደስ ብሎህ ኑር። ባለህ የማትረካ ከሆንክ ሩጫህ ሁሌ ሌላ ነገር ፍለጋ ብቻ የሆናል፡፡ የሌለህን ነገር ብቻ ካሰብክ በማማረርህ ውስጥ ያለህንም ታጣዋለህ፡፡ ያለህን ነገር ካሰብክ ግን በምስጋናህ ውስጥ የሌለህንም ታገኘዋለህ፡፡
ውብ አሁን❤️
@EthioHumanity
@EthioHumanity
✍ @EthioHumanityBot