ውድ ደንበኞቻችን
በቀይ ባህር ውስጥ በሚያልፍ ከፍተኛ ባንድዊድዝ ተሸካሚ ዓለም አቀፍ ባህር ጠለቅ የኢንተርኔት መገናኛ መስመር ላይ ባጋጠመ መቋረጥ ምክንያት የኢንተርኔት አገልግሎታችን በሌሎች አማራጭ መስመሮች ብቻ እየሰራ በመሆኑ ሰሞኑን የኢንተርኔት አገልግሎት ፍጥነት መቀነስ እና መቆራረጥ እያጋጠመ ይገኛል።
ክቡራን ደንበኞቻችን አገልግሎቱን በፍጥነት ለማስቀጠል ከአገልግሎት አቅራቢዎቹ ጋር ከፍተኛ ጥረት በማድረግ ላይ በመሆናችን በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እየጠየቅን፤ ለአገልግሎት መስተጓጎሉ ይቅርታ እንጠይቃለን።