እንደ ድንግልና ሁሉ በጋብቻም “አታመንዝር» የሚለው ሕግ ይጠበቃል እንጂ አይፈርስም። ስለዚህ እስከ ጋብቻ በንጽሕና ተጠብቆ ከሚኖርበት የድንግልና ሕግ ወደ ጥንድነት የሚተላለፉበት ጋብቻም ሕግ›› ይባላል፡፡ ብዙ መንፈሳዊ መጻሕፍት ባለትዳር ወይም ያገባ ለማለት «ሕጋዊ» የሚሉት በዚህ ምክንያት ነው::
ሐ. ድንጋሌ ሥጋ ዓይን ይባላል ወይም በ«ዓይን›› ይመስላል:: ለዚህም ምስክሩ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ «መሀሮሙ ለደናግል ለእለ እያውሰቡ ከመ ይዕቀቡ ድንግልናሆሙ ከመ ብንተ ዓይን›› በማለት የተናገረው ቃል ነው:: ይህም ወደ አማርኛ ሲተረጎም
«ድንግልናቸውን እንደ ዓይን ብሌን ይጠብቁ ዘንድ ላላገቡ ደናግል ምክራቸው፣ አስተምራቸው፡፡>>ማለት ነው:: ድንግልና ለምን «ዓይን› እንደ ተባለ የሚያውቅ ማን ነው? ድንግልና የአንድን ሰው ማንነት እስከ መወሰን ወይም ገልጦ እስከ ማሳየት የሚደርስ መሠረታዊ ምሥጢር እንድትይዝ ሆና በመፈጠሯ አይደለምን? ዓይን ታያለች እርሷም ትታያለች፡፡ አንቺ ሴት ከጋብቻሽ በፊት ድንግልናሽን ያጠፋሽው ከሆነ ስታገቢ ባልሽን በምን ታይዋለሽ? ድንግልና «ዓይን› ተብላለችና፡፡ ባልም ቢሆን ድንግልናውን ጠብቆ ካልኖረ ረቂቅ መነጽር (ድንግልና) የለውምና ሚስቱን በምኑ ያያታል ? ዛሬ ዛሬ ብዙ ባልና ሚስቶች በጥቃቅን አለመግባባቶች ለአንድ ቀን እንኳን ተያይተው የማያውቁ ያህል የሚሆኑትና የሚኳረፉት ምናልባት ድንግልናን መጠበቅ ስለ ቀረ ይሆን? በማለት መጠየቅ አስተዋይነት ነው፡፡ ምክንያቱም ድንግልና ባልና ሚስት በተለየ መልኩ የሚተያዩበት የማይመረመር «ዓይን»ነውና፡፡
ድንግልና ሁሉን አርቆ የሚያሳይ ከፍተኛ ቦታ ነው:: የኑሮ ደረጃቸውን በድንግልና ሆነው መርምረውና ተመልክተው ያገቡ ሰዎች አይጸጸቱም: ማለትም አንድ ስው ደረጃው ማግባትም ይሁን መመንኮስ በሚገባ ለይቶ ማወቅ የሚችለው ንጽሕናውን ጠብቆ ለመኖር ከቻለ ብቻ ነው:: ድንግልና የንጽሕናን ቅባት የተኳለ አጥርቶ የሚመለከት የሰውነት መብራት ነውና፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ «የሰውነት መብራት ዓይን ናት፡፡ እንግዲህ ዓይንህ ጤናማ ብትሆን ሰውነትህ ሁሉ ብሩህ ይሆናል፡፡ ዓይንህ ግን ታማሚ ብትሆን ሰውነትህ : ሁሉ የጨለመ ይሆናል» ይላል:: ማቴ6፡22-23 እንደዚሁም ሁሉ በዓይን የተመሰለች ድንግልናም በሕገ ወጥነት በዝሙት ሥሪ ከጠፋች አንድ ሰው ሰውነቱ ሁሉ እንደጨለመበት ለያምን ይገባዋል፡፡ ምክንያቱም ድንግልና ሃይማኖትና ምግባር መሠረታቸውን ለቀው እንዳይናጉ የሚያደርግ ጽኑ መሠረት ነውና፡፡ ማለትም አመለካከት፣ አነጋገርና አሠራር ሚዛናቸውን እንዳልሳቱ ከድንግልና አጠባበቅ አንጻር መናገር ይቻላል፡፡ ስለዚህ ድንግልና «ዓይን› ቢባል ያንሰዋል እንጂ አይበዛበትም፡፡
ብዙ ጊዜ ደንግልና ለሴቶች የሚነገረው በጉልህ ምልክት የሚታወቀው በእነርሱ ስለሆነ ነው:: ነገር ግን ድንግልና ለወንዶችም ተጠቃሽ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ «ከሴቶች ጋር ያልረከሱ እነዚህ ናቸው፣ ድንግሎች ናቸው::» በማለት ከትቦ ይዟል:: ራእይ14፥4 በመሆኑም ድንግልናን የመጠበቅ ጥቅምም ሆነ ያለ መጠበቅ ጉዳት በማስተዋል ለተመለከተው በወንድም ሆነ በሴት በኩል ያለው ፋይዳ ተመጣጣኝ ነው:: ስለዚህ በዚህ ርእስ ሥር በጎላው ለመናገር ሴቶች ይጠቀሱ እንጂ ልዩ ማመልክቻ እስክ ሌለ ድረስ የሚወሳው ሁሉ ወንዶችንም ያጠቃልላል፡፡
የድንግልና ዓይነቶች
ድንግልናን በሁለት ወገን ከፍሎ ማየት ይቻላል፡፡ በሁለት ወገን ድንግል መሆኗን ለመግለጽ ስለ እመቤታችን ስለ ድንግል ማርያም ‹‹ድንግል በክልኤ» ተብሎ የተነገረው ቃል ለእክፋፈሉ በዋቢነት ይጠቀሳል::
የመጀመሪያው የድንግልና ዓይነት ድንጋሌ ሥጋ ሲሆን ሁለተኛው ዓይነት ደግሞ ድንጋሌ ነፍስ ነው፡፡ ድንጋሌ ነፍስ በሌላ መንገድ ድንጋሌ ሕሊና ይባላል። «ድንግል በሕሊናኪ ወድንግል በሥጋኪ» * «በሐሳብሽ ድንግል ነሽ በሥጋሽም ድንግል ነሽ› እንዲል፡፡ (ጸሎተ በሰላመ ገብርኤል መልአክ)
ድንጋሌ ሥጋ ለድንጋሌ ነፍስ መገለጫ፣ ጥላ ወይም አምሳል ነው:: ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ «እስመ ድንጋሌ ሥጋስ አርአያ ወጽላሎት ለእንታክቲ» ብሏልና፡፡ በእውነት «ድንግልና» የምትባለው ግን ድንጋሌ ነፍስ ናት፡፡ ለዚህም ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ «ወባሕቱ ድንግልናስ አማናዊት ድንጋሌ ነፍስ ይእቲ» በማለት አስረጅ የሚሆን ቃል ተናግሯል፡፡ «ነገር ግን አማናዊት ድንግልና የምትባለው ድንጋሌ ነፍስ ናት» ማለት ነው:: ዮሐ.ተግ28 ከላይ እንደ ተጠቀሰው ድንጋሌ ሥጋ በግዘፍ የሚታይ በገሢሥ የሚታወቅ ሲሆን ድንግሌ ነፍስ ግን ረቂቅ ነው፡፡
ነፍስ ግን ድንግልናዋ በብዙ ጐዳና ነው፡፡ ከቅጥነተ ድንግልናዋ (ከድንግልናዋ ረቂቅነት የተነሣሣ) አንድ ጊዜ በኃጢአት ተግባርና ሐሳብ የተወሰደባት ድንግልና በንስሐ ይመለስላታል:: ስለዚህ ድንጋሌ ነፍስ በኃጢአት ይወገዳል በንስሐ ደግሞ ይመለሳል ማለት ነው፡፡
የነፍስን ድንግልና የሚያጠፋው የኃጢአት ሥራና ሐሳብ ብቻ ነው:: ኃጢአት ካልሆነ በቀር የሥጋን ድንግልና እስክ ማጥፋት የደረሰ ጽኑ ተግባር እንኳን ቢሆን የነፍስን ድንግልና ሊያጠፋ አይችልም፡፡ ለምሳሌ፦ በቅዱስ ጋብቻ የተወሰኑ ባልና ሚስት በሚፈጽሙት ሩካቤ. ድንጋሌ ሥጋቸው ሲጠፋ የነፍስ ድንግልናቸው ግን አይወገድም። ምክንያቱም ሕጋዊ ባለትዳሮች ሩካቢያቸው ኃጢአት ባለመሆኑ ነው:: ይህን ሲያስረዳ ቅዱስ ዮሐንስ እፈ ወርቅ እንዲህ ብሏል:- «ወሶበኒ ባቲ ምት ድንግልት ይእቲ ተደንግሎ መንክረ» ይህም ማለት ባልም ብታገባ ድንቅ በሚሆን ድንጋሌ ነፍስ ድንግል ናት ማለት ነው፡፡ ዮሐ.ተግ.28
በተጨማሪም ከላይ የተጠቀሰውን ሐሳብ በሌላ አገባብ ብንመለከተው ይኽን ሐቅ እንረዳለን፡፡ ክህነትን አጽንቶ ዲያቆን ሆኖ ለመኖር ድንግልናን መጠበቅ ግድ መሆኑ ለማንም የተሠወረ አይደለም፡፡ ስለዚህ አንድ ዲያቆን ሕገ ወጥ በሆነ መንገድ ድንጋሌ ሥጋውን ሲያፈርስ ክህነቱን እያፈረሰ መሆኑ ግልጽ ነው:: ነገር ግን በተገቢ መንገድ ጋብቻ ፈጽሞ ሩካቤ በማድረጉ ምክንያት ድንጋሌ ሥጋውን ሲያጣ ክህነቱን ግን አያጣም:: ምክንያቱም ሕጋዊ ሩካቤ የነፍስን ድንግልና ስለማያጠፋና ስለማያረክስ ነው፡፡
ድንጋሌ ነፍስ የሌለው ሰው የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርስም:: ይህም ማለት የነፍስን ድንግልና የሚያጠፋው ኃጢአት ብቻ በመሆኑ ኃጢአቱን በንስሐ ያላራቀ ወይም ንስሐ ያልገባ ሰው ወደ መንግሥተ ሰማያት አይገባም ማለት ነው፡፡ ዮሐንስ ወንጌላዊ በራእይ መጽሐፉ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት የሚችሉት የነፍስ ድንግልና ያላቸው ብቻ መሆናቸውን ሲገልጽ:- «ከሴቶች ጋር ያልረከሱ እነዚህ ናቸው ድንግሎች ናቸውና፡፡ በጉ ወደሚሄድበት የሚከተሉ እነዚህ ናቸው፡፡ ለእግዚአብሔርና ለበጉ በኩራት እንዲሆኑ ክሰዎች የተዋጁ አነዚህ ናቸው::› ይላል፡፡ ራእይ14፥4
በተጨማሪም ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ድንጋሌ ነፍስ ወደ መንግሥተ ሰማያት ለመግባት ዋና ነገር መሆኑን ሲናገር እንዲህ ብሏል፦ «እስመ ድንጋሌ ነፍስ ይሬሲ ሱታፌ ምስለ ክርስቶስ ወያበውእ ውስተ መንግሥተ ሰማያት» ይህም በአማርኛ «ድንጋሌ ነፍስ ከመርዓዊ (ከሙሽራ) ክርስቶስ ጋራ አንድ ያደርጋል:: ወደ መንግሥተ ሰማያትም ያገባልና» ማለት ነው:: ዮሐ.ተግ.2
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox
ሐ. ድንጋሌ ሥጋ ዓይን ይባላል ወይም በ«ዓይን›› ይመስላል:: ለዚህም ምስክሩ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ «መሀሮሙ ለደናግል ለእለ እያውሰቡ ከመ ይዕቀቡ ድንግልናሆሙ ከመ ብንተ ዓይን›› በማለት የተናገረው ቃል ነው:: ይህም ወደ አማርኛ ሲተረጎም
«ድንግልናቸውን እንደ ዓይን ብሌን ይጠብቁ ዘንድ ላላገቡ ደናግል ምክራቸው፣ አስተምራቸው፡፡>>ማለት ነው:: ድንግልና ለምን «ዓይን› እንደ ተባለ የሚያውቅ ማን ነው? ድንግልና የአንድን ሰው ማንነት እስከ መወሰን ወይም ገልጦ እስከ ማሳየት የሚደርስ መሠረታዊ ምሥጢር እንድትይዝ ሆና በመፈጠሯ አይደለምን? ዓይን ታያለች እርሷም ትታያለች፡፡ አንቺ ሴት ከጋብቻሽ በፊት ድንግልናሽን ያጠፋሽው ከሆነ ስታገቢ ባልሽን በምን ታይዋለሽ? ድንግልና «ዓይን› ተብላለችና፡፡ ባልም ቢሆን ድንግልናውን ጠብቆ ካልኖረ ረቂቅ መነጽር (ድንግልና) የለውምና ሚስቱን በምኑ ያያታል ? ዛሬ ዛሬ ብዙ ባልና ሚስቶች በጥቃቅን አለመግባባቶች ለአንድ ቀን እንኳን ተያይተው የማያውቁ ያህል የሚሆኑትና የሚኳረፉት ምናልባት ድንግልናን መጠበቅ ስለ ቀረ ይሆን? በማለት መጠየቅ አስተዋይነት ነው፡፡ ምክንያቱም ድንግልና ባልና ሚስት በተለየ መልኩ የሚተያዩበት የማይመረመር «ዓይን»ነውና፡፡
ድንግልና ሁሉን አርቆ የሚያሳይ ከፍተኛ ቦታ ነው:: የኑሮ ደረጃቸውን በድንግልና ሆነው መርምረውና ተመልክተው ያገቡ ሰዎች አይጸጸቱም: ማለትም አንድ ስው ደረጃው ማግባትም ይሁን መመንኮስ በሚገባ ለይቶ ማወቅ የሚችለው ንጽሕናውን ጠብቆ ለመኖር ከቻለ ብቻ ነው:: ድንግልና የንጽሕናን ቅባት የተኳለ አጥርቶ የሚመለከት የሰውነት መብራት ነውና፡፡
መጽሐፍ ቅዱስ «የሰውነት መብራት ዓይን ናት፡፡ እንግዲህ ዓይንህ ጤናማ ብትሆን ሰውነትህ ሁሉ ብሩህ ይሆናል፡፡ ዓይንህ ግን ታማሚ ብትሆን ሰውነትህ : ሁሉ የጨለመ ይሆናል» ይላል:: ማቴ6፡22-23 እንደዚሁም ሁሉ በዓይን የተመሰለች ድንግልናም በሕገ ወጥነት በዝሙት ሥሪ ከጠፋች አንድ ሰው ሰውነቱ ሁሉ እንደጨለመበት ለያምን ይገባዋል፡፡ ምክንያቱም ድንግልና ሃይማኖትና ምግባር መሠረታቸውን ለቀው እንዳይናጉ የሚያደርግ ጽኑ መሠረት ነውና፡፡ ማለትም አመለካከት፣ አነጋገርና አሠራር ሚዛናቸውን እንዳልሳቱ ከድንግልና አጠባበቅ አንጻር መናገር ይቻላል፡፡ ስለዚህ ድንግልና «ዓይን› ቢባል ያንሰዋል እንጂ አይበዛበትም፡፡
ብዙ ጊዜ ደንግልና ለሴቶች የሚነገረው በጉልህ ምልክት የሚታወቀው በእነርሱ ስለሆነ ነው:: ነገር ግን ድንግልና ለወንዶችም ተጠቃሽ መሆኑን መጽሐፍ ቅዱስ «ከሴቶች ጋር ያልረከሱ እነዚህ ናቸው፣ ድንግሎች ናቸው::» በማለት ከትቦ ይዟል:: ራእይ14፥4 በመሆኑም ድንግልናን የመጠበቅ ጥቅምም ሆነ ያለ መጠበቅ ጉዳት በማስተዋል ለተመለከተው በወንድም ሆነ በሴት በኩል ያለው ፋይዳ ተመጣጣኝ ነው:: ስለዚህ በዚህ ርእስ ሥር በጎላው ለመናገር ሴቶች ይጠቀሱ እንጂ ልዩ ማመልክቻ እስክ ሌለ ድረስ የሚወሳው ሁሉ ወንዶችንም ያጠቃልላል፡፡
የድንግልና ዓይነቶች
ድንግልናን በሁለት ወገን ከፍሎ ማየት ይቻላል፡፡ በሁለት ወገን ድንግል መሆኗን ለመግለጽ ስለ እመቤታችን ስለ ድንግል ማርያም ‹‹ድንግል በክልኤ» ተብሎ የተነገረው ቃል ለእክፋፈሉ በዋቢነት ይጠቀሳል::
የመጀመሪያው የድንግልና ዓይነት ድንጋሌ ሥጋ ሲሆን ሁለተኛው ዓይነት ደግሞ ድንጋሌ ነፍስ ነው፡፡ ድንጋሌ ነፍስ በሌላ መንገድ ድንጋሌ ሕሊና ይባላል። «ድንግል በሕሊናኪ ወድንግል በሥጋኪ» * «በሐሳብሽ ድንግል ነሽ በሥጋሽም ድንግል ነሽ› እንዲል፡፡ (ጸሎተ በሰላመ ገብርኤል መልአክ)
ድንጋሌ ሥጋ ለድንጋሌ ነፍስ መገለጫ፣ ጥላ ወይም አምሳል ነው:: ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ «እስመ ድንጋሌ ሥጋስ አርአያ ወጽላሎት ለእንታክቲ» ብሏልና፡፡ በእውነት «ድንግልና» የምትባለው ግን ድንጋሌ ነፍስ ናት፡፡ ለዚህም ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ «ወባሕቱ ድንግልናስ አማናዊት ድንጋሌ ነፍስ ይእቲ» በማለት አስረጅ የሚሆን ቃል ተናግሯል፡፡ «ነገር ግን አማናዊት ድንግልና የምትባለው ድንጋሌ ነፍስ ናት» ማለት ነው:: ዮሐ.ተግ28 ከላይ እንደ ተጠቀሰው ድንጋሌ ሥጋ በግዘፍ የሚታይ በገሢሥ የሚታወቅ ሲሆን ድንግሌ ነፍስ ግን ረቂቅ ነው፡፡
ነፍስ ግን ድንግልናዋ በብዙ ጐዳና ነው፡፡ ከቅጥነተ ድንግልናዋ (ከድንግልናዋ ረቂቅነት የተነሣሣ) አንድ ጊዜ በኃጢአት ተግባርና ሐሳብ የተወሰደባት ድንግልና በንስሐ ይመለስላታል:: ስለዚህ ድንጋሌ ነፍስ በኃጢአት ይወገዳል በንስሐ ደግሞ ይመለሳል ማለት ነው፡፡
የነፍስን ድንግልና የሚያጠፋው የኃጢአት ሥራና ሐሳብ ብቻ ነው:: ኃጢአት ካልሆነ በቀር የሥጋን ድንግልና እስክ ማጥፋት የደረሰ ጽኑ ተግባር እንኳን ቢሆን የነፍስን ድንግልና ሊያጠፋ አይችልም፡፡ ለምሳሌ፦ በቅዱስ ጋብቻ የተወሰኑ ባልና ሚስት በሚፈጽሙት ሩካቤ. ድንጋሌ ሥጋቸው ሲጠፋ የነፍስ ድንግልናቸው ግን አይወገድም። ምክንያቱም ሕጋዊ ባለትዳሮች ሩካቢያቸው ኃጢአት ባለመሆኑ ነው:: ይህን ሲያስረዳ ቅዱስ ዮሐንስ እፈ ወርቅ እንዲህ ብሏል:- «ወሶበኒ ባቲ ምት ድንግልት ይእቲ ተደንግሎ መንክረ» ይህም ማለት ባልም ብታገባ ድንቅ በሚሆን ድንጋሌ ነፍስ ድንግል ናት ማለት ነው፡፡ ዮሐ.ተግ.28
በተጨማሪም ከላይ የተጠቀሰውን ሐሳብ በሌላ አገባብ ብንመለከተው ይኽን ሐቅ እንረዳለን፡፡ ክህነትን አጽንቶ ዲያቆን ሆኖ ለመኖር ድንግልናን መጠበቅ ግድ መሆኑ ለማንም የተሠወረ አይደለም፡፡ ስለዚህ አንድ ዲያቆን ሕገ ወጥ በሆነ መንገድ ድንጋሌ ሥጋውን ሲያፈርስ ክህነቱን እያፈረሰ መሆኑ ግልጽ ነው:: ነገር ግን በተገቢ መንገድ ጋብቻ ፈጽሞ ሩካቤ በማድረጉ ምክንያት ድንጋሌ ሥጋውን ሲያጣ ክህነቱን ግን አያጣም:: ምክንያቱም ሕጋዊ ሩካቤ የነፍስን ድንግልና ስለማያጠፋና ስለማያረክስ ነው፡፡
ድንጋሌ ነፍስ የሌለው ሰው የእግዚአብሔርን መንግሥት አይወርስም:: ይህም ማለት የነፍስን ድንግልና የሚያጠፋው ኃጢአት ብቻ በመሆኑ ኃጢአቱን በንስሐ ያላራቀ ወይም ንስሐ ያልገባ ሰው ወደ መንግሥተ ሰማያት አይገባም ማለት ነው፡፡ ዮሐንስ ወንጌላዊ በራእይ መጽሐፉ ወደ እግዚአብሔር መንግሥት መግባት የሚችሉት የነፍስ ድንግልና ያላቸው ብቻ መሆናቸውን ሲገልጽ:- «ከሴቶች ጋር ያልረከሱ እነዚህ ናቸው ድንግሎች ናቸውና፡፡ በጉ ወደሚሄድበት የሚከተሉ እነዚህ ናቸው፡፡ ለእግዚአብሔርና ለበጉ በኩራት እንዲሆኑ ክሰዎች የተዋጁ አነዚህ ናቸው::› ይላል፡፡ ራእይ14፥4
በተጨማሪም ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ድንጋሌ ነፍስ ወደ መንግሥተ ሰማያት ለመግባት ዋና ነገር መሆኑን ሲናገር እንዲህ ብሏል፦ «እስመ ድንጋሌ ነፍስ ይሬሲ ሱታፌ ምስለ ክርስቶስ ወያበውእ ውስተ መንግሥተ ሰማያት» ይህም በአማርኛ «ድንጋሌ ነፍስ ከመርዓዊ (ከሙሽራ) ክርስቶስ ጋራ አንድ ያደርጋል:: ወደ መንግሥተ ሰማያትም ያገባልና» ማለት ነው:: ዮሐ.ተግ.2
@Ethiopian_Orthodox
@Ethiopian_Orthodox