«ድንግል በክልኤ»
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም «ድንግል በክልኤ» እየተባለ በቅዱሳት መጻሕፍት ተነግሮላታል፡፡ ስለ ድንግልናዋ ትንቢት ተነግሯል ምሳሌም ተመስሏል:: ይህም በሁለት ወገን ማለትም በሥጋና በነፍስ ድንግል መሆኗን ለማመልከት ነው:: የደናግልም ሁሉ መመኪያቸው እርሷ ናት፡፡
እመቤታችን ቅድመ ፀኒስ፣ ጊዜ ፀኒስ፣ ድኅረ ፀኒስ ድንግል ናት:: ቅድመ ወሊድ፣ ጊዜ ወሊድ፣ ድኅረ ወሊድም ድንግል ናት፡፡ ቅዱሳንን ሁሉ ስለ ድንግልኗ ምስጋናና ክብር ያለ ማቋረጥ እንዲናገሩ ያደረገ ይህ ንጽሕናዋ ነው፡፡ ‹‹ስብሐተ ድንግልናኪ ወትረ ይነግር አፉየ› እንዲል:: (መልክዐ ማርያም)
የእመቤታችንን ድንግልና «ድንግልና» በመባሉ ብቻ ካልሆነ በቀር የፍጡራን ድንግልና በምንም አይመሳሰለውም፡፡ ስለ እመቤታችን ድንግልና ለመናገር ሌላ ትልቅ ጥራዝ ያለው መጽሐፍ መጻፍ ያስፈልጋል:: ስለድንግልና ለመናገር ስንፈልግ ስለ እርስዋ ከተጻፉት መንፈሳዊ ድርሰቶች አስረጅ አድርገን ብዙ ብንጠቅስም በድንግልና ፍጽምት ከመሆኗ የተነሣ የፍጡራንን ድንግልና ሕጹጽነት ለማየት እንዲረዳን ነው እንጂ ለማመሳሰል አይደለም፡፡
የእመቤታችንን ድንግልና የመላእክትም ንጽሕና አይደርስበትም፡፡ ለዚህም ማስረጃው የተአምረ ማርያም መቅድም እንዲህ ሲል ያሰፈረው ቃል ነው:: «ለመኑ ተውህቦ ተደንግሎ እለ እምውሉደ ሰብእ፣ ለመላእክትኒ ኢተክህሎሙ ተደንግሎ ሕሊና እስመ አበሱ በፍትወት ወወረዱ ምድረ በመዋዕል ዘቀዳሚ» በአማርኛ «ሥጋዊ ምኞትን የማሸነፍ ዕድል ለማን ተሰጠው? ኃጢአትን ከማሰብ መጠበቅ ለመላእክት እንኳን አልተቻላቸውም፤ በቀደመው ዘመን ያልተሰጣቸውን ሽተው በፈጸሙት በደል ከሰማይ ወደ ምድር ወርደዋልና።» (መቅድመ ተአምረ ማርያም)
ደናግላንና አለባበሳቸው!
ለዐቅመ ሔዋን የደረሱና ያልደረሱ፣ ደናግላን የሆኑና ያልሆኑ ሴቶች ተለይተው የሚታወቁበት የፀጉር አሠራር፣ አለጫጨትና የአለባበስ ሁኔታ በየሀገሩ ይገኛል:: በድሮ ጊዜ ደናግለ እስራኤል ለፍሬ -እልደረስንም ሲሉ ወርቅ እንደ አበባ የፈነዳበት ነጭ ሐር ለብሰው ይታዩ ነበር።
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ አለባበስ በሚገባ ካስተማረ በኋላ ትምህርቱ ደናግልንን ብቻ የሚመለከት ለመሰላቸው ሰዎች ‹ወአኮ ዘእቤ በእንተ ደናግል ባሕቲቶን› ማለትም «ይህን ያልኩት ስለ ደናግል ብቻ አይደለም» በማለት ደናግላን ብቻ ሳይሆኑ ሁሉም ሴቶች በሚገባ መንገድ ብቻ ማጌጥ እንዳለባቸው ይገልጻል:: ተግ.ዮሐ28
አለባበስ በዝሙት ለመውደቅ የሚዳርግበት ሁኔታ ሰፊ ስለሆነ በይበለጥ ደናግል አለባበሳቸው ተገቢ መሆን አለበት፡፡ ደናግላን የተለየ አለባበስ እንደ ነበራቸው መጽሐፍ ቅዱስም ይመሰክራል፡፡ ትዕማር ድንግል በነበረችበት ጊዜ ‹‹ብዙ ኅብር ያለውን ልብስ ለብሳ ነበር እንዲህ ያለውን ልብስ የንገሡ ልጆች ደናግሉ ይለብሱት ነበርና።» ነገር ግን በተደፈረችና ክብሯን ባጣች ጊዜ «ብዙ ኅብር ያለውን ልብስዋን ተርትሪ› እየጮኸች ሄደች:: 2ሳሙ13÷18-19
ድንጋሌ ሥጋ አንድ ጊዜ ጠፋ በኋላ ሊመለስ ይችላል?
በግዘፍ ያለ ድንጋሌ ሥጋ አንድ ብቻ ነው፡፡ ይህ ድንጋሌ ሥጋ. በሩካቤም ሆነ ያለ ሩካቤም የሚጠፋበት ጊዜ አለ፡፡ ድንጋሌ ሥጋን የሚያጠፋው ሩካቤ በመንፈሳዊው ሕግ የተደገፈ ሕጋዊ ሩካቤ ወይም ሕገ ወጥ ሩካቤ ሊሆን ይችላል:: በአጠቃላይ ድንጋሌ ሥጋ በልዩ ልዩ መንገድ ሊማስን ይችላል:: አንድ ጊዜ ጨርሶ የጠፋ ዓይን እግዚአብሔር ከሃሊነቱን ለማሳየት ሲፈቅድ ብቻ ካልሆነ በቀር ለበራ እንደማይችል ድንጋሌ ሥጋም አንድ ጊዜ ከተገሠሠ እንዲሁ ነውና አይመለስም፡፡ ድንጋሌ ሥጋ ዓይን መባሉን ከዚህ በላይ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ‹ከመ ብንተ ዓይን» ያለውን በመጥቀስ ተመልክተናል፡፡
ከላይ እንደ ተገለጸው በንስሐ ተመልሶ የሚገኘው የነፍስ ድንግልና እንጂ የሥጋ ድንግልና አይደለም፡፡ መጽሐፈ መነኮሳት «ንስሐሰ ትሬስዮ ለዘአበሰ ከመ ዘኢአበሰ ለዘማዊ ድንግለ›› ፡ «ንስሐ ግን የበደለን እንዳልበደለ ዘማዊን እንደ ድንግል ታድርገዋለች::> በማለት የተናገረው ስለ ነፍስ ድንግልና እንጂ ስለ ድንጋለ ሥጋ አይደለም፡፡ አንድ ሰው ድንጋሌ ሥጋውን አንድ ጊዜ ካጣ በኋላ እንደ ገና በንስሐ ያገኘዋል ለማለትም አይደለም:: በተጨማሪም «እንደ ድንግል» ታደርገዋለች ይላል እንጂ ቁርጥ በሆነ ቃል «ድንግል ታደርገዋለች» አለማለቱን ልብ ማለት ያስፈልጋል:: ስለዚህ ስለ ድንጋሌ ሥጋ በመጀመሪያ መጠንቀቅ እንጂ ከሄደ በኋላ «ድንግል ብሆንስ?›› ማለት አጉል ተስፋ ነው፡፡ እንዲህ ሲባል ግን የእግዚአሔርን ከሃሊነት መጠራጠር ሳይሆን ያለ አግባብ ተስፋ ማድረ ግን ለመንቀፍ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል፡፡
የንጽሕና መርከባችን እንዳይሰበር መጠንቀቅ ያሻል:: «ብርሌ ከነቃ አይሆንም ዕቃ» እንደ ተባለው ድንጋሌ ሥጋም አንድ ጊዜ ከተወሰደ እንደ ተሰበረ የሸክላ ዕቃና እንደ ሞተ ሰው ነው:: እነዚህ ተመልሰው ይረባሉ፣ ይጠቅማሉ እንደማይባሉ ድንጋሌ ሥጋም እንዲሁ ነውና ይመለሳል አይባልም:: መዝ30፥12
የኃጢአት መጥፎነቷ ይታወቅ ዘንድ ኃጢአት ከሠራን በኋላ ቢያንስ በአንድ ነገር እንቀጣለን:: ወይም አንድ ነገር እናጣለን፡፡ ዝሙት ምክንያት ድንጋሌ ሥጋ አንዴ ከተወገደ በኋላ የማይመለስበትም አንዱ ምክንያት ይህ ነው:: ንጉሥ ዳዊት ባመነዘረ ጊዜ ምንም እንኳን ንስሐ ቢገባ በዝሙት የጸነሰው ልጁ ሊፈወስለት አለመቻሉ ኃጢአት ቢያንስ በአንድ ጐዳና ሳትጐዳ እንደ ማትቀር ያመለከታል:: 2ሳሙ12፥13-14
አንዳንድ ነገሮች አንድ ጊዜ ካመለጡ በኋላ በንስሐ እንኳን መልሶ ማግኘት የማይቻልበት ሁኔታ መኖሩን ማወቅ ያስፈልጋል:: ለምሳሌ:- ዔሳው ብኩርናውን ባቃለላት ጊዜ ከሱ ወደ ታናሽ ወንድሙ ወደ ያዕቆብ ተዛውራለች:: በኋላ ግን ምንም ክልብ ቢፈልጋት መልሶ ለማግኘት አለመቻሉን ቅዱስ ጳውሎስ ሲገለጽ እንዲህ ብሏል ዕብ12÷16-17 ድንግልናም አንድ ጊዜ ከተወገደ እንደ ፈሰስ ውኃ ነው።
የኃጢአት ቁስል በንስሐ መድኃኒት መፈወስ ቢችልም ትራት (ጠባሳ) ሳይተው ግን አይቀርም:: ስለዚህ እድናለሁ ብሎ በእሳት መጠበስ እንደማይገባ ንስሐ አለ ብሎም መበደል አይገባም፡፡ ኃጢአት የሚጥለው ጠባሳ ባይኖር ኖሮ ምንም ያልበደለና በድሎ በንስሐ የተመለሰ ሰው ልዩነት ባልኖራቸውም ነበር። በዝሙት የተሰነካከለ ሰው በንስሐ አማካይነት ምንም ካልተሰነካከለው ሰው ጋር በድንጋሌ ነፍስ መተካከል ቢችልም በድንጋሌ ሥጋ መበለጡ አይቀርም፡፡ ተሰብሮ በተጠገነና ምንም ባልተሰበረ ሰው መኻል ያለው ልዩነት ይህ ነውና፡፡
በንስሐ ከተመለስኩ ወዲህ እግዚአብሔር ድንጋሌ ሥጋዬን ቢመልስልኝ ምን አለበት? ማለት ተገቢ ሐሳብ አይደለም፡፡ በመጀመሪያ እግዚአብሔርን መፈታተን ነው፡፡ በሁለተኛ ደረጃ ለዚያ ነገር ሳይበቁ በጎን ነገር ከመመኘት አልፎ ይገባኛል ማለት የትዕቢት ሐሳብ ነው፡፡ ሌላው ይህን ሐሳብ የተለየ የሚያደርገው ደግሞ መጀመሪያ የተሰጠንን ከጣልን በኋላ መመኘታችን ነው፡፡ ራስ አጥፊ ረስ ተቆጭ መሆን አይሆንም? እንደ ሥራዬ ድንጋሌ ሥጋን ብቻ ሳይሆን ሌላም ማጣት ይገባኝ ነበር የሚል ሰው በእግዚአብሔር ዘንድ እንዴት የተወደደ ነው? በአንጻሩ ደግሞ «የኔ ውድቀት እንሌላው ሰው አልነበረም!» በማለት
እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም «ድንግል በክልኤ» እየተባለ በቅዱሳት መጻሕፍት ተነግሮላታል፡፡ ስለ ድንግልናዋ ትንቢት ተነግሯል ምሳሌም ተመስሏል:: ይህም በሁለት ወገን ማለትም በሥጋና በነፍስ ድንግል መሆኗን ለማመልከት ነው:: የደናግልም ሁሉ መመኪያቸው እርሷ ናት፡፡
እመቤታችን ቅድመ ፀኒስ፣ ጊዜ ፀኒስ፣ ድኅረ ፀኒስ ድንግል ናት:: ቅድመ ወሊድ፣ ጊዜ ወሊድ፣ ድኅረ ወሊድም ድንግል ናት፡፡ ቅዱሳንን ሁሉ ስለ ድንግልኗ ምስጋናና ክብር ያለ ማቋረጥ እንዲናገሩ ያደረገ ይህ ንጽሕናዋ ነው፡፡ ‹‹ስብሐተ ድንግልናኪ ወትረ ይነግር አፉየ› እንዲል:: (መልክዐ ማርያም)
የእመቤታችንን ድንግልና «ድንግልና» በመባሉ ብቻ ካልሆነ በቀር የፍጡራን ድንግልና በምንም አይመሳሰለውም፡፡ ስለ እመቤታችን ድንግልና ለመናገር ሌላ ትልቅ ጥራዝ ያለው መጽሐፍ መጻፍ ያስፈልጋል:: ስለድንግልና ለመናገር ስንፈልግ ስለ እርስዋ ከተጻፉት መንፈሳዊ ድርሰቶች አስረጅ አድርገን ብዙ ብንጠቅስም በድንግልና ፍጽምት ከመሆኗ የተነሣ የፍጡራንን ድንግልና ሕጹጽነት ለማየት እንዲረዳን ነው እንጂ ለማመሳሰል አይደለም፡፡
የእመቤታችንን ድንግልና የመላእክትም ንጽሕና አይደርስበትም፡፡ ለዚህም ማስረጃው የተአምረ ማርያም መቅድም እንዲህ ሲል ያሰፈረው ቃል ነው:: «ለመኑ ተውህቦ ተደንግሎ እለ እምውሉደ ሰብእ፣ ለመላእክትኒ ኢተክህሎሙ ተደንግሎ ሕሊና እስመ አበሱ በፍትወት ወወረዱ ምድረ በመዋዕል ዘቀዳሚ» በአማርኛ «ሥጋዊ ምኞትን የማሸነፍ ዕድል ለማን ተሰጠው? ኃጢአትን ከማሰብ መጠበቅ ለመላእክት እንኳን አልተቻላቸውም፤ በቀደመው ዘመን ያልተሰጣቸውን ሽተው በፈጸሙት በደል ከሰማይ ወደ ምድር ወርደዋልና።» (መቅድመ ተአምረ ማርያም)
ደናግላንና አለባበሳቸው!
ለዐቅመ ሔዋን የደረሱና ያልደረሱ፣ ደናግላን የሆኑና ያልሆኑ ሴቶች ተለይተው የሚታወቁበት የፀጉር አሠራር፣ አለጫጨትና የአለባበስ ሁኔታ በየሀገሩ ይገኛል:: በድሮ ጊዜ ደናግለ እስራኤል ለፍሬ -እልደረስንም ሲሉ ወርቅ እንደ አበባ የፈነዳበት ነጭ ሐር ለብሰው ይታዩ ነበር።
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ አለባበስ በሚገባ ካስተማረ በኋላ ትምህርቱ ደናግልንን ብቻ የሚመለከት ለመሰላቸው ሰዎች ‹ወአኮ ዘእቤ በእንተ ደናግል ባሕቲቶን› ማለትም «ይህን ያልኩት ስለ ደናግል ብቻ አይደለም» በማለት ደናግላን ብቻ ሳይሆኑ ሁሉም ሴቶች በሚገባ መንገድ ብቻ ማጌጥ እንዳለባቸው ይገልጻል:: ተግ.ዮሐ28
አለባበስ በዝሙት ለመውደቅ የሚዳርግበት ሁኔታ ሰፊ ስለሆነ በይበለጥ ደናግል አለባበሳቸው ተገቢ መሆን አለበት፡፡ ደናግላን የተለየ አለባበስ እንደ ነበራቸው መጽሐፍ ቅዱስም ይመሰክራል፡፡ ትዕማር ድንግል በነበረችበት ጊዜ ‹‹ብዙ ኅብር ያለውን ልብስ ለብሳ ነበር እንዲህ ያለውን ልብስ የንገሡ ልጆች ደናግሉ ይለብሱት ነበርና።» ነገር ግን በተደፈረችና ክብሯን ባጣች ጊዜ «ብዙ ኅብር ያለውን ልብስዋን ተርትሪ› እየጮኸች ሄደች:: 2ሳሙ13÷18-19
ድንጋሌ ሥጋ አንድ ጊዜ ጠፋ በኋላ ሊመለስ ይችላል?
በግዘፍ ያለ ድንጋሌ ሥጋ አንድ ብቻ ነው፡፡ ይህ ድንጋሌ ሥጋ. በሩካቤም ሆነ ያለ ሩካቤም የሚጠፋበት ጊዜ አለ፡፡ ድንጋሌ ሥጋን የሚያጠፋው ሩካቤ በመንፈሳዊው ሕግ የተደገፈ ሕጋዊ ሩካቤ ወይም ሕገ ወጥ ሩካቤ ሊሆን ይችላል:: በአጠቃላይ ድንጋሌ ሥጋ በልዩ ልዩ መንገድ ሊማስን ይችላል:: አንድ ጊዜ ጨርሶ የጠፋ ዓይን እግዚአብሔር ከሃሊነቱን ለማሳየት ሲፈቅድ ብቻ ካልሆነ በቀር ለበራ እንደማይችል ድንጋሌ ሥጋም አንድ ጊዜ ከተገሠሠ እንዲሁ ነውና አይመለስም፡፡ ድንጋሌ ሥጋ ዓይን መባሉን ከዚህ በላይ ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ‹ከመ ብንተ ዓይን» ያለውን በመጥቀስ ተመልክተናል፡፡
ከላይ እንደ ተገለጸው በንስሐ ተመልሶ የሚገኘው የነፍስ ድንግልና እንጂ የሥጋ ድንግልና አይደለም፡፡ መጽሐፈ መነኮሳት «ንስሐሰ ትሬስዮ ለዘአበሰ ከመ ዘኢአበሰ ለዘማዊ ድንግለ›› ፡ «ንስሐ ግን የበደለን እንዳልበደለ ዘማዊን እንደ ድንግል ታድርገዋለች::> በማለት የተናገረው ስለ ነፍስ ድንግልና እንጂ ስለ ድንጋለ ሥጋ አይደለም፡፡ አንድ ሰው ድንጋሌ ሥጋውን አንድ ጊዜ ካጣ በኋላ እንደ ገና በንስሐ ያገኘዋል ለማለትም አይደለም:: በተጨማሪም «እንደ ድንግል» ታደርገዋለች ይላል እንጂ ቁርጥ በሆነ ቃል «ድንግል ታደርገዋለች» አለማለቱን ልብ ማለት ያስፈልጋል:: ስለዚህ ስለ ድንጋሌ ሥጋ በመጀመሪያ መጠንቀቅ እንጂ ከሄደ በኋላ «ድንግል ብሆንስ?›› ማለት አጉል ተስፋ ነው፡፡ እንዲህ ሲባል ግን የእግዚአሔርን ከሃሊነት መጠራጠር ሳይሆን ያለ አግባብ ተስፋ ማድረ ግን ለመንቀፍ መሆኑን መረዳት ያስፈልጋል፡፡
የንጽሕና መርከባችን እንዳይሰበር መጠንቀቅ ያሻል:: «ብርሌ ከነቃ አይሆንም ዕቃ» እንደ ተባለው ድንጋሌ ሥጋም አንድ ጊዜ ከተወሰደ እንደ ተሰበረ የሸክላ ዕቃና እንደ ሞተ ሰው ነው:: እነዚህ ተመልሰው ይረባሉ፣ ይጠቅማሉ እንደማይባሉ ድንጋሌ ሥጋም እንዲሁ ነውና ይመለሳል አይባልም:: መዝ30፥12
የኃጢአት መጥፎነቷ ይታወቅ ዘንድ ኃጢአት ከሠራን በኋላ ቢያንስ በአንድ ነገር እንቀጣለን:: ወይም አንድ ነገር እናጣለን፡፡ ዝሙት ምክንያት ድንጋሌ ሥጋ አንዴ ከተወገደ በኋላ የማይመለስበትም አንዱ ምክንያት ይህ ነው:: ንጉሥ ዳዊት ባመነዘረ ጊዜ ምንም እንኳን ንስሐ ቢገባ በዝሙት የጸነሰው ልጁ ሊፈወስለት አለመቻሉ ኃጢአት ቢያንስ በአንድ ጐዳና ሳትጐዳ እንደ ማትቀር ያመለከታል:: 2ሳሙ12፥13-14
አንዳንድ ነገሮች አንድ ጊዜ ካመለጡ በኋላ በንስሐ እንኳን መልሶ ማግኘት የማይቻልበት ሁኔታ መኖሩን ማወቅ ያስፈልጋል:: ለምሳሌ:- ዔሳው ብኩርናውን ባቃለላት ጊዜ ከሱ ወደ ታናሽ ወንድሙ ወደ ያዕቆብ ተዛውራለች:: በኋላ ግን ምንም ክልብ ቢፈልጋት መልሶ ለማግኘት አለመቻሉን ቅዱስ ጳውሎስ ሲገለጽ እንዲህ ብሏል ዕብ12÷16-17 ድንግልናም አንድ ጊዜ ከተወገደ እንደ ፈሰስ ውኃ ነው።
የኃጢአት ቁስል በንስሐ መድኃኒት መፈወስ ቢችልም ትራት (ጠባሳ) ሳይተው ግን አይቀርም:: ስለዚህ እድናለሁ ብሎ በእሳት መጠበስ እንደማይገባ ንስሐ አለ ብሎም መበደል አይገባም፡፡ ኃጢአት የሚጥለው ጠባሳ ባይኖር ኖሮ ምንም ያልበደለና በድሎ በንስሐ የተመለሰ ሰው ልዩነት ባልኖራቸውም ነበር። በዝሙት የተሰነካከለ ሰው በንስሐ አማካይነት ምንም ካልተሰነካከለው ሰው ጋር በድንጋሌ ነፍስ መተካከል ቢችልም በድንጋሌ ሥጋ መበለጡ አይቀርም፡፡ ተሰብሮ በተጠገነና ምንም ባልተሰበረ ሰው መኻል ያለው ልዩነት ይህ ነውና፡፡
በንስሐ ከተመለስኩ ወዲህ እግዚአብሔር ድንጋሌ ሥጋዬን ቢመልስልኝ ምን አለበት? ማለት ተገቢ ሐሳብ አይደለም፡፡ በመጀመሪያ እግዚአብሔርን መፈታተን ነው፡፡ በሁለተኛ ደረጃ ለዚያ ነገር ሳይበቁ በጎን ነገር ከመመኘት አልፎ ይገባኛል ማለት የትዕቢት ሐሳብ ነው፡፡ ሌላው ይህን ሐሳብ የተለየ የሚያደርገው ደግሞ መጀመሪያ የተሰጠንን ከጣልን በኋላ መመኘታችን ነው፡፡ ራስ አጥፊ ረስ ተቆጭ መሆን አይሆንም? እንደ ሥራዬ ድንጋሌ ሥጋን ብቻ ሳይሆን ሌላም ማጣት ይገባኝ ነበር የሚል ሰው በእግዚአብሔር ዘንድ እንዴት የተወደደ ነው? በአንጻሩ ደግሞ «የኔ ውድቀት እንሌላው ሰው አልነበረም!» በማለት