የህዳሴ ግድብ አምስተኛው ተርባይ ኃይል ማመንጨት ጀመረ
-----------
የቅድመ ኃይል ማመንጨት ሙከራ ስራ በተሳካ ሁኔታ ተከናውኖባቸው ወደ ዋና ስራቸው እንዲገቡ ዝግጁ ከሆኑ ተርባይኖች መካከል ተርባይን ቁጥር 6 የሙከራ ስራው ተጠናቆ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ጀምሯል።
አሁን ባለው ተጨባጭ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም እስከ 401.26 MW ኃይል እያመነጨ ይገኛል።
እያንዳንዱን የውኃ ጠብታ ወደ ኃይል በመቀየር 400 ምጋ ዋት ኃይል ከሚያመነጩት 11 ተርባይኖች መካከል አምስተኛው ተርባይን ቁጥር ስድስት ወደ ኃይል ማምረት ስራ ገብቷል፡፡
በተጨማሪ ተርባይን ቁጥር 5 ደግሞ የኮሚሽኒንግ ስራው የመጨረሻ ምዕራፍ ሙከራ ላይ ይገኛል፡፡
የግድቡ ስድስተኛው ተርባይን የሆነው ተርባይን ቁጥር 5 በቅርቡ ማለፍ ያለበትን የሙከራ ሂደቶቹን አጠናቆ ወደ ማመንጨት ስራ እንደሚገባም የማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤቱ መረጃ ያመለክታል።
ከዚህ ቀደም የቅድመ ተርባይን ቁጥር 8 እና ተርባይን ቁጥር 7 ኃይል የማምረት ሂደት መግባታቸው ይታውቃል፡፡
-----------
የቅድመ ኃይል ማመንጨት ሙከራ ስራ በተሳካ ሁኔታ ተከናውኖባቸው ወደ ዋና ስራቸው እንዲገቡ ዝግጁ ከሆኑ ተርባይኖች መካከል ተርባይን ቁጥር 6 የሙከራ ስራው ተጠናቆ የኤሌክትሪክ ኃይል ማመንጨት ጀምሯል።
አሁን ባለው ተጨባጭ የኤሌክትሪክ ኃይል የማመንጨት አቅም እስከ 401.26 MW ኃይል እያመነጨ ይገኛል።
እያንዳንዱን የውኃ ጠብታ ወደ ኃይል በመቀየር 400 ምጋ ዋት ኃይል ከሚያመነጩት 11 ተርባይኖች መካከል አምስተኛው ተርባይን ቁጥር ስድስት ወደ ኃይል ማምረት ስራ ገብቷል፡፡
በተጨማሪ ተርባይን ቁጥር 5 ደግሞ የኮሚሽኒንግ ስራው የመጨረሻ ምዕራፍ ሙከራ ላይ ይገኛል፡፡
የግድቡ ስድስተኛው ተርባይን የሆነው ተርባይን ቁጥር 5 በቅርቡ ማለፍ ያለበትን የሙከራ ሂደቶቹን አጠናቆ ወደ ማመንጨት ስራ እንደሚገባም የማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤቱ መረጃ ያመለክታል።
ከዚህ ቀደም የቅድመ ተርባይን ቁጥር 8 እና ተርባይን ቁጥር 7 ኃይል የማምረት ሂደት መግባታቸው ይታውቃል፡፡