የሱዳን የፈጥኖ ደራሽ ወታደሮች በመቶዎች የተቆጠሩ ሰዎችን መግደላቸው ተነገረ
----------
የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል በነጭ አባይ ግዛት በፈጸመው ጥቃት ጨቅላ ህፃናትን ጨምሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሲቪሎች መሞታቸውን የሱዳን ባለሥልጣናት እና የመብት ተሟጋች ድርጅቶች ትላንት ማክሰኞ አስታወቁ።
የሱዳን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፣ “ቡድኑ ባለፉት ጥቂት ቀናት ውስጥ በሱዳን ጦር ‘አሰቃቂ ሽንፈት’ ከደረሰበት በኋላ በአል-ጊታይና አካባቢ በሚገኙ መንደሮች ውስጥ በሰላማዊ ሰዎች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ፈጽሟል።” ብሏል፡፡ የሱዳን ዶክተሮች ሠራተኛ ማኅበር የሟቾች ቁጥር 300 መኾኑን ሲያስታውቅ መግለጫው ቁጥሩ 433 አድርሶታል።
በሲቪሎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን የሚከታተለው የአደጋ ጊዜ ጠበቆች የመብት ተሟጋች ቡድን ትላንት ማክሰኞ ማለዳ በሰጠው መግለጫ፣ “ባለፉት ሦስት ቀናት ውስጥ፣ ሴቶች እና ህፃናትን ጨምሮ ከ200 በላይ ሰዎች በፈጥኖ ደራሽ ጥቃቶች መገደላቸውን” ጠቅሶ ሌሎች በመቶዎች የሚቆጠሩ ቆስለዋል ብሏል።
----------
የሱዳን ፈጥኖ ደራሽ ኃይል በነጭ አባይ ግዛት በፈጸመው ጥቃት ጨቅላ ህፃናትን ጨምሮ በመቶዎች የሚቆጠሩ ሲቪሎች መሞታቸውን የሱዳን ባለሥልጣናት እና የመብት ተሟጋች ድርጅቶች ትላንት ማክሰኞ አስታወቁ።
የሱዳን ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ባወጣው መግለጫ፣ “ቡድኑ ባለፉት ጥቂት ቀናት ውስጥ በሱዳን ጦር ‘አሰቃቂ ሽንፈት’ ከደረሰበት በኋላ በአል-ጊታይና አካባቢ በሚገኙ መንደሮች ውስጥ በሰላማዊ ሰዎች ላይ ያነጣጠረ ጥቃት ፈጽሟል።” ብሏል፡፡ የሱዳን ዶክተሮች ሠራተኛ ማኅበር የሟቾች ቁጥር 300 መኾኑን ሲያስታውቅ መግለጫው ቁጥሩ 433 አድርሶታል።
በሲቪሎች ላይ የሚፈጸሙ ጥቃቶችን የሚከታተለው የአደጋ ጊዜ ጠበቆች የመብት ተሟጋች ቡድን ትላንት ማክሰኞ ማለዳ በሰጠው መግለጫ፣ “ባለፉት ሦስት ቀናት ውስጥ፣ ሴቶች እና ህፃናትን ጨምሮ ከ200 በላይ ሰዎች በፈጥኖ ደራሽ ጥቃቶች መገደላቸውን” ጠቅሶ ሌሎች በመቶዎች የሚቆጠሩ ቆስለዋል ብሏል።