የታላላቆቹ የአውሮፓ ሃገራት ውርደት እና ክስረት
-----------
የአውሮፓ ሃገራትን እና የዩክሬን መንግስትን ወዲያ በሉ ብለው ኘሬዝደንት ትራምኘ ፥ መንግስታቸው በዩክሬን ጉዳይ ከሩሲያ ጋር በሪያድ ንግግር መጀመሩ ጨዋታውን ሁሉ ቀይሮታል።
በትራምኘ እርምጃ ተከዳን ያሉት የአውሮፓ ሃገራት ትላንት በፓሪስ ተሰብስበው የነበረ ይሁን እንጂ በሃሳብ ተከፋፍለው ፥ በአቋም ተለያይተው ያለ ውጤት ተበትነዋል።
ከዩክሬን ጎን ተሰልፈው ያለፉትን ሁለት አመታት ጦርነቱን በገንዘብ ፣ በመሳሪያ ፣ በሚድያ እና በዲኘሎማሲ ሲደግፉ የነበሩት ዋንኞቹ ሃገራት ፈረንሳይ ፣ ጀርመን እና እንግሊዝ የአሜሪካ መንግስት በጀመረው አዲስ ድርድር ፍፁም ልዩነት ያለው አቋም ይዘዋል።
ሁሉም ግራ ተጋብተው ተከዳን የሚል ድምፅ እያሰሙ ነው።
የአውሮፓ ህብረት መሪ የሆኑት ሶስቱ ሃገራት የጋራ በሚሉት ጉዳይ ላይ እንዲህ ያለ የተለያየ አቋም ይዘው አያውቁም እየተባለ ነው።
ፈረንሳይ የአውሮፓ ህብረት የሌለበት ድርደር በዩክሬን ጉዳይ መካሄድ የለበትም የሚል ሃሳብ ይዛ በመቅረብ ሃሳቡን ጀርመን እና እንግሊዝ እንዲደግፉ ጠይቃለች።
ከአሜሪካ መንገድ የማትወጣው እንግሊዝ ደግሞ ሪያድ ላይ ስምምነት የሚደረስ ከሆነ ሰላም አስከባሪ በዩክሬን አሰማራለሁ በማለት አቋሟን አሳውቃለች። በሌላ መልኩ ለትራምኘ መንግስት እርምጃዎች እውቅና ሰጥታለች።
ይህ የእንግሊዝ አቋም ጀርመን እና ፈረንሳይን ይበለጥ አስደንግጧል።
የጀርመን መራሄመንግስት ኦላፍ ሾልዝ የእንግሊዝ አቋም በጣሙን አስቆጥቷቸው የሃገራቱን ፍላጎት የገፋ እና ወቅቱን ያልጠበቀ ሃሳብ ሲሉ ነቅፈውታል።
የጉዳዩ ባለቤት ነን የሚሉት ሶስቱ ሃገራት እነርሱን ከጨዋታ ሜዳ ያገለለ ድርድር መጀመሩን በመቃወም የጋራ አቋም እንዲይዙ ቢታሰብም ሊሳካ አልቻለም።
የትራምኘ መንግስት ፈጣን እና ያልተጠበቀ አካሄድ ክፍፍላቸው እንዲሰፋ አድርጓል።
በፓሪስ ለምክክር ሲጠራሩ በዩክሬን የሰላም ሂደት ላይ ለመነጋገር መሆኑን ቢገልፁም " ያለፉት ሁለት አመታትን ጦርነቱን ሲደግፉ ቆይተው አሁን ከየት መጥተው ስለሰላም ለማውራት ደፈሩ " የሚሉ የስላቅ አስተያየቶች ከአሜሪካ እና ሩሲያ ሰዎች ተሰንዝሮባቸዋል።
ሶስቱ ሃገራት መቶ ቢሊየኖችን ያፈሰሱበት ጦርነት በውርደት እና ከባድ ክስረት ሊደመደም ዋዜማው ላይ እንደሆነ ተረድተዋል።
-----------
የአውሮፓ ሃገራትን እና የዩክሬን መንግስትን ወዲያ በሉ ብለው ኘሬዝደንት ትራምኘ ፥ መንግስታቸው በዩክሬን ጉዳይ ከሩሲያ ጋር በሪያድ ንግግር መጀመሩ ጨዋታውን ሁሉ ቀይሮታል።
በትራምኘ እርምጃ ተከዳን ያሉት የአውሮፓ ሃገራት ትላንት በፓሪስ ተሰብስበው የነበረ ይሁን እንጂ በሃሳብ ተከፋፍለው ፥ በአቋም ተለያይተው ያለ ውጤት ተበትነዋል።
ከዩክሬን ጎን ተሰልፈው ያለፉትን ሁለት አመታት ጦርነቱን በገንዘብ ፣ በመሳሪያ ፣ በሚድያ እና በዲኘሎማሲ ሲደግፉ የነበሩት ዋንኞቹ ሃገራት ፈረንሳይ ፣ ጀርመን እና እንግሊዝ የአሜሪካ መንግስት በጀመረው አዲስ ድርድር ፍፁም ልዩነት ያለው አቋም ይዘዋል።
ሁሉም ግራ ተጋብተው ተከዳን የሚል ድምፅ እያሰሙ ነው።
የአውሮፓ ህብረት መሪ የሆኑት ሶስቱ ሃገራት የጋራ በሚሉት ጉዳይ ላይ እንዲህ ያለ የተለያየ አቋም ይዘው አያውቁም እየተባለ ነው።
ፈረንሳይ የአውሮፓ ህብረት የሌለበት ድርደር በዩክሬን ጉዳይ መካሄድ የለበትም የሚል ሃሳብ ይዛ በመቅረብ ሃሳቡን ጀርመን እና እንግሊዝ እንዲደግፉ ጠይቃለች።
ከአሜሪካ መንገድ የማትወጣው እንግሊዝ ደግሞ ሪያድ ላይ ስምምነት የሚደረስ ከሆነ ሰላም አስከባሪ በዩክሬን አሰማራለሁ በማለት አቋሟን አሳውቃለች። በሌላ መልኩ ለትራምኘ መንግስት እርምጃዎች እውቅና ሰጥታለች።
ይህ የእንግሊዝ አቋም ጀርመን እና ፈረንሳይን ይበለጥ አስደንግጧል።
የጀርመን መራሄመንግስት ኦላፍ ሾልዝ የእንግሊዝ አቋም በጣሙን አስቆጥቷቸው የሃገራቱን ፍላጎት የገፋ እና ወቅቱን ያልጠበቀ ሃሳብ ሲሉ ነቅፈውታል።
የጉዳዩ ባለቤት ነን የሚሉት ሶስቱ ሃገራት እነርሱን ከጨዋታ ሜዳ ያገለለ ድርድር መጀመሩን በመቃወም የጋራ አቋም እንዲይዙ ቢታሰብም ሊሳካ አልቻለም።
የትራምኘ መንግስት ፈጣን እና ያልተጠበቀ አካሄድ ክፍፍላቸው እንዲሰፋ አድርጓል።
በፓሪስ ለምክክር ሲጠራሩ በዩክሬን የሰላም ሂደት ላይ ለመነጋገር መሆኑን ቢገልፁም " ያለፉት ሁለት አመታትን ጦርነቱን ሲደግፉ ቆይተው አሁን ከየት መጥተው ስለሰላም ለማውራት ደፈሩ " የሚሉ የስላቅ አስተያየቶች ከአሜሪካ እና ሩሲያ ሰዎች ተሰንዝሮባቸዋል።
ሶስቱ ሃገራት መቶ ቢሊየኖችን ያፈሰሱበት ጦርነት በውርደት እና ከባድ ክስረት ሊደመደም ዋዜማው ላይ እንደሆነ ተረድተዋል።