አንድ መሪ በሌላ መሪ እስከ ዶቃው ማሰሪያ ሲነገረው ዛሬ አየሁ
------------
በታሪክ አንድ መሪ የሌላ ሃገርን መሪ ቀሃገሩ ጦርቶ በሚድያ ፊት ለዚያውም በቀጥታ ስርጭት ለአለም እየተላለፈ እንዲህ ሲዘልፍ ፣ ሲቆጣ ፣ ሲገፅስ ታይቶ አይታወቅም።
ትራምኘ ዘለንስኪን ዛሬ እንደ መሪ ሳይሆን እንደ ሰፈር ጎረምሳ በስድብ እና ሃይለቃል ፍፁም ዲኘሎማሲን በጣሰ አግባብ ሲዘልፉ ታዩ።
ትራምኘ ከምክትላቸው ጄድ ቫንስ ጋር እየተቀባበሉ በአለም ህዝብ ፊት ዘለንስኪን ቃል ሳይመርጡ ወርፈው አባረውታል።
እንዲህ ያለ የሁለት መሪዎች ንግግር በይፋ ለህዝብ ቀርቦ አያውቅም ሲሉ ሚድያዎች እየዘገቡ ነው።
ዜለንስኪ ዋሽንግተን የተገኘው አሜሪካ ዩክሬን ከሩሲያ ጋር ለምታደርገው ጦርነት ለሰጠኋት ገንዘብ መካሻ ማዕድኖቿን በመስጠት ትክፈለኝ በሚል በያዘችው አቋም ለመደራደር ነበር ።
ድርድሩ ሳይካሄድ በሚድያ ፊት የተዘለፈው ዘለንስኪ የመጣበትን ጉዳይ ሳይፈፅም ወደ ሃገሩ ተመልሷል።
እስከ ዶቃው ማሰሪያ በሚያስብል ደረጃ ቁጣና ዘለፋን ትራምኘ ከምክትላቸው ጋር እየተቀባበሉ አዝንበውበታል።
ስሜቱን መቆጣጠር የተሳነው ዜለንስኪ የሁለቱን ሰዎች ዘለፋ ለማቋረጥ ቢሞክርም " በኦቫሉ ቢሮ መጥተህ አስተዳደራችን ልትተች ተሞክረለህ እንዴ ፥ ይህ ክብረነክነት ነው " ብለው አስጎንብሰውታል።
በነበረው የጦፈ ንግግር ትራምኘ ዜለንስኪን በንቀት እና ቁጣ እንዲህ አሉት፥
👉" የምትሰራው ስራ ለአሜሪካ ያለህን ዝቅ ያለ አክብሮት የሚያሳይ ነው "
👉"በምናቀርብልህ መደራደሪያ ወይ ትስማማለህ ወይ ብቻህን ትቀራለህ "
👉" ክብር የሌለህ ሰው ነህ "
👉" አንተ ሶስተኛውን የአለም ጦርነት ለመቀስቀስ የቆመርክ ሰው ነህ "
👉" ፑቲንን አስቀያሚ ነገር እንድናገርልህ እና አየህ ፑቲን እኛ ተግባብተናል ማለት ነው የአንተ ፍላጎት ፥ ይህ ፈፅም አይሆንም "
👉" በተቃራኒ ያለውን ልንገርህ እኔ ፑቲንን እወደዋለሁ ፥ እኛ እንዋደዳለን "
👉" አሁን ምንም አይነት የመደራደሪያ ካርድ የለህም "
👉" ያለ እኛ ምንም አይነት አቅም የለህም "
👉 " የውጊያ አቅም የለህም ሰራዊትህ ሁሉ ተበትኗል "
👉 " ልታመሰግነኝ ይገባህ ነበር ፥አንዴም ግን ስታመሰግን አልተሰማህም "
የመናገር እድል ያጣው ዜለንስኪ እጅግ ለአንድ መሪ በማይገባ መልኩ በንዴት ተሞልቶ ከነጩ ቤት ወጥቷል።
ጉብኝቱም ስምምነቱም ሳይፈፀም ቆይታውን በአጭር ቋጭቶ ወደ ሃገሩ ተመልሷል።
ትራምኘ ከውይይቱ በኋላ ዘለንስኪ መንግስታቸው ያቀረበውን የድርድር ሃሳብ ባለመቀበሉ ስምምነት ሊፈፀም አልቻለም ብለዋል።
" ለሰላም ዝግጁ ሲሆን ተመልሶ ይመጣል " ብለዋል።
የዩክሬን ህዝብ ምን ብሎ ይሆን ግን ?
ተፃፈ በሰይፈዲን በአማን ለ #ኢትዮ_ኘላስ
------------
በታሪክ አንድ መሪ የሌላ ሃገርን መሪ ቀሃገሩ ጦርቶ በሚድያ ፊት ለዚያውም በቀጥታ ስርጭት ለአለም እየተላለፈ እንዲህ ሲዘልፍ ፣ ሲቆጣ ፣ ሲገፅስ ታይቶ አይታወቅም።
ትራምኘ ዘለንስኪን ዛሬ እንደ መሪ ሳይሆን እንደ ሰፈር ጎረምሳ በስድብ እና ሃይለቃል ፍፁም ዲኘሎማሲን በጣሰ አግባብ ሲዘልፉ ታዩ።
ትራምኘ ከምክትላቸው ጄድ ቫንስ ጋር እየተቀባበሉ በአለም ህዝብ ፊት ዘለንስኪን ቃል ሳይመርጡ ወርፈው አባረውታል።
እንዲህ ያለ የሁለት መሪዎች ንግግር በይፋ ለህዝብ ቀርቦ አያውቅም ሲሉ ሚድያዎች እየዘገቡ ነው።
ዜለንስኪ ዋሽንግተን የተገኘው አሜሪካ ዩክሬን ከሩሲያ ጋር ለምታደርገው ጦርነት ለሰጠኋት ገንዘብ መካሻ ማዕድኖቿን በመስጠት ትክፈለኝ በሚል በያዘችው አቋም ለመደራደር ነበር ።
ድርድሩ ሳይካሄድ በሚድያ ፊት የተዘለፈው ዘለንስኪ የመጣበትን ጉዳይ ሳይፈፅም ወደ ሃገሩ ተመልሷል።
እስከ ዶቃው ማሰሪያ በሚያስብል ደረጃ ቁጣና ዘለፋን ትራምኘ ከምክትላቸው ጋር እየተቀባበሉ አዝንበውበታል።
ስሜቱን መቆጣጠር የተሳነው ዜለንስኪ የሁለቱን ሰዎች ዘለፋ ለማቋረጥ ቢሞክርም " በኦቫሉ ቢሮ መጥተህ አስተዳደራችን ልትተች ተሞክረለህ እንዴ ፥ ይህ ክብረነክነት ነው " ብለው አስጎንብሰውታል።
በነበረው የጦፈ ንግግር ትራምኘ ዜለንስኪን በንቀት እና ቁጣ እንዲህ አሉት፥
👉" የምትሰራው ስራ ለአሜሪካ ያለህን ዝቅ ያለ አክብሮት የሚያሳይ ነው "
👉"በምናቀርብልህ መደራደሪያ ወይ ትስማማለህ ወይ ብቻህን ትቀራለህ "
👉" ክብር የሌለህ ሰው ነህ "
👉" አንተ ሶስተኛውን የአለም ጦርነት ለመቀስቀስ የቆመርክ ሰው ነህ "
👉" ፑቲንን አስቀያሚ ነገር እንድናገርልህ እና አየህ ፑቲን እኛ ተግባብተናል ማለት ነው የአንተ ፍላጎት ፥ ይህ ፈፅም አይሆንም "
👉" በተቃራኒ ያለውን ልንገርህ እኔ ፑቲንን እወደዋለሁ ፥ እኛ እንዋደዳለን "
👉" አሁን ምንም አይነት የመደራደሪያ ካርድ የለህም "
👉" ያለ እኛ ምንም አይነት አቅም የለህም "
👉 " የውጊያ አቅም የለህም ሰራዊትህ ሁሉ ተበትኗል "
👉 " ልታመሰግነኝ ይገባህ ነበር ፥አንዴም ግን ስታመሰግን አልተሰማህም "
የመናገር እድል ያጣው ዜለንስኪ እጅግ ለአንድ መሪ በማይገባ መልኩ በንዴት ተሞልቶ ከነጩ ቤት ወጥቷል።
ጉብኝቱም ስምምነቱም ሳይፈፀም ቆይታውን በአጭር ቋጭቶ ወደ ሃገሩ ተመልሷል።
ትራምኘ ከውይይቱ በኋላ ዘለንስኪ መንግስታቸው ያቀረበውን የድርድር ሃሳብ ባለመቀበሉ ስምምነት ሊፈፀም አልቻለም ብለዋል።
" ለሰላም ዝግጁ ሲሆን ተመልሶ ይመጣል " ብለዋል።
የዩክሬን ህዝብ ምን ብሎ ይሆን ግን ?
ተፃፈ በሰይፈዲን በአማን ለ #ኢትዮ_ኘላስ