እንግሊዝ የያዘችው መንገድ የት ድረስ ያስጉዛታል ?
--------
የትራምኘ መንግስት በዩክሬን ጉዳይ የአቋም ለውጥ ማድረጉን ተክተሎ ነገሮችን ለማለዘብ ያልተሳካ ጥረት ሲያደርጉ እንደነበር ይታወቃል።
በተለይ እንግሊዝ እና ፈረንሳይ ሌሎች የአውሮፓ ሃገራትን አካተው ከዩክሬን ጎን መሰለፋቸውን እንደሚቀጥሉ ፣ ድጋፋቸውን እንደሚያጠናክሩ ባለፉት ሁለት ቀናት ሲገልፁ ተሰምተዋል።
በተለይ እንግሊዝ ከትራምኘ ጋር የተቃረነ አቋሟን እንደቀደሙት ጊዜያት ለማስታረቅ ስትሞክር ሳይሆን የታየችው ፥ ሌሎች የአቋሟ ተጋሪ የአውሮፓ ሃገራትን አስከትላ በተፃራሪነት መቀጠልን ነው።
አርብ ከኋይትሃውስ አቀርቅረው የተመለሱትን ቭላድሜር ዜሌንስኪን በክብር የተቀበለችው እንግሊዝ እሁድ እለት በለንደን የአውሮፓ ሃገራት የተሳተፉበት ቀጣይ ሂደት ላይ የሚመክር ጉባኤን አካሂዳለች።
ዛሬ ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትር ኬር ስታንመር አማካኝነት ዩክሬንን በቀጣይ ለመደገፍ እና የሩሲያን ቀጣይ ወረራ ለመከላከል ያስችላል ያለችውን ባለአራት ነጥብ ዕቅድ ይፋ አድርጋለች።
አራት ነጥቦችን የያዘው የእንግሊዝ ምክረ ሃሰብ የሚከተለው ነው፦
1. ለዩክሬን የሚደረግ ወታደራዊ ድጋፍ መቀጠል
2. ዩክሬንን ያካተተ የሰላም ንግግር እንዲጀመር ማድረግ
3. የሩሲያ ወረራ ለመመከት የሚያስችል የመከላከያ አቅም ዩክሬን እንድተገነባ መደገፍ
4. ዩክሬንን የሚደግፉ ፈቃደኛ ሃገራት ጥምረት መመስረት እና ሰራዊት ወደ ዩክሬን መላክ የሚሉ ናቸው።
በዩክሬን ጉዳይ የጠ/ሚር ስታንመር መንግስት የያዘውን አቋም ለሃገሪቱ ምክር ቤት ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን አብላጫ ድጋፍ አግኝቷል።
እንግሊዝ አሜሪካ አልሄድበትም ባለችው መንገድ " ምን ያህል ልትጓዝ ትችላለች ?" የሚለው የወቅቱ ጥያቄ ነው።
--------
የትራምኘ መንግስት በዩክሬን ጉዳይ የአቋም ለውጥ ማድረጉን ተክተሎ ነገሮችን ለማለዘብ ያልተሳካ ጥረት ሲያደርጉ እንደነበር ይታወቃል።
በተለይ እንግሊዝ እና ፈረንሳይ ሌሎች የአውሮፓ ሃገራትን አካተው ከዩክሬን ጎን መሰለፋቸውን እንደሚቀጥሉ ፣ ድጋፋቸውን እንደሚያጠናክሩ ባለፉት ሁለት ቀናት ሲገልፁ ተሰምተዋል።
በተለይ እንግሊዝ ከትራምኘ ጋር የተቃረነ አቋሟን እንደቀደሙት ጊዜያት ለማስታረቅ ስትሞክር ሳይሆን የታየችው ፥ ሌሎች የአቋሟ ተጋሪ የአውሮፓ ሃገራትን አስከትላ በተፃራሪነት መቀጠልን ነው።
አርብ ከኋይትሃውስ አቀርቅረው የተመለሱትን ቭላድሜር ዜሌንስኪን በክብር የተቀበለችው እንግሊዝ እሁድ እለት በለንደን የአውሮፓ ሃገራት የተሳተፉበት ቀጣይ ሂደት ላይ የሚመክር ጉባኤን አካሂዳለች።
ዛሬ ደግሞ በጠቅላይ ሚኒስትር ኬር ስታንመር አማካኝነት ዩክሬንን በቀጣይ ለመደገፍ እና የሩሲያን ቀጣይ ወረራ ለመከላከል ያስችላል ያለችውን ባለአራት ነጥብ ዕቅድ ይፋ አድርጋለች።
አራት ነጥቦችን የያዘው የእንግሊዝ ምክረ ሃሰብ የሚከተለው ነው፦
1. ለዩክሬን የሚደረግ ወታደራዊ ድጋፍ መቀጠል
2. ዩክሬንን ያካተተ የሰላም ንግግር እንዲጀመር ማድረግ
3. የሩሲያ ወረራ ለመመከት የሚያስችል የመከላከያ አቅም ዩክሬን እንድተገነባ መደገፍ
4. ዩክሬንን የሚደግፉ ፈቃደኛ ሃገራት ጥምረት መመስረት እና ሰራዊት ወደ ዩክሬን መላክ የሚሉ ናቸው።
በዩክሬን ጉዳይ የጠ/ሚር ስታንመር መንግስት የያዘውን አቋም ለሃገሪቱ ምክር ቤት ቀርቦ ውይይት የተደረገበት ሲሆን አብላጫ ድጋፍ አግኝቷል።
እንግሊዝ አሜሪካ አልሄድበትም ባለችው መንገድ " ምን ያህል ልትጓዝ ትችላለች ?" የሚለው የወቅቱ ጥያቄ ነው።