" ተፀፅቻሁ " አሉ ቭላድሚር ዜለንስኪ
-----
ኘሬዝደንት ዜለንስኪ ባለፈው አርብ በኋይትሃውስ ከትራምኘ እና ምክትላቸው ጋር በዘለፋ እና ቁጣ የታጀው ውይይት በዚያ መልኩ መካሄዱ ፀፀት ውስጥ ከቶኛል ብለዋል።
ኘሬዝደንቱ " ከአሜሪካ ጋር ያለንን አጋርነት ለማስጠበቅ አሁንም ዝግጁ ነኝ። የነጩ ቤተመንግስት ውይይት ፀፀት የፈጠረብኝ ቢሆንም ፥ አሁን ነገሮችን ወደ ትክክለኛ መስመር የምንመልስበት ነው " ሲሉ ገልፀዋል።
ዜለንስኪ ይህን መልዕከት በኤክስ ገፃቸው ያስተላለፉት ዛሬ የአሜሪካ መንግስት በይፋ ለዩክሬን ሲሰጥ የነበረውን ወታደራዊ ድጋፋ እንዳቋረጠ ማስታወቁን ተከትሎ ነው።
ፈጣኑ የአሜሪካ ውሳኔ የሚጠበቅ ሲሆን ይዞት የሚመጣው ጣጣ የበዛ መሆኑን የሚያውቁት ዘለንስኪ ለሰላም ስምምነት ዝግጁ መሆናቸውንም ተናግረዋል።
ባለፈው ሳምንት ውድቅ ያደረጉትን የማዕድን ስምምነት ለመፈፀምም ዝግጁ እንደሆኑ ዛሬ ምሽት አስታውቀዋል።
ዜለንስኪ የአቋም ለውጥ ማድረጋቸውን ተከትሎ የአሜሪካ መንግስት ምላሽ ምን ሊሆን እንደሚችል እየተጠበቀ ነው።
-----
ኘሬዝደንት ዜለንስኪ ባለፈው አርብ በኋይትሃውስ ከትራምኘ እና ምክትላቸው ጋር በዘለፋ እና ቁጣ የታጀው ውይይት በዚያ መልኩ መካሄዱ ፀፀት ውስጥ ከቶኛል ብለዋል።
ኘሬዝደንቱ " ከአሜሪካ ጋር ያለንን አጋርነት ለማስጠበቅ አሁንም ዝግጁ ነኝ። የነጩ ቤተመንግስት ውይይት ፀፀት የፈጠረብኝ ቢሆንም ፥ አሁን ነገሮችን ወደ ትክክለኛ መስመር የምንመልስበት ነው " ሲሉ ገልፀዋል።
ዜለንስኪ ይህን መልዕከት በኤክስ ገፃቸው ያስተላለፉት ዛሬ የአሜሪካ መንግስት በይፋ ለዩክሬን ሲሰጥ የነበረውን ወታደራዊ ድጋፋ እንዳቋረጠ ማስታወቁን ተከትሎ ነው።
ፈጣኑ የአሜሪካ ውሳኔ የሚጠበቅ ሲሆን ይዞት የሚመጣው ጣጣ የበዛ መሆኑን የሚያውቁት ዘለንስኪ ለሰላም ስምምነት ዝግጁ መሆናቸውንም ተናግረዋል።
ባለፈው ሳምንት ውድቅ ያደረጉትን የማዕድን ስምምነት ለመፈፀምም ዝግጁ እንደሆኑ ዛሬ ምሽት አስታውቀዋል።
ዜለንስኪ የአቋም ለውጥ ማድረጋቸውን ተከትሎ የአሜሪካ መንግስት ምላሽ ምን ሊሆን እንደሚችል እየተጠበቀ ነው።