ገምሀልያ አንሆንም


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


ካየሁት 👀 አስገራሚ
ከሠማሁት 👂 መሣጭ
ካነበብኩት 📖 አስተማሪ
ካሠብኩት ♀🅱 ልዩ ልዩ
እነሆ
ፅሁፎቻችሁን በ @NomoreGemhalya አካፍሉን።
ለማንኛውም አስተያየት ጥያቄ እና ጥቆማ @NomoreGemhalya ይጠቀሙ።

Связанные каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


🇪🇹 ኢትዮ Students dan repost
የወጣቶች ራስን ማጥፋት ምክንያቱ ምን ይሆን?

ብንሄድ ይሻለናል የሚልዕክት በፌስቡክ ገጿ ላይ ያሰፈረችው ወጣት ራሷ. አጠፋች!



ናዝራዊት ተስፋዬ ትባላለች። ከሁለት ቀን በፊት ስንብት የሚመስሉ ልጥፎችን አጋርታ ዛሬ ራሷን ማጥፋቷ ተሰምቷል። ይሄ ድርጊት እየተለመደ መጥቷል። ይህቺ ነፍስ ብዙ መከራ ብቻዋን እንደታገለች፣እምባ ዘመዷ እንደሆነ፣የምታዋየው፣ልቧ የሚያርፍበት ሰው ማጣቷን ያሳብቃሉ ልጥፎቿ። ምንም ማድረግ ባንችል አጠገባችን ያሉ ሰዎችን እናስተውል፣የአንዳንዱ ችግር ''አይዞን'' በሚል ነጠላ ቃል ይቀረፋል። በሰው ረሃብ ቸነፈር የተገረፈ ስንቱ አለ? ብዙ የነገ ተስፋዎቻችንን አይነጠቁብን፤የአንዳችን መኖር ለሌላኛችን ነው!! የነፍሳችን ባለቤት ፈጣሪ ነውና እስከ ፈቀደልን ጊዜ እንቆይ!!

Via Tiblets Tesfaye Ritha

@ETHIOSTUDENTS
@ETHIOSTUDENTS


ሰው ለራሱ ጥቅም
እኔን የማይመጥን ውሸት ቢለቃቅም
ተይው ፊት አትስጪው
እኔን የመሰለ ሸጋ ነው ምታጭው
ይልቅ ብለሽ ጠንቀቅ
እኔን ብቻ ማድነቅ
ልማድሽ አድርጊ
ነገረኛን አምነሽ ነገር አትፈልጊ

ይልቅ አስቢበት
አዋቂ ያስመሰለኝ ጺሜ መከረኛው
ሸሚዝ ማይጣላው አቋሜ ጉደኛው
ሚስት ሳያሳጣኝ ይሉኛል ብቸኛው
መለስ ካላልሽ አንዴ
ሊቀሙሽ ነው ውዴ

ለራስሽ ብዬ ነው

ማኩረፍ ላያዋጣሽ
መፀፀት አይቅጣሽ

ብቻ ፈራሁልሽ

እንዳይቆጭሽ ሲያታልሉሽ
ፈዝዘሽ ቁመሽ እንዳይቀሙሽ

በኋለ አጥተሽኝ ደጅ ከምትጠኚ
እድል አያምልጥሽ በይማ ፊጠኚ


ይቀጥላል...

👨‍🦼አካልህ በድኖ አንደበትህ ታስሮ
መከራህ ቢበዛ ችግር ተደማምሮ
መሸከም ቢያቅትህ ጫንቃህ አቅም ቢያጣ😔😔😔😔😔😔😔
መኖር ቢሰለችህ ምን ሀዘን ቢመጣ
መኖር ይቀጥላል የመጣው ቢመጣ።


ገንዘብ ቢበዛለት በምቾት ቢደለቅ
በደስታ ቢጨፍር በሳቅ ቢፍለቀለቅ
በሰዎች ቢከበር ስልጣን ላይ ቢወጣ
ፈላጭ ቆራጭ ቢሆን ምን ነገር ቢያመጣ
ሀገር ቢያስተዳድር አለምን ቢገዛ
መሞት ይቀጥላል መኖርም እንደዛ
🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹


                   ከአዒሻ

📱ከወደዱት ለወዳጅዎ ያጋሩት!📱


፨፨፨  የልብ_ቋንቋ ፨፨፨
==========================
   💜  የህይወት ጥዕሙ የጠፋባቸው ሰዎች አሉ ። በየእለቱ ተመሳሳይ ህይወት የሚኖሩ እና በህይወታቸው ውስጥ አዲስ ክስተት አጥተው ስልቹ የሆኑ ሰዎች ።  ዘውትር ተመሳሳይ ህይወት ፣ መግባትና መውጣት ፣ መብላትና መጠጣት ብቻ አዲስ ህይወት የሌለበት ስልቹ አለም ።

    💜  እነዚህ ሰዎች ህይወትን በማሰብ ( አይምሮ ) ብቻ የሚኖሯት ሰዎች ናቸው ። ምክንያቱም የሰው ልጅ የልብ ቋንቋ ካልገባው በአይምሮው ብቻ ከኖረ ህይወት ትርጉም የሌላት ባዶ ስለምትሆን ህይወትህን በአይምሮህ  ብቻ ሳይሆን በልብህ ኑራት ፣ ህይወትህን በልብ ቋንቋ ስትመራት አይምሮህ ታላቅ ተፈጥሮን ያሳይሀል ። በአይምሮህ ስትኖር  ፖለቲከኛ ፣ ዘረኛ ፣ አክራሪ.....  ወዘተ  ትሆናለህ ፣ በልብህ ስትኖር ግን መንፈሳዊ ትሆናለህ ።

    💜  በልብህ ስትኖር የህይወት ጣዕሙ ይገባሀል ፣ የፍቅር ሙቀቱ ይሰማሀል ። ተልዕኮህን ስታውቅና በተሰጦህ ስትኖር የህይወትህ ገዢ ሀይል ከልብህ ይመነጫል ። አይምሮህም የልብህ ታዛዥ ይሆናል ። እናም ተሰጦህን ፈልግ ፣ ራስህንም ፈልግ አግኘውም የዚያን ጊዜ ህይወትህ ከአሰልቺነት ወጥቶ በደስታ ይሞላል።

       መልካም ምሽት    💜

✍🤟🤟


ቃል ይስጠን 🙏

መራቀቅ ባልችልም
ሚስጥር ማወጣጣት
ግን አለሜ እወቂ
ፍቅር አይፈልግም ተራ ባዶ ቃላት
አይን አፋሮች ሆነን
መናገር ብንፈራ
እንባች ይወርዳል
በተራ በተራ
ቃሌን በመጠበቅ
አንቺም ሳታወሪ
ተለያይተን ሳንቀር
ቃል ይሰጠን ፈጣሪ 🙏


#አልገባሽም
:
:
:
ስንለያይ ጊዜ
የየብቻው ጉዞ ገና ሲጠነሰስ፤
አብረን የገራነው የጋራችን ፈረስ፤
ትዝታን ሸክፎ ቤትሽ እንደመጣ፤
ከዛም ከደጃፍሽ አራግፎ እንደወጣ፤
የኋሊት ጎትቶ ሆዴን ሊያላውሰው፤
በሰመመን ስትሄጅ ነግሮኛል ያየሽ ሰው።
:
:
ስንለያይ ጊዜ
ህይወት በኛ ስትከር፤
እንዲው እንደ ዘበት ፍቅራችን ሲሰበር፤
የሀዘን ድንኳን ጥለሽ፤
እንዴት ሆነ ብለሽ፤
እንባሽን ስትዘሪ፤
ደግሞም ከራስሽ ጋር ስትከራከሪ፤
ባላይ እንኳን ባይኔ፤
ያየሽ አርድቶኛል ሁሉን ክንዋኔ።
:
:
ስንለያይ ጊዜ
ያቆራኘን ገመድ እንደተበጠሰ፤
የትካዜው ሾተል ስለቱን አስሎ ካንቺ እንደደረሰ፤
ከዚያም አልፎ ተርፎ እንዶነብሽ እዳ፤
ሁሉን ሰምቻለው ያንቺን ሳሎን ጓዳ።
:
:
ስንለያይ ጊዜ
ደስታ ሚባል ነገር ጥሎሽ እንደሄደ፤
የቀለለሽ ሁሉ ደርሶ እንደከበደ፤
እንኳን እኔን ቀርቶ ዘር አዳም ሚረታ፤
የተከዘን ሚያስቅ ያ ምጥን ፈገግታ፤
ፅልመት መደረቡን፤
ድንገት መለዘቡን፤
አንቺ ባታወሪኝ ያየሽ ሰው ነግሮኛል፤
በሰማውኝ ጊዜም በጣሙን ከፍቶኛል፤
ደግሞም አስቆኛል።
:
:
እውነት ነው አንቺ ሴት፤
እየው ተሰምቶኛል ሁለት አይነት ስሜት።
እያዘኑ መሳቅ እየሳቁ ማዘን፤
ከራሴ ጋር ማውጋት እራሴን መመዘን።
:
:
እያዘንኩኝ ስቄ እየሳቅኩኝ ሳዝን፤
በህሊና ሚዛን ላይ እራሴን ስመዝን፤
የሳቅኩት ባንቺ ነው
እውነቱን መርምረሽ ገልጠሽ ላላወቅሽው፤
መቦረቅ ሲገባሽ በእምባ ለታጠብሽው፤
ገራገር ለሆንሽው።
ያዘንኩት ለራሴ ይብላኝ ያልኩት ለኔው፤
ወርቁ ላልበራልኝ የመዋደድ ቅኔው፤
ለሰጠሺኝ ፍቅር ለጠፋኝ ምጣኔው።
:
:
ሀቅ ነው አንቺ ሴት ...
ያንቺ አይነት ነው እንጂ
ሚገኝ ከስንት አንዴ እሱም ለታደለ፤
የኔ አይነት ሰውማ
የትም በሄድሽበት በየቦታው አለ።
:
:
አልገባሽም እንጂ
የእኔ 'ና አንቺ ቅኔ ወርቁ ቢበረበር፤
ፍቅርን ከቃል በስቲያ ሆኖት ማያቅን ሰው
አጥቻለው ብለሽ አታለቅሺም ነበር።
አልተረዳሽ እንጂ እውነቱን ብታውቂ፤
እንኳን ልተክዢ
ካንጀትሽ ነበር ሰርክ ምትስቂ።
ሽፍንፍኑን ገልጠሽ ብትረጂ ኖሮ፤
በደስታ ነበረ
ጥለሺኝ ምትሄጂው ገና ያኔ ድሮ።
:
:
እናልሽ አንቺ ሴት...
ዋጋሽ የከበረ ገራገር ቀይ ዕንቁ፤
የተለባበሰው ሲገለጥ ድብቁ፤
የኔ ፋንታ ማልቀስ ያንቺም ነው መሳቁ።

#ሄኖክ_ብርሃኑ (@Gemhalya)
@Gemhalya


#ለፈገግታ😁

🙅‍♀እሺ አትበይ አሁን🙅‍♀

አፈቀርኩሽ ብልሽ

ሁሌ ብከተልሽ

እያልኩኝ ብነግርሽ

ካላንቺ አልኖርም

ሳላይሽ ከዋልኩኝ እህል ባፌ አይዞርም

የተጎዳው መስሎሽ እየተሰማሽ ሀዘን

እባክሽ ቸኩለሽ እሺ አትበይ አሁን::
:
:
እንዴት ካልሽኝ ለምን?

ግራ እንዳትጋቢ ልንገርሽ ምክኒያቴን::
:
:
በዚ እሳት ዘመን በዚ ከባድ ኑሮ

ምግብ ስለዘጋኝ ብር ቆጠብኩ ዛሬ
            ታሪክ ተቀይሮ
:
:
እና እሺ ብለሽ ሆዴ ከሚከፈት

መልስሸ ይቆይና ለትንሽ ጊዜያት
         ዘግቶኝ ልኑርበት::🙏

፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠
       
       ✍️ @Gemhalya


❤️❤️ሰበበኛው ልቤ❤️❤️

ለስንት አመት ኖሮ ሆኖ ኩሩ ላጤ

ዛሬ ቢነካካው ትንሽ ፍቅር ቢጤ

ያ ልቤ ከውስጤ ሳይወጣ አምልጦ

ያስጨንቀኝ ጀመር ካምሮዬ በልጦ::
:
:
ባፅኖት ነግሬው ሰላም እንዲሰጠኝ
            በስድብ በቁጣ

ጭራሹን ባሰበት እሷ ስትመጣ::


፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠፠

        ✍️ @Gemhalya


[ማ መ ን ታ ት]
.
አየሽ ልቤ...
ትታህ ሄዳለች| ይለኝና
(መራቅሽን ያስብና)
ሌላ ሴት| ገላ ለመልመድ፤
(ይጀምርና፥ መራመድ...)
ድንገት ያስባል| መንገድ ላይ ቆሞ፣
ማን ያዉቃል| ብትመጪስ ደግሞ!?
(ልጠብቅሽ መሰል...)
.
ይሄዉ|ይሄዉ
አሁን
አሁን
ዛሬ
ዛሬ
(እንደ ትላንት፥እንደ ነገ)
ፀሀይ ወጣች|ፀሀይ ገባች፣
ነፍሴ ሳቀች| ደግሞ ባባች።
ደግሞ መሸ| ደግሞ ነጋ።
ደግሞ አንዲት ሴት|መልከ ሸጋ፤
ሀር ፀጉር|ጠይም ሎጋ፣
(ለነፍሷ ነፍሴን ፈልጋ)
ባይኖቿ እየጠራችኝ፣
(በቅንድቧ በብሌኗ)
አነጋግረኝ?| እያለችኝ።

ለጥቂት ቅፅበት (ለሰከንዶች)
ልቤ ሄደሻል ብሎ፣
ቀልቡን ከ`ሷ ላይ ጥሎ።
ለመሄድ ይሽተዉና፣
ይጨነቃል እንደገና።
.
.
.
.
(እንደገና ይጨነቃል..)
ተስፋ ጠልፎት ይወድቃል።
ብትመጪስ ደግሞ...
ማን ያዉቃል!?
(ልጠብቅሽ መሰል...)
{}

By በቃሉ ሹምዬ
@Gemhalya


✨ለመላው ኢትዮጵያዊያን ሙስሊም ወገኖቻችን በሙሉ እንኳን ለ1444'ኛው የዒድ አል አድሃ (አረፋ) በዓል በሰላም አደረሳችሁ!

            ዒድ ሙባረክ!❤️

@Gemhalya
@Gemhalya


❝ እኔ ያላንቺ መኖር አልችልም︎︎..❞

. .በፍፁም : አልልም❗️
የመኖሬን ዋጋ ፡ ከላባ አላቀልም።
ከጅል አፍቃሪዎች : ቃላት አልዋስም
የ'እኔነቴን ህንፃ : 'ባሸዋ አልቀልስም።

ሂጂ!!..ካለሁበት ቦታ : ለዘላለሙ ራቂ፣
ኩራት የወለደውን ሳቅ : ከፊቴ አትሳቂ!

የሚል ንግግርም 'ካፌ አትጠብቂ።
­❄️

በቃ!!
ስኖር በዚች አለም
ባንድ ሰው አይደለም
ህይወቴ ሚጎድለው. .ህይወቴ ሚሞላው
መኖሬን ምወደው  . . መኖሬን ምጠላው
[ባንድ ሰው አይደለም!]

እንኳን አንድ ይቅርና መላው የአለም ሰው፣
ምንም ቢያስቀይመኝ
የመኖር ፍላጎቴን ቅንጣት አይቀንሰው።
❄️

አዎ..!
ይሄ ነው ሀቄ!
ጥለሽኝ  ስቴጂ : ያለመነፍረቄ
በነገ ማመኔ : ተስፋ መሰነቄ
❄️
በቃ እወቂልኝ..!
ያፍቃሪነት ደሜ
ከ'ግር እስከ 'ራሴ ቢታጨቅ ቢሞላም፣
አንቺን አጣሁ ብዬ
ካምላኬ አልኩዋረፍ ከነፍሴ አልጣላም!
×××××××××××
By @benejigu26

@getem
@getem
@paappii




#የተከፋፈለ_ማንነት_መኖር_ችግር
#Dissociative_identity_disorder
#በማን_ያዘዋል_ፊልም

የተከፍፈለ ማንነት መኖር(DID) የሥነ ልቦና ችግር ሲሆን ሁለትና ከዚያ በላይ ያሉ ከታማሚው ጋር ተዳባይ የሆኑ የራሳቸው ማንነት ያላቸው ስብእናቸው በአንድ ሰው ውስጥ ሲፈጠር ነው። የአንድ ሰው ማንነት መለያ ወደ ተለያዩ  ሁለት እና ከዛ በላይ የስብዕና አይነት ሲከፍፈል እና እነዚህ የተለያዩ ማንነቶች እየተቀያየሩ ግለሰቡን ሲቆጣጠሩ የሚፈጠር የሥነልቦና ችግር ወይም የግለሰቡ የማንነት፣ ትውስታ እና የንቁነት መገለጫዎች የማቀናጀት እና በተለያየ አቅጣጫ የተዋቀረ አንድ ማንነት ያለመኖር ችግር ሲሆን በዚህ ችግር የሚጠቁ ሰዎች ዋናው ማንነት የግለሰቡን ከቤተሰብ የተሰጠ ስም የሚይዝ ቢሆንም በአብዛኛው በራሱ ምንም የማያደርግ፣ ጥገኛ፣ በድብርት እና የወንጀለኝነት ስሜት የሚጠቃ ሲሆን ሌላኛው ማንነት ሰውየውን በሚቆጣጠር ግዜ ይሄው  ክፍል የራሱ የተለየ ታሪክ፣ የራስ ምልከታ እና ማንነት ሊኖረው ሲችል በተጨማሪም የቃላት ምርጫ፣ ስምን ጨምሮ የሚገልፀው ፆታ፣ እድሜ፣ ጠቅላላ እውቀት እና አጠቃላይ ፀባይ ከዋናው ጋር የሚለያይ ሲሆን እነዚህ ለውጦች የሚመጡት ያለምንም የህክምና ሁኔታ እና ዕፅ መውሰድ መሆኑ ልዩ ያደርገዋል።

እነዚህ ሌሎች ማንነቶች ወደ ላይ ለመምጣት ወይም ሰውየውን በግል ለመቆጣጠር የተለየ ሁነት ወይም አስጨናቂ ሁኔታዎች ምክኒያት ሊሆን ሲችል በብዛት እነዚህ ማንነቶች እርስ በርሳቸው እንደማይተዋወቁ ቢያስመስሉም የእርስበርስ ግንኙነት እንዳይፈጠር ማለትም የጋራ ውይይት እንዳይኖር በጥንቃቄ ይጠባበቃሉ።
ይህ ችግር ከአጠቃላይ ማህበረሰቡ 1 ከመቶውን የሚያጋጥምና በአብዛኛው ሴቶችን ሲያጠቃ ይታያል።

የችግሩ ምክኒያት
በህፃንነት የሚያጋጥም መጥፎ/አስቸጋሪ ሁኔታ (ጥቃት፣ በደል) ከዚህ የስነልቦና ችግር ጋር የሚያያዝ ሲሆን  ጥናቶች እንደሚያሳዩት 90% የሚሆኑት የችግሩ ተጠቂዎች በህፃንነታቸው ተመሳሳይ የበደል ታሪክ አላቸው። እነዚህ ጥቃቶች አካላዊ፣ ስሜታዊ ወይም ወሲባዊ ጥቃቶች ሊሆኑ ይችላሉ። በሌላ በኩል ችግሩ ከአደጋ፣ ጦርነት፣ ቤተሰብን በህፃንነት ማጣት እና በበሽታ ምክኒያት የተፈጠረ የተራዘመ ከቤተሰብ መነጠል ጋር ሊያያዝ ይችላል።

ህክምና (Therapy)
የዚህ ችግር ብቸኛ መፍትሄ የሥነልቦና የምክክር አገልግሎት ሲሆን አላማውን በግለሰቡ አስቸጋሪ እና ህመም የሚፈጥሩ ትዝታዎቹን እንዲያብላላ እና እንዲገልፅ መርዳት፣ ከችገሮችን የመቋቋም እና የህይወት ብቃት እንዲያሳድግ፣ የመፈፀም አቅሙ እንዲመለስ እና የተሻሻለ ግንኙነት ኢንዲኖረው መርዳት ላይ በማድረግ እንደ ችግሩ ሁኔታ የሚስማማ የምክክር ፍልስፍና እና ስልት በመከተል የሰውየውን ማንነቶች በማገናኘት ወደ አንድ እንዲዋሄዱ መርዳት ይቻላል።

ግን ከዚህ ፊልም በፊት አንድ የታዋቂው አሜሪካዊ ፀሀፊ ሲድኒ ሺልደን ድርሰት የሆነውና Tell me your dreams የተሰኘው በአማርኛ የተተረጎመው ህልምሽን አጫውቺኝ የተሰኘው መፅሀፍ ስለዚህ የአእምሮ በሽታ ይበልጥ የሚያብራራና የሚገልፅ ሲሆን ፊልሙ ይበል የሚያስብል ሲሆን ይሄን ፊልም ያያችሁት ይበልጥ ነገሩን ለመረዳት ከላይ የገለፅኩትን መፅሀፍ እንድታነበት እጋብዛለሁ።

የአእምሮ ህመም ምን ያክል ውስብስብ ምን ያክል አስቸጋሪ ምን ያክል ትኩረት የሚሻ እውነትም "ያለ አእምሮ ጤና ጤና እንደሌለ" የሚያሳይ ጥሩ እይታን የሚፈጥር ፊልም ነው።


እንማር dan repost
አንዲት ቀይ ልጅ የጀበና ቡና ይዛ መጣች። ከቡናዋ ጋር ምን እንዳቀመሰችኝ አላውቅም ከዛ ቡኃላ ልክ አይደለሁም።

መንገድ ላይ የጀበና ቡና የምትሸጥ ሴት ማፍቀርኮ ችግር የለውም። ችግሩ ፉክክርህ ከግንበኛ፣ ከተራ አስከባሪ፣ ከአናፂ ምናምን ጋር ነው።

የማስተርስ ዲግሪ ሰርቼ...ስምንት አመት ሙሉ የባንክ ስራን ቀጥቅጨ...ያሰብኩትን ሁሉ ጨብጬ...የአልማዝ ልብ ግን ከመንገድ ወያላዎች ለይቶ አያዬኝም።

"የሴት ልጅን ልብ የሚያሸንፈው ያልተጫወተ ነው" የሚለው የእማዬ ምክር እዚህ ላይ አይሰራም። በኑሮ ሰባት እጥፍ የምበልጣቸውን ሰዎች በምላስም በልጨ መገኘት አለብኝ። ችግሩ መሰሎቼ ስላልሆኑ ያ ባለጌ ሽመልስ እንደ ኮሜዲያን የሚታይበት ዳስ ውስጥ የኔ ቀልድ እጅ እጅ ይላቸዋል። አንዳንዶቹማ እያወራሁ በፈጠጣው አቋርጠውኝ ሁላ ሌላ ወሬ ይጀምራሉ። ሽመልስ ማውራት ሲጀምር ግን አልሚ ራሱ ቡና መቅዳቷን ቆም ታደርጋለች (ስትስቅ እንዳያስደፋት መሆኑ ነው። ገና ሲጀምር እንደሚያስቃት እርግጠኛ ነች።) እኔ በበኩሌ ከሚያሰቀው ነገሩ ብልግናው ስለሚበዛብኝ ሁሌ እንደተሸማቀኩ ነው።


ይለዋል አንዱ ሰው መስሎት።


#አበስ_ገበርኩ
:
:
እንደተለያየን ...
ንቃቃቷ ሞላ ጣለች ገፋ ከሏን፤
ነዶ ሰበሰበች ጠል ወርሶት አካሏን።
እግሯ ባ'ለት ፀና ሻረች መወላገድ፤
ተደላደለላት ስርጓጎጡ መንገድ።


እንደተለያየን ...
ዕድል ተከተላት፤
ንዋይ ሲሳይ ምንዳ ባንድነት ነደላት።
ራስ ሆነች ቁንጮ ፈላጊዋ ጋመ፤
የማይደገመው እየደጋገመ፤
መዳፏ ላይ ታየ፤
የሚያያት ፈዘዘ የነካት በረየ።


እንደተለያየን...
ገዛት ህያው ቃሉ፤
ሰላም ሰፈነለት ሰላም ያላት ሁሉ።
የአፏም ቃል ፀና ይሁን ስትል ሆነ፤
ፈሪው ድፍረት በዛው አንጋሴው ጀገነ።
ተገለጠ ጥርሷ፤
ይስረቀረቅ ጀመር ቱማታው የልብሷ።
እንደ ጀምበር ፈካች፤
በሳቋ ካካት ሰማይ ጫፉን ነካች።


እግዚኦ ምህረት ለኔ አበሳ ለገበርኩ፤
በደል ሀጥያቷ ለካስ እኔ ነበርኩ።
@Gemhalya


እኔ ዛፉ....
ያማረለት ቅርንጫፉ
አንቺ ቆራጭ....
ያማረልሽ የእጅሽ ምላጭ
ከፍሬዬ ጓጓሽ መዝገን
ገዘገዝሽው ምስኪን ስሬን 🩸
በዚ አልበቃሽ...
ወጣሽብኝ ተንጠልጥለሽ....
ጎድቶኝ ኖሮ መገዝገዜ
ተገነደስኩ ከ ገዛ ወንዜ 😭
.....አብረን ወደቅን...🍁


@Gemhalya
ዳዊት ጌታቸው


ክርስቶስ ተንስአ እሙታን፤
    በዐቢይ ኃይል ወስልጣን፤
         አሠሮ ለሰይጣን፤
         አግዐዞ ለአዳም፤
               ሰላም፤
         እምይእዜሰ፤
                 ኮነ፤
         ፍሥሐ ወሰላም።
   
📖 ተነስቷል!  እንደ ተናገረ፤ ተነስቶአልና በዚህ የለም፤ የተኛበትን ስፍራ ኑና እዩ:: ማቴ (28:6)

📖 “ሕያውን ከሙታን መካከል ስለ ምን ትፈልጋላችሁ፤ ተነሥቶአል እንጂ በዚኽ የለም" ሉቃ 24፥5

"አሁን ግን ክርስቶስ ላንቀላፉት በኩራት ሆኖ ከሙታን ተነሥቶአል።"
(1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 15:20፤)

እንኳን ለብርሃነ ትንሳኤው በሰላም አደረሰን!❤️


#እንቶ_ፈንቶ



««በጭራሽ አትምጪ በፍፁም አልመጣም፣
የፍቅርን ፅዋ ዳግም እንደገና ባብሮነት አንጠጣም።
ተቀብሯል ነገርሽ ተቀብሯል ነገሬ፣
በይ ትፊኝ አንቅረሽ ተፋውሽ አንቅሬ።»»


የሚል ግጥም ልፅፍ ብዕሬን ስመዘው፣
እጅ ለካ አይፅፍም ልብ እስካላዘዘው።


ቢፅፍም ቢጭርም በንዴት ተገፍቶ፣
ሀረጉ አርቲ ቡርቲ ስንኙ እንቶ ፈንቶ።

#ሄኖክ_ብርሃኑ
@Gemhalya


ከሮበርት_ሙጋቤ ንግግሮች ውስጥ 👇

➊.ደሞዝ የመጣ ቀን ዶሮ ትበላለህ።
:
➋.በማግስቱ ደሞዝ ሲያንስብህ የዶሮ ውጤት (እንቁላል) ትበላለህ።
:
➌.በቀጣዩ ቀን ደሞዝህ የበለጠ ሲሳሳ ደግሞ የዶሮ ምግቦችን (በቆሎ እና ገብስ) ትመገባለህ።
:
➍.በተከታዩ ቀን ደሞዝህ ሲሟጠጥ ደግሞ አንተ እራስህ ዶሮ ትሆንና የምትበላውን ነገር ፍለጋ ወዲያ ወዲህ በመባዘን ጊዜህን ታሳልፋለህ።
:
#ሮበርት_ሙጋቤ!
♡ ㅤ   ⎙ㅤ  ⌲   🔔                    
ˡᶦᵏᵉ    ˢᵃᵛᵉ  ˢʰᵃʳᵉ unmute


ተረኛው ጨባጭ!

“አንድ ሰው ሕጻን ሆኖ ሲወለድ እጁን (መዳፉን) ጨብጦ ነው፤ አንድ ሰው ሸምግሎ ሲሞት ደግሞ እጁን (መዳፉን) ዘርግቶ ነው” ይላል ካልታወቀ ምንጭ የተቀዳ አባባል፡፡

ለአንድ ሕጻን አንድን ነገር በእጁ አስይዛችሁት ካወቃችሁ ልጁ የያዘውን ነገር በቀላሉ እንደማይለቅ ትደርሱበታላችሁ፡፡ አንድ ሕጻን ልጅ እጁን ጨብጦ መወለዱ ሁሉን ለመያዝ፣ ሁሉን በእጁ ለማስገባትና ሁሉን ነገር በቁጥጥሩ ስር ለማድረግ የመሞከሩ ምልክት ነው፡፡

አንድ ሰው ሸምግሎ ሲሞት እጁን ዘርግቶ መሞቱ ደግሞ ሁሉን አይቶት፣ ሞክሮት፣ ጨብጦና “የእኔ ነው” ብሎ በመጨረሻ ምንም ነገር የእርሱ እንዳልሆነና አንድ ቀን ሁሉም ነገር ከእርሱ ቁጥጥር ውጪ እንደሚሆን የመገንዘቡ ምልክት ነው፡፡  

እውነታው ይህ ነው፡- ተወልደን በልጅነት ባሳለፍንበት ወቅትና ሸምግለን ከዚህ አለም ወደመሰናበት በምንደርስበት ወቅት መካከል ባሉን እንደ ጥላ በሚያልፉት አመታቶቻችን መያዝና መቆጣጠር በምንችለውና በማንችለው መካከል መለየት አስፈላጊ ነው፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ነገ ሁሉንም ነገር ትተነው እንደምናልፍ በመገንዘብ ሁሉን ነገር የእኛ ለማድረግ ጦር ስንማዘዝ ዘመናችንን እንዳናባክነው እናስተውል፡፡

እጅህ በገባው ነገር ደስተኛ ሁን፣ ለመልካም ነገር ተጠቀምበት፡፡ እጅህ ለማስገባት ያልቻልከውን ነገር ለማስገባት ሞክር፣ ነገር ግን ሁሉን ካልያዝኩ በማለት ስትሟገት በጦርነትና በፍርድ ቤት ዘመንህን አታስበላ፡፡ የአለምን ምድር ሁሉ ጨብጠን የእኛ እናደርጋለን ብለው የነበሩ ምእራባውያን ቅኝ ገዢዎች የጨበጡትን ሁሉ ቀስ በቀስ እየለቀቁ እንደሄዱ አትዘንጋ፡፡ እንዲያውም የእነሱንም ቀስ በቀስ የሚያስለቅቃቸው ሁኔታ እየተጋረጠባቸው ነው፡፡

ለጊዜው ነው እንጂ ምንም ነገር በቋሚነት የአንተ አይደለም፡፡ የእኔ ነው ብለህ የምታስበው ሁሉ ለጊዜው በአደራ የተሰጠህ ነው፡፡ ዛሬ አንተ የምትኖርበትን ቤትና መሬት ትናንት የእኔ ነው ብሎ የሚኖርበት ሰው ነበር፡፡ ዛሬ ግን የአንተ ነው፡፡ ነገ ደግሞ ይህንን ስፍራ ሌላው ተረኛው ጨባጭ ይረከበዋል፡፡ ቁም ነገሩ በዘመንህ የጨበጥከውን ነገር የመልቀቂያህ ጊዜ እስከሚመጣ ድረስ ለመልካም ዓላማ የመጠቀምህ ጉዳይ መሆኑን ላስታውስህ፡፡

✍ዶ/ር እዮብ ማሞ

@Gemhalya

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.

164

obunachilar
Kanal statistikasi