📚📚 #የአንድ_ሺህ_ዲናሩ_ገጠመኝ
✍ አሚር ሰይድ
መነሻቸውን ከበስራ አድርገው መድረሻው ወዳልታወቀ ስፍራ ተቅጣጭተዋል። ሐዲስን የሚያውቅ ሰው አለ ተብለው ከምንጩ ሊቀስሙ ፈልገዋል። ጉዞው አድካሚ ነው። መንገዱም ሲበዛ የረዘመ። በረሀውን አቋርጠው ሲጨርሱ ገደል ገደሉን ሲያልፉ ጋራ ይጠብቃቸዋል። ዕድሜ ያቸው የገፋ አንድ አዛውንት አብረው በፍጥነት ይራመዳሉ። በዕውቀት የመጠቁ ዓሊም ናቸው። ኢማሙል ቡኻሪ ይሰኛሉ። ከእልህ አስጨራሽ ጉዞ በኋላ ከተማውን ለቀው በመውጣት በጀልባ ተሳፍረው ባህሩን ያቋርጡት ይዘዋል። አንድ ሺህ ዲናር በከረጢታቸው ቋጥረው ከቦርሳቸው አኑረዋል። ከጎናቸው ለተቀመጠው ሰው ስለያዙት ገንዘብ ነግረውታል።
ገንዘብ የመያዛቸውን ወሬ የሰማው ሰው ቀይሉላ ሰዓት ወገቡን ከመጋደሚያው አሳርፎ ከእንቅልፉ እንደነቃ ስቅስቅ ብሎ አያለቀሰ እሪታውንና ኡኡታውን ያሰማ ጀመር። ልብሱን እየቀዳደደ ፊቱን እየቧጨረ ጭንቅላቱን እየመታ መሬት ላይ ይንከባለል ጀመር። ሰዎች ሁኔታውን ሲያዩ ግራ ተጋብተው ምን እንደሆነ ጠየቁት።
አንድ ሺህ ዲናር ከነቦርሳዬ ጠፋ አላቸው። ለካስ የኢማሙን ብር ከጀሎ ኖሯል።
.....በመርከቡ ውስጥ ያሉት ተሳፋሪዎች አንድ በአንድ እየተፈተሹ ገንዘቡን ያፈላልጉት ጀመር። ኢማም አል-ቡኻሪ በከረጢቱ ያስቀመጡትን ገንዘባቸውን አውጥተው ሰው ሳያያቸው ወደ ባህሩ ወረወሩት። መርከቡ ላይ የተሳፈሩት ፈልገው አፈላልገው አንድ ሺህ ዲርሀሙን ሲያጡ ተወሰደብኝ ብሎ የሚጮኸውን ሰው ወቅሰውና ሰድበው ከአጠገባቸው አገለሉት።
ከመርከቡ እንደወረዱ ሽማግሌው ሰው ወደ አማም አል-ቡኻሪ ተጠጋና ከበስራ ይዘውት የመጡትን አንድ ሺህ ዲናር የት አንዳደረጉት ጠየቃቸው።
“ወደ ባህር ወረወርኩት” አሉት።
"ይህን ታላቅ ገንዘብ በከንቱ ሲጠፋ ማየት አንዴት አስቻለህ?" አላቸው።
ኢማሙም እንዲህ አሉ "የአላህ መልአክተኛ ﷺ
ሐዲስ በመሰብሰብ ዕድሜዬን ሙሉ እንደፈጀሁ ታውቃለህ። ዓለምም ታማኙ የሐዲስ ሰው እያለ ይጠራኛል። ታዲያ በገዛ ሀቄም ቢሆን በስርቆት ተወንጅዬ አማናዬን አጥቼ የደከምኩበት የረሱል ﷺ ሀዲስ ተቀባይነት እንዳይኖረው ላደርግ አይገባም። በሕይወቴ ያገኘሁትን ውድ ዕንቁ ታማኝነትንና ፍትሀዊነትን ለጥቂት ዲርሃም ብዬ አንዴት አጠፋዋለሁ? "
ብለዉ መለሱለት
ምንጭ☞ታሪኮችን ተርክላቸዉ መፅሀፍ
join👇👇👇
t.me/IslamisUniverstiy_public_group
t.me/IslamisUniverstiy_public_group
✍ አሚር ሰይድ
መነሻቸውን ከበስራ አድርገው መድረሻው ወዳልታወቀ ስፍራ ተቅጣጭተዋል። ሐዲስን የሚያውቅ ሰው አለ ተብለው ከምንጩ ሊቀስሙ ፈልገዋል። ጉዞው አድካሚ ነው። መንገዱም ሲበዛ የረዘመ። በረሀውን አቋርጠው ሲጨርሱ ገደል ገደሉን ሲያልፉ ጋራ ይጠብቃቸዋል። ዕድሜ ያቸው የገፋ አንድ አዛውንት አብረው በፍጥነት ይራመዳሉ። በዕውቀት የመጠቁ ዓሊም ናቸው። ኢማሙል ቡኻሪ ይሰኛሉ። ከእልህ አስጨራሽ ጉዞ በኋላ ከተማውን ለቀው በመውጣት በጀልባ ተሳፍረው ባህሩን ያቋርጡት ይዘዋል። አንድ ሺህ ዲናር በከረጢታቸው ቋጥረው ከቦርሳቸው አኑረዋል። ከጎናቸው ለተቀመጠው ሰው ስለያዙት ገንዘብ ነግረውታል።
ገንዘብ የመያዛቸውን ወሬ የሰማው ሰው ቀይሉላ ሰዓት ወገቡን ከመጋደሚያው አሳርፎ ከእንቅልፉ እንደነቃ ስቅስቅ ብሎ አያለቀሰ እሪታውንና ኡኡታውን ያሰማ ጀመር። ልብሱን እየቀዳደደ ፊቱን እየቧጨረ ጭንቅላቱን እየመታ መሬት ላይ ይንከባለል ጀመር። ሰዎች ሁኔታውን ሲያዩ ግራ ተጋብተው ምን እንደሆነ ጠየቁት።
አንድ ሺህ ዲናር ከነቦርሳዬ ጠፋ አላቸው። ለካስ የኢማሙን ብር ከጀሎ ኖሯል።
.....በመርከቡ ውስጥ ያሉት ተሳፋሪዎች አንድ በአንድ እየተፈተሹ ገንዘቡን ያፈላልጉት ጀመር። ኢማም አል-ቡኻሪ በከረጢቱ ያስቀመጡትን ገንዘባቸውን አውጥተው ሰው ሳያያቸው ወደ ባህሩ ወረወሩት። መርከቡ ላይ የተሳፈሩት ፈልገው አፈላልገው አንድ ሺህ ዲርሀሙን ሲያጡ ተወሰደብኝ ብሎ የሚጮኸውን ሰው ወቅሰውና ሰድበው ከአጠገባቸው አገለሉት።
ከመርከቡ እንደወረዱ ሽማግሌው ሰው ወደ አማም አል-ቡኻሪ ተጠጋና ከበስራ ይዘውት የመጡትን አንድ ሺህ ዲናር የት አንዳደረጉት ጠየቃቸው።
“ወደ ባህር ወረወርኩት” አሉት።
"ይህን ታላቅ ገንዘብ በከንቱ ሲጠፋ ማየት አንዴት አስቻለህ?" አላቸው።
ኢማሙም እንዲህ አሉ "የአላህ መልአክተኛ ﷺ
ሐዲስ በመሰብሰብ ዕድሜዬን ሙሉ እንደፈጀሁ ታውቃለህ። ዓለምም ታማኙ የሐዲስ ሰው እያለ ይጠራኛል። ታዲያ በገዛ ሀቄም ቢሆን በስርቆት ተወንጅዬ አማናዬን አጥቼ የደከምኩበት የረሱል ﷺ ሀዲስ ተቀባይነት እንዳይኖረው ላደርግ አይገባም። በሕይወቴ ያገኘሁትን ውድ ዕንቁ ታማኝነትንና ፍትሀዊነትን ለጥቂት ዲርሃም ብዬ አንዴት አጠፋዋለሁ? "
ብለዉ መለሱለት
ምንጭ☞ታሪኮችን ተርክላቸዉ መፅሀፍ
join👇👇👇
t.me/IslamisUniverstiy_public_group
t.me/IslamisUniverstiy_public_group