ምርጥ ጽሑፎች✍️✍️


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


ትልቁ ልማት የሰውን አእምሮ ማልማት ነው።ሌላው ቁልቁለት ነው። የተሰራውን ፎቅ በመድፍ እያደባየ የሚደረምስ ትውልድ ከማፍራት በደሳሳዋ ጎጆ አጠገብ ተቀምጦ " ሃገሬ ኢትዮጲያ፣ ተራራሽ አየሩ" የሚል ዘፈን እያቀነቀነ የሚፅናና ትውልድ ቢኖረን እመርጣለሁ። የልማት የመጨረሻና መድረሻ ግቡ የሰው ልጅ ቁሳዊና መንፈሳዊ ፍላጎቱን በበቂ መጠንና ጥራት እንዲያገኝ ማስቻል ነው፡፡ የልማት ግብን ዳር የሚያደርሰው ያው ሰው እራሱ ነው፡፡

ይህ ሰው በውስጣዊና ሁለንተናዊ መልኩ እንዲለማ በትምህርት ማነጽ ያስፈልጋል! በስነጥበብ መግራት ያሻናል! የለብለብ ትምህርት ሳይሆን ህብሩ የረቀቀና ሀገርና ወገንን የሚያስወድዱ ት/ ቤት፣ በየከተማው ደረጃቸውን የጠበቁ ቤተመጽሃፍትና ሙዜየሞች፤ ትያትር ቤቶችና የኪነት ቡድኖች ለልማት መኖር እጅግ አጋዥም ምስክርም ናቸው፡፡ ሰው በስጋም በመንፈስም እኩል ሊረካ ሲችል ነው ጤናማ ማህበረሰብ ሊፈራና ሊያብብ የሚችለው‼


ምርጥ ጽሑፎች✍️✍️ dan repost
#_የአራዳ_ቋንቋ_ትርጉም
1.ባለ ሞባይል ናት=ቦርጫም ናት
2.ብርቄ=ስጋ ወጥ
3.ወፌ ላላ=ኮት የማያምርበት ቀጫጫ ወንድ
4.ትራንዚት=የክፍለሀገር ልጅ
5.ወርቸቦ =ሸፋፋ ወንድ
6.ሰስፔንስ=ስጋ ጣል ጣል ያለበት ወጥ
7.ሸንኩርት =ልጅ እግር
8.አውራ ዶሮ=አልጋ ላይ ሰነፍ
9.ፈንጅ =ጡት
10.ላቦሮ =ሌባ             
11.ዛፓ =ፖሊስ
12.ልባብ =ልብስ             
13.ትሴ =ሴት                 
14.ፍንዳታ-ዱርዬ
15.ዳፍ =ዳግም ፍንዳታ
16.ኬ 50=የሽማግሌ ፍንዳታ
17.ወመሽ =ወጣት መሳይ ሽማግሌ
18.ብጠማ =ብሄራዊ ጠጮች ማህበር
19.ጌጃ =ፋራ =እርጥብ =እንደወረደ
20.ቡሌ እንጥለፍ =ምግብ እንብላ
21.በቄ =ቦርሳ
22.ጡጢ =ቅምቀማ =መጠጥ
23.እስቴፓ =ዳሌና አካባቢው
24.አርፈው =እየው
25.ደቀሰ =ተኛ
26.ላላ በል =ተረጋጋ
27.ሼባ =ሽሜጉጉ =ሽምትር =ሽማግሌ
28.ጮካ=አራዳ
29.ኩሼ=መተኛት
30.መንጠቆ=ቛጣሪ
31.ከናች =ተካይ =ብዙ ሴቶችን የሚያወጣ
32.የወርቅ ሙዳይ=የሴት ፓንት
33.ቺልቺሎ=ጢንጥዬ የወንድ ብልት
34.ዲጌ ሉጌዋ ሲደላ =ጡትቿ ሲመቹ
35.ጎመን=ኤድስ
36.ዳዉን ሎድ አረገኝ=አወጣኝ
37.ደንገጎ=ዳሌ
38.ትስሚየው=ሚስትየው
39.አቤ እና ከቤ=ግራና ቀኝ ጡት
40.ወላንሳ=ወሲባም
41.ጩባ=ወርቅ
42.ደምቋል=ሰክሯል
43.ይሸክካል=ይደብራል
44.እንደወረደ =እርጥብ=ፋራ
45.ስኔፍ=ሽታ=የጫማ ወይም የብብት ሽታ
46.እንፖሽረው=እንሽጠው
47.ቀለሙዋ=ንቅሳታም
48.ምትኬ=ውሽማ
49.አሠፉ=ወረኛ
50.ውላ=ዱሩዬ
51.ተላላጠች=ጉራ ነዛች
52.ነቄ አለ=አወቀ
53.ማስተር ኪ=ከንፈር
54.ሮማንስ=ፓስታ
55.አዳብለው=ሼር አድርገው
56.ጫነች=አረገዘች
57.ሸቀጥ/ ላጃ=የወንድ ልጅ እቃው
58.ቦርኮ=ለማኝ
59.ጃሬ መቱኝ=ሰረቁኝ
60.ፑንቲና ተኮሰ=ጋለ=ነቀለ
61.ፎጋሪ =ኮሚክ
62.ሾዳ =ጫማ
63.ጨማቂ =ወረኛ
64.ነፍሱን አያቅም =ዘንጧል
65.ጭቃ ሽኖ =አይነምድር
66.ላሽ በል=ሂድ=ንካው=እንዳላየ ሁን
67.ሽምጣጭ =ውሽታም
68.ቂንጬ =ሴት            
67.በቻይንኛ=በአሽሙር
68.እሙሙ=የሴት እቃ
69.ከች አሉ =መጡ
70.አንፎጋገር=አንወሻሽ
71.ጋቢና=ፊት
72.አላምጠው የተፉት=አስጠሊታ=አስቀያሚ
73.ፎጣ ፊት=ቡግራም
74.ቴስትኒ =ጭንቅላት
75.ኢቢሲ=ውሸታም=ወረኛ
76.እልል የተባለለት =የተጨበጨበለት
77.መቀፈል=ኮይን መቀበል
78.ቦከመ=ሰረቀ
79.ዱቅ አለ=ተቀመጠ
80.አርካ=ጉራ
81.በአልፋ ወረደ=መኪናው ሳይቆም ወረደ
82.ኣርፋ=መኪና ላይ መንጠልጠል
83.እጥፍ አለ=አቋርጦ መረሸ
84.ኤቨረዲ=ዘጠነኛ ክፍል ላይ ብዙ የደገመች
85.በጠሳት=ድንግልናዋን ገረሰሰ
86.ጥቂ =ስፖንዳ =ጢዝ
87.ለማስክ ነው =ለማስመሰል ነው ::
88.ጨላጣ=የድሮ አራዳ
89.ቂፍሬ= ጨፋሪ=ሙደኛ
90.ቀሚስ=ሴት ልጅ
100.አርፋታለው=አውቃታ ለው
101.ልከርካት=ልጀነጅና ት=ላግባባት
102.ገጀረች=እምቢ አለች
103.ሾዳ ጥፊ=ጫማ ጥፊ
104.መቃ=አንገት
105.ጩባ=ወርቅ
106.መንጩ=መቀማት
107.ሸቤ=እስር ቤት
108.ፋርጣ=ፋራ=የማይባትት=የማይገ ባው
109.ልደቅስ ነው = ልተኛ ነው
110.ቀዩን ተጫነው=አፍህን ዝጋ=ስልኩን ዝጋ
111.ሞተር ነከሰች=ለገዘች
112.ሞተር አስወረደች=ያረገዘችውን አስወረደች
113.ድንቡሎ=5 ሳ.
114.ቼላ-50 ሳ.
115.ጢና ወይም ፋርዳ=5 ሳ.
116.ዲናሬ=10 ሳ.
117.ከርክ=25 ሳ.
118.ኤካ=1 ብር
119.ዱ=2 ብር
120.ትሪስ=3 ብር
121.ኳትሪስ=4 ብር
122.ቢጫ=5 ብር
123.ቢቻ=6 ብር
124.ከዘራ=7 ብር
═════════❁✿❁ ═════════
💪💯 ሶሻል ሚዲያ ያገኛነውን እውቀት ለሌላውም የምናደርስበት የመረጃ ቋጥ ነውና ይህን ጹሁፍ ካነበባችሁት በኋላ ለሌላውም እንዲደርስ #ሼር ማድረጋችሁን አትርሱ!!!👌የቴሌግራም ቻናላችንን ግቡና Join አድርጉ ።
https://t.me/joinchat/AAAAAFAtO5kL7-YczXxg_Q


😘ናፍቆት የታባቱ😔
እንኳን ልትናፍቂኝ ፣ በሃሳቤ ላስብሽ ፣ በህልሜ ላልምሽ
ትዝ እንኳ አትዪኝም አጠገቤ ቆመሽ።
እውነት ይመስልሻል ? እንደዚህ ግን ብልሽ ፣
እውነቴንም ቢሆን ፣ በጣም እንዳይገርምሽ ፤
ሚገርምሽ ከሆነ ፣ እውነቱን ልንገርሽ ?
ስተነፍስ ብቻ ፣ ትዝ ትዪኛለሽ❤️‍🩹❤️‍🔥
በልብ ምቴ ልክ ፣ ትናፍቂኛለሽ
ያልተነፈስኩና...ልቤም ያልመታለት ፣
ማሰቡ ማለሙ ፣ ሁሉም ሲያበቃለት ፣
ናፍቆት የታባቱ! ትዝታም እንጃለት!


✅✅ ዛሬም ሰላም መሆን ይቻላል!

✅✅ ዛሬም ሰላምን ማውረድ ፣ በሰላም መቆየት ፣ በሰላም መነጋገር ይቻላል ። ያለፉት መልካም የአብሮነት ጊዜያት ቢያበቁም ዛሬ በሰላማዊና ጥሩ ሁኔታ ግንኙነትን ማስኬድ ይቻላል ። በተበደልኩ ስሜት ለበዛ ጥላቻ መሰናዳት አያስፈልግም ፣ የማይረባ እልህ መገባት አያዋጣም ። መለያየቱ የተሻለ ምርጫ እስከሆነ ድረስ ያለፉትን አስደሳች ጊዜያት በመዘንጋት ክፋትን ብቻ መቁጠር ፣ በአሉታዊ መንገድ ብቻ መፈረጅ ጤነኛ አመለካከት አይደለም ። መሆን ስላለበት ሆኗልና ያለፈ ግንኙነትን እንከን ብቻ መፈለግ ዋጋ የለውም ።

✅✅ አዎ! ጀግኒት..! ምንም ቢሆን የሆነ ጊዜ የደስታሽ ምክንያት እርሱ ነበር ፤ ሲንከባከብሽ ፣ ሲያዝንልሽ የነበረው ሰው እርሱ ነው ። ሁኔታዎች የግንኙነቱን ቀጣይነት ባለመፍቀዳቸው ማብቃቱ እንዳለ ሆኖ ፣ ልዩነቱም በስምምነትና በፍቅር መሆን ይችላል ። ከዛም በኋላ ሰላማዊ ግንኙነት መፍጠር ፣ ከተበዳይነት ስሜት መውጣትና የተረጋጋ ሰላማዊ ግንኙነት መፍጠሩ ለሁለቱም አካል እጅግ ተመራጭ አካሔድ ነው ።

✅✅ አዎ! በውስጥህ ቂምን አዝለህ ፣ ለበቀል እየተንደረደርክ መቼም የተረጋጋ ህይወት ሊኖርህ አይችልም ። በዳይ ሆንክ ተበዳይ ፣ ጎጂም ሆንክ ተጎጂ ከፀፀት የምትድነው ፣ ወደፊት የምታስበው ፣ የተሻለ የምታደርገው ፣ ጥሩ ተማሪ የምትሆነው በይቀርባይነት ስትታነፅ ፣ በደልን ስትተውና ቂምን ስትረሳ ብቻ ነው ። አብራቹ በነበራቹ ሰዓት የሚደረግልህን ነገር ካልጠበክ ሰላም የማትሆንበትና ነፃ የማትሆንበት ምክንያት የለም ።

✅✅ ሰው ተጎዳድቶ በይቅርታ ይታረቃል ፤ ምንም ታሪክ አብሮ ያላሳለፈ ሰው በሰዓታት ግጭት ቢጣላ አንድ የሚያደርገውን ፣ የሚያስማማውን ነገር ላያገኝ ይችላል ። ለረጅም ጊዜ አብሮ የቆየ ፣ ብዙ ነገር አብሮ ያሳለፈ ሰው ግን ቢያንስ አንድ የሚያስማማውና የሚያስታርቀው ነገር አያጣም ። ዳግም መስማማት በምትችለው ቁርሾ ሰላምህን አትጣ ።

✅✅ ዛሬም ሰላም መሆን ይቻላልና ልዩነትን በፀጋ ፣ ጉዳትንም በይቅርታ ማለፉን ለእራስህ ብለህ እወቅበት ። ማንም ሁን ብሎ ቢበድለህ ከበዳይነት ነፃ እስከሆንክ ድረስ እራስህን አረጋጋ ፣ ህሊናህን ነፃ አውጣ ፣ ተጠያቂነትን ከእራስህ ላይ አውርድ ።


ከነድካምህ ትጠቅማለህ!
፨፨፨፨፨///////////፨፨፨፨፨
ሰው ከነድካሙ፣ ሰው ከነህመሙ፣ ሰው ከነጉድለቱ ከነክፈተቱ ይጠቅማል። ቢወድቀም ይነሳል፣ ቢጠፋም ይመለሳል፣ ተስፋን ቢያጣ፣ መንገድ ቢስት፣ አዙሪት ውስጥ ቢገባም ዳግም ተስፋን ያገኛል፣ መልሶ ተስፋን ይዘራል፣ ደግም ትክክለኛውን መንገድ ያገኛል። ይሔን ብርታቱን ያገኘው ከራሱ ሳይሆን ከህያው አምላኩ ነው፣ ይሔ ፀጋ እንዲሁ የተሰጠውም አይደለም። ወኔው ታይቶ፣ ፍላጎቱ ተለክቶና ተነሳሽነቱ ተመዝኖ ነው። ተስፋ ቆርጦ ደግም ተስፋን የሚሰንቅ ሰው ቀላል ሰው አይደለም፣ ከጠፋበት ስፍራ የሚመለስ ሰው ማንም አይደለም፣ የህይወቱን ፈተና በፅናት የሚጋፈጥ ሰው ለእራሱ ቦታ የማይሰጥ ሰው አይደለም። የሰው ልጅ ምንም ከማግኘቱና ምንም ከማጣቱ በፊት አንድም በእግዚአብሔር አምላኩ ይመዘናል፣ ሌላም በአምሳያው የሰው ልጅ ይገመገማል። አባት ልጁን ሲያምንበት ሃላፊነት ይሰጠዋል፣ እናት በልጇ ስትተማመን እንደማያሳፍራት ከልብ ታምንበታለች። ሰማያዊው ህያው አባት በልጁ ላይ ያለው እምነት ግን ከዚህ በላይ ነው። ምናልባትም ልክ እንደ አብረሃም አባታችን ልጁ እስከ የእኔ የሚለውን ልጁን እንኳን ለመሰዋት የሚያበቃው እምነትን ይሰጠዋል። ፈጣሪ የፍቃድ አምላክ ነውና ማንም ልቡን ቢከፍትለት ያራራዋል፣ ማንም ልቡን ቢያደነድነውም ፍላጎቱን ያከብርለታል።

አዎ! ጀግናዬ..! ከነድካምህ ትጠቅማለህ፣ ከነህመምና ጉድለትህ ዋጋ አለህ። ዋነኛው ሚዛንህ ያለህ ወይም ያጣሀው ነገር ሳይሆን ሰውነትህ ነው። ማንም ሰው እርሱ ካለበት ደረጃ አንፃር የበታቹን የመናቅና የመጠየፍ መብት የለውም። ብታጣ ሰርተህ ታገኛለህ፣ ብታገኝም ያገኘሀውን መቼ እንደምታጣ አታውቅምና በማጣትም ሆነ በማግኘት መኮፈስም ሆነ አንገትን መድፋት አያስፈልግህም። "እግዚአብሔር ሰጠ እግዚአብሔር ነሳ" ብሎ የመቀበልን ብርታት እስካለህ ድረስ በህይወትህ የማይመጣልህ በጎ ነገር አይኖርም። የሰው ልጅ የጥንካሬው ምንጭ ከሆኑት ውስጥ መቀበልን የመሰለ ፀጋ ከቶ የለም። ብርታቱ እውነታውን የመቀበል አቅሙ ውስጥ ነው፣ ጥንካሬው ታሪኩን መቀበሉ ውስጥ ነው፣ ተስፋው፣ ለውጡ፣ እድገቱ ሁሉ አሁን ያለበትን ተቀብሎ የወደፊቱን መቀየር እንደሚችል ማመኑ ነው። አንተ ለእራስህ ጥሩ ቦታ እስከሰጠህና እራስህን እስከተቀበልክ ድረስ ድክመት እያለብህም ሆነ ስህተት ሰረተህ ሰው ይቀበልሃል፣ ጥሩ ቦታም ይሰጥሃል። በችግር ውስጥ ያላለፈ፣ ስቃይ ያልደቆሰው፣ ፈተና ያልተፈራረቀበት፣ በማጣትና በማግኘት መንገድ ውስጥ ያላለፈ ሰው የለም።

አዎ! እውነታውን መቀበል ባትፈልግም እውነታው ግን ሰውነትህ በራሱ የሆነ ደረጃ ላይ ደካማና አቅመቢስ እንደሚያደርግህ ነው። ነገር ግን የተሰጠህ መንፈሳዊ ፀጋ ከድካምህ በላይ እንድትኖርና ዋጋህን እንድትጨምር ያደርግሃል። ማንም ሰው ያለተስፋ ለደቂቃዎች መኖር አይችልም። ከሀገሩ ወጥቶ ለረጅም ሰዓት የሚሰራው ሰው አንድ ቀን ወደ ሀገሩ ተመልሶ የእራሱንም ሆነ የቤተሰቦቹን ህይወት የመቀየር ተስፋ ስላለውነው፣ ማንም ሰው ዛሬ አቀርቅሮ ችግሩን ችሎ፣ በሰው መገፋቱን፣ ጫናውንና በደሉን ተቋቁሞ አቀርቅሮ መስራቱ ነገ ቀን ይወጣልኛል፣ ነገ ቀና እላለው የሚል ተስፋ ስላለው ነው። ተስፋ በተስፋ እንጂ በምንም ሊተካ አይችልም። ይህ መተኪያ የሌለው ስጦታ ደግሞ እግዚአብሔር አምላክ ነው። ከሰው፣ ካፈራው ንብረትና ከገነባው ዝና በላይ ባጣም ባገኘም፣ በወደቀም በተነሳም፣ በተገፋም በተወደደም ሰዓት ፈጣሪውን ተስፋ የሚያደርግ ሰው መቼም ወድቆ አይወድቅም፣ እንዴትም ባዶ እጁን ሊመለስ አይችልም። "ደካማ ነኝ" ብለህ የበታችነት አይሰማህ፣ "ሃጥዕ ነኝ፣ ጥፋቴ በዝቷል፣ ፈጣሪዬን አሳዝኜዋለሁ" ብለህ ሸሽተህ የማታመልጠውን አምላክህን አትራቅ። ምንም ብትሆን በሰውነትህ ብቻ ለእራስህ፣ ለሰውና ለፈጣሪህ እንደምታስፈልግ እመን።
ግሩም ድንቅ ቀን ይሁንልን! 🌅🌞🏞
(Epha A.)
ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ! 🦋

🔺🔻በYouTube ቤተሰብ ስለሚሆኑ እናመሰግናለን!
SUBSCRIBE NOW! 👇
https://www.youtube.com/channel/UCIZv4h3iDx2C7CGbv9WIkVg?sub_confirmation=1
ምክረ-አዕምሮ/ @MentalCounsel 😊💪


የእራስሽ እቅድ አለሽ!
፨፨፨፨//////////፨፨፨፨
ጫናዎች ሲበረቱ፣ ከየአቅጣጫው ሲያይሉ የእራስሽ እቅድ እንዳለሽ አስታውሺ። ከዚህም ከዛም ግፊቶች ሲበዙ፣ አቋምሽን ሲያብረከርኩ፣ በውሳኔዎችሽ ጣልቃ ሲገቡ፣ በገዛ ህይወትሽ አዋቂ ለመሆን ሲሞክሩ ቆም ብለሽ እራስሽን ተመልከቺ። " እውን እኔ ለእራሴ አንሼ ነውን የሰዎች ሃሳብ ማስፈፀሚያ የምሆነው " ብለሽ ጠይቂ ። ምንምእንኳን የታቀደልሽ ጥሩ ቢሆንም፣ የታሰበልሽ መልካም ቢሆንም አንቺ ለእራስሽ ካቀድሽው ግን ሊበልጥ አይችልም። እራስሽን የምትውቂው አንቺ፣ የምትወጂውን የምትጠይውን የምታውቂው አንቺ። በእራስሽ እንደማትጨከኚ ግልፅ ነውና አንቺ ለእራስሽ ከምታስቢው፣ ከምታዝኚው በላይ የሚያስብልሽና የሚያዝንልሽ እንደማይኖር አስተውዪ።

አዎ! ጀግኒት..! የእራስሽ እቅድ አለሽ። ጓደኛሽ ስላገባች አታገቢም፣ እኩያሽ ስራ ስለቀየረች አትቀይሪም፣ ወዳጅሽ ፍቅር ስለጀመረች አትጀምሪም። ለሁሉም ነገር ብቁና ዝግጁ ስትሆኚ የመጀመር ፅኑ አቋም አለሽ፤ ፍላጎትሽን ጠንቅቀሽ ታውቂያለሽ፤ የመረጥሽው እንጂ የተመረጠልሽ እንደማይበጅሽ ታውቂያለሽ። ማንም ቢሆን እንድትመስይው ይፈልጋል፤ ብቻውን ችግሮቹን መጋፈጥ አይፈልግም፤ ያየውን እንድታዪና እንዳትፈርጂበት ይፈልጋል። በእራሱ ህይወት የከበደውን ባንቺ ህይወት አቅልሎ እንድታደርጊው ይመክርሻል።

አዎ! የአቋምሽ ፈተና፣ የእቅድሽ ፅናት መታወቅ የሚጀምረው ውጫዊ ጫናዎች ሲበረቱና አውቅልሻለሁ ባዮች ሲበዙ ነው። ምክረ ሃሳቦችን እየለየሽ በቀናነት ተቀበይ፣ ትዕዛዝ ሲሆን ግን ለምን፣ እንዴት ማለት ጀምሪ። የአንዱን ሃሳብ ብትፈፅሚ ሌላኛው ማውራቱ አይቀርም፤ የአንደኛውን ምክር ብትሰሚ ሌላኛውም የራሱን ይቀጥላል። የእራስሽን እቅዶች አስታውሺ፣ ደጋግመሽ መርምሪያቸው፣ መጨረስ ያለብሽን ሳትጨርሺ፣ መድረስ ያለብሽ ቦታ ሳትደርሽ የማይሆን ውሳኔ ከመወሰን ተቆጠቢ። ዋጋሽን በእቅድሽ ውስጥ፣ ፍላጎትሽንም በተግባርሽ ውስጥ ተመልከቺው።

አዎ! ጀግናዬ..! " አለማቀድ ፣ ለውድቀት እንደማቀድ ነው " እንደሚባለው ሁሉ ሳታቅድ ስትቀር የሚማርክህ ሃሳብ ብዛቱ፣ የሚገዛህ ትዕዛዝ ማየሉ የማይቀር ጉዳይ ነው። በጫና ውስጥ የተወሰኑ ውሳኔዎች የማይመለከቱህ ጭንቀት ውስጥ ሲከቱህ ትመለከታለህ፤ የብዙ ሃሳቦች ተቀባይ መሆን ከየትኛውም ሳትሆን ያስቀርሃል፤ አቋም አልባ ጉዞ መቋጫ የለውም። መስማት ያለብህን ስማ የተባልከው ሁሉ ግን እውነት እንዳልሆነ ተገንዘብ። ወሳኝ የተባሉ የህይወት መርሆችህን ለይተህ አስቀምጥ፤ የሚረብሹህን ሃሳቦች እየጣልክ ጠቃሚዎቹን እየተቀበልክ በእራስህ መንገድ መኖርህን ቀጥል። እቅድህ የሚተገበር፣ ሃሳብህም በተጨባጭ የሚኖር ይሁን።
ውብ ምሽት ይሁንልን! 🌘🌒💫✨
(Epha A.)
ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ! 🦋

🔺🔻በYouTube ቤተሰብ ስለሚሆኑ እናመሰግናለን!
SUBSCRIBE NOW! 👇
https://www.youtube.com/channel/UCIZv4h3iDx2C7CGbv9WIkVg?sub_confirmation=1
ምክረ-አዕምሮ/ @MentalCounsel 😊💪


ማንም አያዝንላችሁም!
፨፨፨፨////////////፨፨፨፨
ማንም ሁኑ የምትኖሩት የእራሳችሁን ህይወት ነው፤ ምንም አግኙ የእናንተን ነገር በዋናነት የምትጠቀሙት እናንተው ናቹ። የሚገባችሁ ነገር ዛሬ ካላችሁ ነገር የሚበልጥ እንደሆነ ማረጋገጥ እስካልቻላችሁ ድረስ ህይወት የተለመደውን ነገር ትሰጣችኋለች፣ በተለመደው መንገድ ትመራችኋለች፣ የሚመጥናችሁ ቦታ ታደርሳችኋለች። እርግጥ ነው ህይወት ከባድ ነች። በተለይ ሀዘን ሲደራረብ፣ መኖር ትርጉም ሲያጣ፣ ግፊቶች ሲበዙ፣ ብቸኝነት ሲያጠቃን፣ ውስጣዊ ሰላምና መረጋጋት ሲጠፋ ህይወት ከባድ ነች። ክብደቷ የሚቀንሰውም እያንዳንዱን ጥያቄ በጥልቀት መርምሮ ምላሽ በመስጠት ብቻ ነው። ህይወት ትርጉም ካልሰጣችሁ ትርጉሙን ፈልጉ፣ የተፈጠራችሁለትን አላማ መርምሩ፣ ግብ አስቀምጡ። በብቸኝነት ከተቸገራችሁ፣ ሰዎች ከራቋችሁ በቅድሚያ የእራሳችሁ ወዳጅ መሆን ጀምሩ፣ ለእራሳችሁ ጊዜና ቦታ መስጠት ጀምሩ። ሀዘናችሁን መቋጫ አብጁለት፣ ስንፍናችሁን ወደኋላ በሉት፣ ለውስጣዊ ሰላምና መረጋጋታችሁ ትኩረት ስጡ። ሁሌም ቢሆን ጥረታችሁ ለማሸነፍ ይሁን፣ ሁሌም ቢሆን ሙከራችሁ የተሻለ ስፍራ ለመገኘት ይሁን።

አዎ! በሚያሳዝን ሁኔታ ካላችሁበት ከባድ ሁኔታ አንፃር ሰዎች እንዲያዝኑላችሁ፣ ሰዎች ስለእናንተ ተጨንቀው ጊዜ እንዲሰጧችሁ ብትፈልጉም ማንም አያዝንላችሁም። ችግራችሁ የእናንተ ብቻ ነውና ችግራችሁን ለመጋፈጥ የምትወስኑት ውሳኔም የእናንተ ነው። ከእግዚአብሔር ቀጥሎ የሚያስብላችሁ ሰው እራሳችሁ ናችሁ።ሁሌም ቢሆን የሰው ነገር የአንድ ሰሞን ጉዳይ ነው። አንድ ሰሞን ያዝንላችሁ ይሆናል፣ አንድ ሰሞን ሊረዳችሁ ይሞክር ይሆናል፣ አንድ ሰሞን ከጎናችሁ ይቆም ይሆናል ነገር ግን በፍፁም የህይወት ዘመናችሁን በሙሉ ሊያዝንላችሁ፣ ሊደግፋችሁና ከጎናችሁ ሊቆም አይችልም። ምክንያቱም እርሱም እንደእናንተ የሚያዝንለትና የሚደግፈው ይፈልጋልና። የህይወት ዘመን ድጋፋችሁ ፈጣሪያችሁ ብቻ ነው፤ መፅናኛችሁ፣ አሳቢያችሁና ነፃ አውጪያችሁ አምላካችሁ ብቻ ነው። ሰው እንዲያዝንላችሁ አትጠብቁ፣ ሰው ከንፈር እንዲመጥላችሁ አትመኙ። ይልቅ ፈጣሪያችሁ እንዲያስባችሁ ተማፀኑት፣ እግዚአብሔር እንዲመለከታችሁ ጠይቁት። ብትሰበሩ የሚያቀናችሁ፣ ብትወድቁም የሚያነሳችሁ ሃይል አላችሁ ሃይላችሁም ምንጩ የአምላካችሁ መንፈስ ነው።

አዎ! ጀግናዬ..! ያንተ ጉዳይ ትናንት የእራስህ ጉዳይ ነበረ፣ ዛሬም ያንተ ጉዳይ ነው፣ ነገም እንዲሁ የእራስህ ጉዳይ ነው። ሸክም ቢኖርብህ ከብደቱን የምታውቀውም ሆነ የማውረድህን ዋጋ የምትረዳው አንተው። የሰው ልጅ ችግርህን እንዳቅሙ ሊካፈልህ ወይም ሊረዳህ ይችል ይሆናል፣ ነገር ግን የችግርህ መፍትሔ ሙሉ በሙሉ ያለው ባንተ እጅ ነው። "እንዲህ አድርግ፣ እንደዛ አድርግ፣ ይሔንን አቁም፣ ያንን ጀመር" ትባላለህ የተባልከውን ካላደረክ ግን ዛሬም እዛው ትናንት የነበርክበት ስፍራ ትሆናለህ። ያንተ መንቀሳቀስ ጥቅሙ ለእራስህ ነው፣ መቀመጥህም እንዲሁ ጉዳቱ ለእራስህ ነው። በዚህ ሰዓት ካንተና ከፈጣሪህ በቀር ምን እንደሚያስፈልግህ የሚያውቅ ሰው የለም። ተጨንቀህ ይሁን ተረጋግተህ፣ ከፍቶህ ይሁን ነፃ ሆነህ፣ አዝነህ ይሁን ተደስተህ ማንም መረጃው የለውም። ለእራስህ ማድረግ ያለብህን አድርግ፣ በቻልከው ልክ ሰው ባስፈለገህ ሰዓት ለእራስህ ቀድመህ ተገኝ፣ እንዳቅምህ ህመምህን እራስህ አክመው፣ ከሰው በላይ ፈጣሪ እንዲያግዝህ አድርግ፣ እጅህን ለአምላክህ ስጥ። መቆም በሌለብህ ሰዓት አትቁም፣ እግዚአብሔር አምላክህን ተደግፈህ መኖርህን ቀጥል፣ በፈጣሪህ መሪነት ወደፊት መጓዝህን ቀጥል።
ውብ ምሽት ይሁንልን! 🌘🌒💫✨
(Epha A.)
ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ! 🦋

🔺🔻በYouTube ቤተሰብ ስለሚሆኑ እናመሰግናለን!
SUBSCRIBE NOW! 👇
https://www.youtube.com/channel/UCIZv4h3iDx2C7CGbv9WIkVg?sub_confirmation=1
ምክረ-አዕምሮ/ @MentalCounsel 😊💪


የትኛው ነህ?
፨፨//////፨፨
አንዲት ከአባቷ ጋብር የምትኖር ህፃን ልጅ ነበረች። በህይወቷ ደስተኛ አልነበረችም፣ ከሰዎች ጋር ባላት ግንኙነት ትበሳጫለች፣ ትምህርት ቤት በጓደኞችዋ መቀለጃ ሆናለች፣ ለትምህርቷ ትኩረት ሰጥታ መከታተል አልቻለችም፣ በሰዎች የሚደርስባት ጫና እጅጉን እያሳሰባት መጥቷል። በራሷ መንገድ ነገሮችን ለማስተካከል ብትሞክርም አልቻለችም። በስተመጨረሻም ከአቅሟ በላይ ሲሆን ያለችበትን ሁኔታ በሃዘንና ተስፋ በመቁረጥ ስሜት ሁኔታውን መቋቋም እንዳልቻለች ለአባቷ ትነግረዋለች። አባትም ካረጋጋት ቦሃላ በምሳሌ ሊያስረዳት ስለፈለገ አእጇን ይዞ ወደ ኩሽና ይዟት ይገባል። በመቀጠልም ድንች መቀቀል ይጀምራል፣ ድንቹ ከበሰለ ቦሃላም እንደገና እንቁላል ይቀቅላል፣ ከእንቁላሉም ቦሃላ ቡና አፍልቶ ያሳያታል። ህፃንዋም እነዚህ የሚያደርጋቸው ነገሮች ሊገቧት አልቻሉም። ጥያቄውን በተሳሳተ መንገድ እንደተረዳ መገመተ ጀመረች። አባት ግን ጥያቄዋን በሚገባ ተረድቷት ነበር። መልሱንም እንዲሁ በደፈናው ከሚነግራት በምሳሌ አድርጎ በምንም ሁኔታ ውስጥ ብትገባም ሁሌም እያስታወሰችው እንድትኖር በማሰብ እራሷን እንደ ድንች፣ እንደ እንቁላልና እንደ የቡና ዱቄት እንድታስብ ይነግራታል።

በመቀጠልም ይህን በአፅንዖት ያስረዳታል። "ድንቹ በፈላ ውሃ ከመቀቀሉ በፊት ጠንካራ ነበር ከተቀቀለ ቦሃላ ግን ለስላሳ ሆነ፣ እንቁላሉ ከመቀቀሉ በፊት ፈሳሽ ነበረ ከተቀቀለ ቦሃላ ግን ጠንካራ ሆነ፣ ቡናውም ከመፈላቱ በፊት የተፈጨ የቡና ዱቄት ነበር ከውሃ ጋር ተዋህዶ ከተፈላ ቦሃላ ግን ብዙዎች በፍቅር የሚወዱትንና የሚጠጡትን ቡና ሆነ።" አላት። ንግግሩን ቀጠለ፦ "አሁን ያለሽበትን ሁኔታ እንደፈላው ውሃ ውሰጂው እራስሽን ደግሞ በሶስቱ ደንች፣ እንቁላልና የቡና ቦታ አስቀምጪ። የፈላ ውሃ ውስጥ ከመግባትሽ በፊት እንደ ድንቹ ጠንካራ ነበርሽ? ወይስ እንደ እንቁላሉ ለስላሳ ወይም ፈሳሽ ነበርሽ? ወይስ ደግሞ እንዲሁ በእሳት ላይ ተቆልቶ ተፈጭቶና በስተመጨረሻ ለመጠጥነት ለመቅረብ ከውሃ ጋር እንደተፈላው የቡና ዱቄት ነሽ? የትኛው አንቺን የሚወክል ይመስልሻል? ብሎ ድጋሜ ጠይቋት ግራመጋባቷን ስላወቀ ይበልጥ ማብራራቱን ቀጠለ።

እንዲም አላት "ሁሉም ነገሮች በተፈጥሯቸው ምክንያት ለገቡበት የፈላ ውሃ ተገቢውን ምላሽ ሰጥተዋል። እኛ የሰው ልጆች ግን ምንም ከባድ ሁኔታ ውስጥ ብንገባ ከዛ ሁኔታ ስንወጣ የምንሆነውን ማንነት የምንወስነው እኛው እራሳችን ነን። "ጓደኞቼ እያሾፉብኝ ነው፣ ሰዎች የሚሰጡኝ ቦታ ያስጨንቀኛል፣ ትምህርቴ ላይ ማተኮር አልቻልኩም" ብለሽ ልክ እንደ ደንቹ ቀድሞ የነበረሽን ጥንካሬና በራስመተማመን በመተው ልፍስፍስ የመሆኑ ምርጫ ያንቺ ነው፣ እንዲሁም ልክ እንደ እንቁላሉ በዚሁ ምክንያት ይበልጥ ጠንካራ መሆንሽን የማሳየቱ ምርጫ ያንቺ ነው። ከዚህም በተጨማሪ ልክ ከመቆላት ተነስቶ ለመጠጥነት እስከሚደርሰው ቡና እያንዳንዱን የሚደርስብሽን ጫና በመቋቋም በብዙዎች ዘንድ የምትወደጂና የምትፈለጊ ሰው የመሆን ምርጫ አለሽ።" ብሎ አስረዳት። ልጅቱም አባቷ በዚህ መልክ ካስረዳት ቦሃላ በህይወት የሚገጥማትን የትኛውንም ሁኔታ በተለየ መንገድ መመልከት ጀመረች።

አዎ! ጀግናዬ..! አንተስ የትኛው ነህ? ልክ እንደ ድንቹ ለሁኔታዎች እጅ ሰተህ የምትልፈሰፈስ ነህን? ወይስ ልክ እንደ እንቁላሉ ከገጠመህ ከባድ ሁኔታ ውስጥ ጠንካራና የተሻልክ ሰው ሆነህ የምትወጣ ነህ? ወይስ ደግሞ ልክ እንደ ቡናው ብዙ ፈተናንን ተቋቁመህ በማለፍ ተወዳጅና ተፈላጊ ማንነትን የምትፈጥር ነህ? አሁን ምንም ነገር ሊገጥምህ ይችላል ከገጠመህ ነገር ቦሃላ የምትሆነውን ሰው የምትወስነው ግን አንተ ነህ። ማናችንም በምን ውስጥ እንደምናልፍ አናውቅም፣ ማናችንም ነገ ምን እንደሚገጥመን አናውቅም። ነገር ግን አንድ ነገር በሚገባ ልናውቅ ይገባል "በየትኛውም ሁኔታ ውስጥ አልፈን የተሻለ ሰው የመሆንም ሆነ በሁኔታው ተሰብረን የመቅረት ምርጫ አለን።" ትናንትም፣ ዛሬም፣ ነገም ህይወት አልጋ በአልጋ ሆና አታውቅምም ወደፊትም ልትሆን አትችልምና አንተ ከገጠመህ ሁኔታ በላይ እንደሆንክ ለማሳየት ተዘጋጅ። ምንም ቋሚ ነገር በሌለበት ዓለም ቶሎ እጅ ለመስጠት አትንደርደር። ተረጋጋ፣ ደጋግመህ አስብ፣ ሞክር፣ ጥረትህን ቀጥል፣ በከባድ ሁኔታዎች መሃል የተሻለ ማንነትን ለመገንበት ሞክር። ምንም ውስጥ ብትሆን ለውጥና እድገትህን በፍፁም እንዳታቆም።
ግሩም ድንቅ ቀን ይሁንልን! 🌅🌞🏞
(Epha A.)
ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ! 🦋

🔺🔻በYouTube ቤተሰብ ስለሚሆኑ እናመሰግናለን!
SUBSCRIBE NOW! 👇
https://www.youtube.com/channel/UCIZv4h3iDx2C7CGbv9WIkVg?sub_confirmation=1
ምክረ-አዕምሮ/ @MentalCounsel 😊💪


18 40 60 መርህ!
፨፨፨//////////፨፨፨
በአስራ ስምንት ዓመትህ ሰዎች ሁሉ ስላንተ የሚያወሩ፣ አንተን ብቻ የሚመለከቱ፣ የሚከታተሉህ፣ የዘወትር ጉዳያቸው አንተ እንደሆንክ ታስባለህ። በዚህም ልክ ከእራስህ በላይ ሰዎች ስለሚሰጡህ ስምና ከእነርሱ ስለምታገኘው ምላሽ በመጨነቅ ጊዜህን ታባክናለህ፤ እራስህን ከማስደሰት በላይ ለሰዎች ደስታና እርካታ ትልቅ ዋጋ ትከፍላለህ፤ ሰው ምን ይለኛል በሚል ሃፍረት ትታሰራለህ፤ ነፃነትህን ለማወጅ ባሰብክ ቁጥር የሰው ምላስ ከፊትህ ተደቅኖ ትመለከታለህ፤ ባጠቃላይ ህይወትህ በሙሉ ለሰዎች በሚከፈል መሱዓትነት ይሞላል። በአርባ ዓመትህ የሰው ነገር ምንም አይመስልህም፤ ምንም ብትባል ግድ አይሰጥህም፤ ስለፈለጉት ቢያወሩብህ፣ ስምህን ቢያጠፉ፣ ስራህን ቢተቹ፣ አንተን ቢነቅፉህ ምርጫቸው እንደሆነ ይገባሃል። በቀደሙት አመታት ሲያስጨንቁህ የነበሩ ጉዳዮች ማስጨነቃቸውን ያቆማሉ፤ ሌላ የተለየ አጀንዳ ውስጥ ትገባለህ። በስልሳ ዓመትህ የሁለቱንም ልዩነት ማመዛዘን ትጀምራለህ፤ ለሰዎች ብለህ ያጣሀው ነገር ካለ በእርሱ ትቆጫለህ፤ ማንም ግድ በማይሰጠው ጉዳይ ስትጨነቅ እንደነበር ታስተውላለህ፤ የሰዎች ስጋትና ፍራቻ ሁሉ የውሸት እንደነበር ይገባሃል።

አዎ! ጀግናዬ..! መርሁን አስተውል፤ በሚገባ ተረዳው። ብዙዎች ስላላወቁት ይሸወዳሉ አንተ ግን ካወከው ዘንዳ፣ ከተረዳሀው፣ ከገባህ ለመተግበር ወደኋላ አትበል። ማንም ሰው ግድ ለማይሰጠው ጉዳይ እየፈራህና እየተጨነክ አትኑር። ያዩኛል፣ ይከታተሉኛል፣ ይተቹኛል፣ ምን ይሉኛል ብለህ የምትጨነቅላቸው ሰዎች በሙሉ የእራሳቸው የማያልቅ ጉዳይ አለባቸው። ማንም ያንተ አዲስ ነገር መጀመር፣ በተለየ መንገድ መጓዝ፣ በአዲስ አቋም መታደስ አያሳስበውም። ሁሉም የግሉ ሩጫ ላይ ነው። ምናልባት በአጋጣሚ ሲያይህ የመጣበትን ቃል ሊሰነዝርብህ ይችላል ከዛ ቦሃላ ግን ትዝም አትለውም። እያንዳንዱ ሰው በግል ጡዘት በተጠመደበት ጊዜ አይኖች ሁሉ እኔ ላይ ናቸው ብለህ አትሸወድ። ማንም ስታልፍ ያይህ ይሆናል እንጂ ጉዞህን በሙሉ እየተከታተለ አይኖርም። የእራስህን ኑሮ መኖር ላይ አተኩር፣ ከፈጣሪህና ግድ የሚሰጠሁን ሰዎች እስካላሳዘንክ ድረስ ሌላው ነገር ትርፍ ነው። መጀመሪያ የምትኖረው ለእራስህ እንጂ ለሰው አይደለም።

አዎ! ሰበብ አታብዛ ደስታ የሚሰጥህን፣ ያመንክበትን፣ የሚጠቅምህን ነገር በጊዜ አድርግ። ህይወትህን በፍረሃት አትሰራት፤ መኖርን በማይሆን ገደብ አትከልላት። በትንሹም ቢሆን ጥረትህን ጀምር፤ ደስታህን ወደ መፍጠር ተሸጋገር፤ የእራስህን አለም አበጃጅ፤ ፈጣሪህ ያይሃል፤ አምላክ ያውቅልሃል፤ ይረዳሃል፤ ይቀድምልሃል። ስለመጪው ጊዜ ቁጪትና ብትስጪት የምትጨነቅበት ምክንያት የለህም። በአጋጣሚ ያገኘህና የተመለከተህ ባላወቀህ መጠን ሊናገር ይችላል፤ አስቦና ፈልጎ የሚመለከትህ ግን በእርግጥም ሊደግፍህ እንደሚመጣ አትጠራጠር። ልዩነት መፍጠሩን አሁኑኑ ጀምር፤ በልብህ የያዝከውን፣ በአዕምሮህ ያነገብከውን ሃሳባዊ አለም ከምድራዊው ተጨባጭ አለም ጋር ቀላቅለው። የመጣው ይምጣ፤ የሆነው ይሁን፤ የማይቀር ነገር እንደሆነ የመጣውን ተቀበል። በእራስህ ተመማመን፤ ለእራስህ ብለህ ድፈር፤ ጠንክር፤ ለእራስህ ብለህ ህይወትህን በሙላት ኑር።
ውብ ምሽት ይሁንልን! 🌘🌒💫✨
(Epha A.)
ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ! 🦋

🔺🔻በYouTube ቤተሰብ ስለሚሆኑ እናመሰግናለን!
SUBSCRIBE NOW! 👇
https://www.youtube.com/channel/UCIZv4h3iDx2C7CGbv9WIkVg?sub_confirmation=1
ምክረ-አዕምሮ/ @MentalCounsel 😊💪


ተሰጦና ክህሎት!
፨፨፨፨////፨፨፨፨
"ተሰጦ ከአምላክህ የሚሰጥህ ስጦታ ነው፣ አንተም እርሱን ተጠቅመህ የምትሰራው ስራ ለአምላክህ መልሰህ የምትሰጠው ስጦታ ነው።"
                               -Leo Buscaglia

ተሰጦህ (talent) ምንም ሊሆን ይችላል ጠንክረህ ካልሰራህበት ግን ምንም ነው። ዓለም በብዙ ባለተሰጦዎች ተሞልታለች ነገር ግን እነዚህ ባለተሰጦዎች በሙሉ ስኬታሞች አይደሉም። ማንም ሰው ስኬትን ይጎናፀፍ ዘንድ ተሰጦውን በማያቋርጥ ጥረት መደገፍ አለበት ወይም አንድ በፅናት የሚሰራበት ክህሎት (skill) ያስፈልገዋል። ጠንክሮ የመስራትን ዋጋ ማሳነስ ስትጀምር ውድቀትህ ይጀምራል። የህይወትህን ዋጋ በመንፈሳዊነት፣ በተሰጦና በክህሎት መሃል ታገኘዋለህ። መንፈሳዊነት እንደ ክህሎትና ተሰጦ ጠንክሮ በመስራትም ሆነ ሌትከቀን በመልፋት የሚዳብር ነገር አይደለም። መንፈሳዊነት ለፈጣሪ እጅ መስጠትና ለእርሱ መገዛት ነው። የተቀሩት ሁለቱ የህይወት ምሰሶዎች ግን ይለያሉ። ተሰጦ ካልተሰራበት ይባክናል፣ ክህሎት ግን ገና ከጅምሩ ሊመጣ የሚችለው በጥረትና በማያቋርጥ ትጋት ነውና መቼም ውጤት አልባ ሊሆን አይችልም። በተሰማራህበት የስራ ዘርፍ ፈፅሞ ጠንክሮ የመስራትን ዋጋ አቅልለህ እንዳትመለከት። በፅናት የመፋለምን ቦታ እራሱ በፅናት መፋለም ካልሆነ በቀር ምንም ሊተካው እንደማይችል እወቅ።

አዎ! ጀግናዬ..! ተሰጦና ክህሎት ጉዟቸው ለየቅል ነው። ተሰጦህን ብቻ ተማምነህ ህይወትን ልታሸንፍ አትችልም፤ ክህሎትህን በማዳበር ግን የምትመኘውን ህይወት መኖር ትችላለህ። ዓለም የምትመራው በባለተሰጦዎች ሳይሆን ክህሎታቸውን አዳብረው የዘርፉን ከፍታ በተቆናጠጡ ሰዎች ነው። እግር ኳስ ተጫዋች ብትሆን ስመጥርና ተመራጭ ለመሆን ልክ እንደ ክርስቲያኖ ሮናልዶ ጠንክሮ መስራት አማራጭ የሌለው ብቸኛ አማራጭህ ነው፣ ልክ እንደ ሻለቃ ሀይሌ ገብረስላሴ ብዙ የዓለም ሪኮርዶችን በመሰባበር ስመጥር ዓለማቀፍ አትሌት ለመሆን ለረጅም ዓመታት የማያቋርጥ ልምምድና ዲሲፕሊን ግዴታህ ነው። በተሰጦህ ብቻ መደበኛ ህይወት ልትኖር ትችላለህ፣ ባዳበርከው ክህሎት ግን ጥራት ያለው ከራስ በላይ ለሰው የሚፈስ ህይወት መኖር ትችላለህ። ማንም ህልም የሌለው ሰው የለም፣ ማንም ምኞት የሌለው ሰው የለም። ህልምና ምኞቱን ለማሳካትም ደግሞ ክህሎትና ገንዘብ ያስፈልገዋል። የሚያዳብረው ክህሎት ህልሙን እውን የሚያደርግበትን ገንዘብ በእጅ እንዲያስገባ ያግዘዋል። ጠንክሮ ለሚሰራ ብርቱ ሰው ገንዘብ ማግኘት ከባድ ሊሆን አይችልም፤ ተሰጦውን ተማምኖ ለሚቀመጥ ሰው ግን የሚመኘውን ያህል ገንዘብ ማግኘት በጣም ከባድ ነው።

አዎ! መርጠህ ተለማምደህ ካዳበርከው ክህሎትና ከእግዚአብሔር ከተሰጠህ ተሰጦ በየትኛው መተማመን እንዳለብህ በሚገባ እወቅ። በእርግጥ ተሰጦህን ችላ ማለት፣ ከፈጣሪህ በተሰጠህ ነገር አለመተማመን ከፈጣሪ እምነትና ክብር ጋር የሚያገናኘው ነገር ላይኖር ይችላል ነገር ግን እስካወከው ድረስ ከቻልክ በተሰጠህ አንድም ሆነ ሁለትም ሆነ አምስት መክሊት የማትረፍና ለሰጪህ ትርፉን የመመለስ ግዴታ አለብህ። ጥረህ ግረህ ብላ መባሉ አንድም ቅጣት ሌላም ግዴታ ነው። ማንም የሰው ልጅ ሆኖ ያለልፋቱ የሚያገኘው ነገር ሊባረክለት አይችልም። በቀላሉ የምታገኘው የትኛውም ነገር በቀላሉ ሲጠፋ ትመለከታለህ። ረጅም ርቀት ተጉዘህ፣ ብዙ ተምረህበት፣ ብዙ አውቀህበት፣ ለረጅም ጊዜ ጥረህለት ያመጣሀው ነገር በአንድ ሌሊት ቢጠፋ እንኳን እንዴት አድርገህ ድጋሜ ልታገኘው እንደምትችል ጠንቅቀህ ታውቃለህ። በተሰጦህ አትዘናጋ፣ ባለህ አቅም ሁሉ በየጊዜው አሳድገው፣ ስራበት፣ ያለማቋረጥ አዳብረው፣ ከሌላው ሰው በተለየ ትርፍን አግኝበት። ካልሆነ አንድ ክህሎት መርጠህ አዳብር፣ ደከመኝ ሰለቸኝ ሳትል ማስተር አድርገው፣ ንገስበት፣ ከሌላው ሰው በተሻለ ተቆጣጠረው፣ እራስህን አስገዛለት፣ ስኬትንም በእርሱ መንገድ እጅህ አስገባው።
ግሩም ድንቅ ቀን ይሁንልን! 🌅🌞🏞
(Epha A.)
ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ! 🦋

🔺🔻በYouTube ቤተሰብ ስለሚሆኑ እናመሰግናለን!
SUBSCRIBE NOW! 👇
https://www.youtube.com/channel/UCIZv4h3iDx2C7CGbv9WIkVg?sub_confirmation=1
ምክረ-አዕምሮ/ @MentalCounsel 😊💪


ማህበራዊ ስኬት!
፨፨፨፨//////፨፨፨፨
ሲታዩ ደስተኛ መምሰል፣ ለይስሙላ ለባብሶ ደምቆ መውጣት፣ ሰው ፊት እንዲወራልን መጠበቅ፣ ሁሌም ተከብረን፣ ተሞግሰን፣ ተደንቀን መኖርን መመኘትን የማህበራዊ ስኬት ጥማት እንለዋለን። እያንዳንዱ ጉዟችን ለእኛ ሳይሆን ለስማችን ነው፤ ለሚሰጠን ክብርና ዝና ነው፤ በሰው ዘንድ ለምናገኘው ቦታ ነው። ለእራሰህ ያልሆነህ፣ አንተን ያላስደሰትህ፣ ላንተ ያልጠቀመህ ስኬትም ይሁን ከፍታ በሰው ፊት ቢያስከብርህ፣ ከፍ ቢያስደርግህ ለከፋው ውድቀት ከማመቻቸት ውጪ ምንም ጥቅም የለውም። የምትችለው ነገር ብዙ ሆኖ ሳለ ለሰዎች ጭብጨባና አድናቆት ብቻ መልፋትህን አቁም። ዛሬ ብትነሳ ነገ ላለመውደቅህ ምንም ዋስትና እንደሌለህ ተረዳ። ትናንት ያነሳህ፣ ያሞገሰህ፣ የደገፈህ ሰው ዛሬ በተራው ሊጥልህ እንደሚችል አስብ።

አዎ! ጀግናዬ..! የማህበራዊ ስኬት ጥማትህን ገታ አድርገው፤ በሰው ለመወደድ፣ ይሁንታን ለማግኘት፣ ዝናን ለማትረፍ ከመሯሯጥ መለስ በል። እራስህን ማስደሰት ሳትችል ደስተኛ ሆኖ መታየት ሸክም እንጂ ምንም ትርፍ አያመጣልህም። የሆንከውን ብትሆን ሰው ቢቀበልህ ባይቀበልህ፣ ቢያጨበጭብልህ ባያጨበጭብልህ፣ ቢደግፍህ ባይደግፍህ ዋናው ቁብ ነገር አንተ የእራስህ ደጋፊ መሆንህ ነው። ለእራሱ የሚወግንን ሰው ማንም ሊያስቆመው አይችልም። ምክንያቱም አብሮት ያለው ሁሉን ማድረግ የሚችለው አምላክ ነውና። ዛሬ አንተ ደክመህ፣ ለፍተህ፣ እራስህን አተህ፣ ተጋግጠህ ያመጣሀውን ዝና ነገ በሌላ ነገር የሚቀይረው በወረት የሚመራ የሰው ልጅ ውስጥ እንዳለህ አስታውስ። ትናንት ሲመረቁ የነበሩ ሰዎች ዛሬ ሲረገሙ ማየት አዲስ አይደለም። ቦታህን ይዘህ የምትቀጥለው በሰዎች ስሜት ስለተነዳህ ሳይሆን እራስህን ስለሆንክና እራስህን ከማስደሰት ስለተነሳህ ነው።

አዎ! ለመታየት፣ ለመደነቅ፣ ለመሞገስ ሳይሆን ዋጋህን ለመጨመር፣ ጥራትህን ለማሳደግ፣ ማንነትህን ለማሳየት ትጋ። ከምንም በላይ እራሱን ማውጣትና ከፍ አድርጎ ተፅዕኖ መፍጠር የሚችለው እራሱ ሰውዬው ነው። አለም በቅፅበታት ትቀያየራለች፣ የሚቀይራትም የሰው ልጅ ቅፅበታዊ ስሜት ነው። በምክንያት ቢወድህ በምክንያት ሊጠላህ ከሚችል ሰው ጋር እየኖርክ ለእርሱ ደስታና እርካታ፣ ከእርሱ ቅቡልነትን ለማግኘት ብትሰቃይ ዋጋህን ከማሳነስ በቀር የምታተርፈው ነገር አይኖርም። ሁላችንም የተለያየ አቅም አለን። ያ አቅም ሰዎችን Impress ለማድረግ ሳይሆን እራሳችንን በጠለቀ የመሞላት ስሜት ለማነፅ ብንጠቀመው ስሜቱ በእራሱ ውጫዊውን ድባብ ሲቀይረው ለመመልከት ጊዜ አይፈጅብንም። ለመታየት ሳይሆን ብቁ ለመሆን ስራ፤ ለተቀባይነት ሳይሆን ለውስጥ መሻትህ ትጋ፤ ለስምና ዝና ሳይሆን ለእውነተኛው መጠራትህ እራስህን ስጥ።
ውብ ምሽት ይሁንልን! 🌘🌒💫✨
(Epha A.)
ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ! 🦋

YouTube አማራጭ ይቀላቀሉን!
🔺🔻 SUBSCRIBE NOW
https://www.youtube.com/channel/UCIZv4h3iDx2C7CGbv9WIkVg?sub_confirmation=1
ምክረ-አዕምሮ/ @MentalCounsel 😊 💪


የተረጋጋ ሰው ሁን!
፨፨፨/////////፨፨፨
ከሰው ልጅ ባህሪያት መካከል እንደ ግራማምገስ የሚያስከብር እንደ ተረጋጋ ስብዕናም የሚማርክ ነገር ምን አለ? አስቡት ስማችሁ ሲነሳ ግርማችሁ ሲከተላችሁ፣ ለትንሹም ለትልቁም መደንገጥ ስታቆሙ ሰዎች እናንተን መከተል ሲጀምሩ፣ አስቡት በምንም ሁኔታ ውስጥ የተረጋጋችሁና ለተፈጠረባችሁ ነገር ፈጣን ምላሽ የማትሰጡ እንዲሁም በቀላሉ የማትረበሹ ስትሆኑ ምንያህል ተፅዕኖ መፍጠር እንደምትጀምሩ። መጣል የጀመረው ዝናብ እስኪያባራ ተረጋጉ፣ ንዴታችሁ አስኪበርድ ተረጋጉ፣ የለመናችሁት ነገር እስኪሆንላችሁ ተረጋግታችሁ ጠበቁ፣ ፈልጋችሁ ያጣችሁት ሰው ወደ ህይወታችሁ እስኪመጣ፣ የሚያስፈልጋችሁ ስራ ከፈጣሪ እስኪሰጣችሁ ተረጋጉ። የእናንተ ካልሆነ ስለቸኮላችሁ የምታገኙት ክብርም ሆነ ሽልማት አይኖርም፣ ካልተፈቀደላችሁ አለቀሳችሁም፣ ተነጫነጫችሁም፣ ተናደዳችሁም የእናንተ የሚሆን ነገር የለም። የሀገራችን አባባል እንዲ ይላል፦ "የቸኮለች አፍሳ ለቀመች።" ባትቸኩልና ብትረጋጋ የያዘችውን እህል ተገቢው ስፍራ ሳታደርስ አፍሳ ለመልቀም ባልበቃች ነበር።

አዎ! ጀግናዬ..! አትዋከብ የተረጋጋ ሰው ሁን፤ እራስህን አታስጨንቅ ጊዜ የሚፈታቸውን ጉዳዮች ለጊዜ ሰጥ። ስለቸኮልክ ብቻ የምትደርስበትና በፍጥነትህ ምክንያት ብቻ በእጅህ የምታስገባው ነገር የለም። ህይወት የራሷ የህይወት መንገድ፣ የእራሷ የቀን ገደብ አላት። አንተ ስላዘንክ ፈጥኖ የሚደረግልህ አንተም ስለተደሰትክ በፍጥነት ከእጅህ የሚዘጣ ነገር አይኖርም። አንዳንድ ያለመረጋጋቶች የሚፈጠሩት የያዝነውን እንዳናጣ ወይም የሚመጣው እንዳያመልጠን ይሆናል። እውነታው ግን በመርበትበት ያለንን ማቆየት ወይም የሚመጣውን ማግኘት አለመቻላችን ነው። ንዴትና ብስጪታችን የሆነን መጥፎ ነገር እንዳልሆነ ቢያደርገው ጥሩ ነበር፣ ችኮላና ሩጫችንን የዛሬ ዓመት መድረስ ያለብህን ስፍራ ዛሬ ቢያደርሰን መልካም ነበር፣ የማያባራው ፍላጎትና ምኞታችን ብቻ አሁኑ ያሰኘንን ነገር በእጃችን ቢያስገባ ጥሩ ነበር። ነገር ግን የተፈጥሮ አሰራር ከዚህ የተለየ ነው። የምትመኘውን ትልቅ ነገር ለማግኘት መታገስ አለብህ፣ መድረስ የምትፈልገው ስፍራ ለመድረስ ተረጋግተህ ሁሌም ጉዞ ላይ መሆን ይኖርብሃል፣ የስሜት ብለሃትህን ለማሻሻል፣ በአስተሳሰብና በማንነት ልቆ ለመገኘት ለምላሾች መዘግየት፣ እራስን መግዛትና የተጠኑ እርምጃዎችን ማድረግ ይኖርብሃል።

አዎ! በህይወት ሽንፈትም አሸናፊነትም አለ፣ በህይወት ደስታም ሀዘንም አለ፣ ማግኘትም ማጣትም አለ፣ ማትረፍም መክሰርም አለ፣ ፍቅርም ጥላቻም አለ። ትልቁ ቁብነገር በእነዚህ ሁሉ ተቃራኒ ሁኔታዎች ውስጥ አቋምን አክብሮ፣ ስሜትን ገዝቶ፣ እራስን ገስፆና ተረጋግቶ ነገሮችን ማሳለፍ መቻል ነው። ጊዜ እንደ ወረጅ ወንዝ ነው። ወራጁ ውሃ በወንዙ ውስጥ ያለውን ቆሻሻ ቀስበቀስ እያጠራ እንደመምጣቱ ጊዜም እንዲሁ በህይወትህ ያለውን አላስፈላጊ ነገር በሂደት እያስወገደ ይመጣል። ይህም የሚሆነው ስለቸኮልክ ወይም ያዙኝ ልቀቁኝ ስላልክ አይደለም። ለጥያቄዎችህ በሙሉ ፈጣሪ በጊዜ ምላሽ እንዲሰጥህ ስትፈቅድ የሚሆንህና የሚገባህ ነገር በሰዓቱ ይደረግልሃል። መቆጣጠር የምትችለውን የህይወትህን ክፍል ተቆጣጠር፣ ማስተካከል የምትችለውን ጉዳይ አስተካክል፣ ከአቅምህ በላይ የሆነን ጉዳይ በመታገል ጊዜህን አታጥፋ። ተረጋጋ እግዚአብሔር የሚሰጥህን ምላሽ በትዕግስት ጠብቅ፣ የፈጣሪን ትክክለኛ ሰዓት ተጠባበቅ። ከሆነብህ በላይ ለሆነብህ ጉዳይ የምትሰጠው ምላሽ ያንተን ጥበብና ብስለት እንደሚያሳይ እወቅ።
ግሩም ድንቅ ቀን ይሁንልን! 🌅🌞🏞
(Epha A.)
ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ! 🦋

🔺🔻በYouTube ቤተሰብ ስለሚሆኑ እናመሰግናለን!
SUBSCRIBE NOW! 👇
https://www.youtube.com/channel/UCIZv4h3iDx2C7CGbv9WIkVg?sub_confirmation=1
ምክረ-አዕምሮ/ @MentalCounsel 😊💪


በሰዎች ሰትናቁ!
፨፨፨///////፨፨፨
ሰው የሰወን ልጅ እንደ ሰውነቱ ያከብር ዘንድ ግዴታ አለበት። ነገር ግን ይህን ግዴታውን በመሻር ክብራችሁን የሚነካና የሚንቃችሁ ከሆነ ለእራሳችሁ ዘብ የምትቆሙት፣ ንቀቱን የምታስታግሱትና ደረጃችሁን የምታሳዩት እራሳችሁ ናችሁ። እየተናቁ መኖር ልብን የሚነካ ህመም አለው። እየተገፉ፣ እንደ አማራጭ እየታዩ፣ ችላ እየተባሉ መኖር ልብ ላይ የሚያሳርፈው ጠባሳ እጅግ ከባድ ነው። ምናልባት አንዳንዶች ንቀትን ተላምደው ይኖሩ ይሆናል፣ ቢገፉም፣ ቢጣሉም ላይሰማቸው ይችል ይሆናል። ነገር ግን በሰዓቱ ባይሆንም ነገሮች በተደራረበባቸውና አስጨናቂ ሁኔታ ውስጥ በገቡ ሰዓት ይሔም ጉዳይ ጫና ውስጥ ይከታቸዋል። አትናቁ እንድትናቁም አትፍቀዱ፣ ሰውን አታራክሱ እንተንም ማንም እንዲያራክሳችሁ አትፍቀዱ፣ በሰው ክብር ላይ አትረማመዱ ሰውም ክብራችሁን እንዲነካ አትፍቀዱ። እያዩ እንዳላዩ፣ ሰምተው እንዳልሰሙ መሆን እየተቻለ የንቀት ባህሪ ካላቸው ሰዎች ጋር ግብ ግብ ውስጥ አትግቡ። ንቀትን ንቆ ማለፍ ጥበብም ብለሃትም እንደሆነ አስታውሱ።

አዎ! አስተውሉ ንቀትን በግብግብ አታሸንፉም፣ ንቀትን በሃይልና በብስጭት አታልፉትም። ስትናቁ አጥብቃችሁ ጥበብን ተማሩ፣ ያለምንም ቅድመሁኔታ መርሳት የተባለን ስጦታችሁን ተጠቀሙ። የሚገባችሁ ቦታ ሲነፈጋችሁ፣ እየሰራችሁ፣ እየጣራችሁ የልፋታችሁን ዋጋ እየተነፈጋችሁ፣ መደነቅ ሲገባችሁ ስትተቹ፣ መሞገስ እያለባችሁ ስትሰደቡ እንደማንኛውም ሰው ስሜታችሁ መጎዳቱ፣ ለምንም ነገር ተነሳሽነት ማጣታችሁና ለጥልና በቀል መዘጋጀታችሁ አይቀርም። ነገር ግን በዚህ ምላሽ ይበልጥ ለጥቃትና ለንቀት እራሳችሁን ብታጋልጡ እንጂ የደረሰባችሁን ጉዳት ልታስቀሩት አትችሉም። የሚወራባችሁን በጥቂቱ ስሙ፣ በቻላችሁት አቅም የሰውን ፊት ለማንበብ ሞክሩ፣ ሁኔታዎች በጥቂቱ መርምሩ፣ ለምላሽና ለሰጣገባ አትቸኩሉ፣ ለጥቂት ጊዜ በዝምታ ቆዩ፣ ታገሱ፣ የጊዜ ገደብ አስቀምጡ። በስተመጨረሻ ግን ለእራሳችሁ ክብር ስትሉ ፊታችሁን አዙሩ፣ ንቀታቸውን ላለመመልከት ወስኑ፣ ከደረጃችሁ ወርዳችሁ የሚያሳንሳችሁን ተመሳሳይ ተግባር ላለመፈፀም ለእራሳችሁ ቃል ግጉ። የእራሳችሁን መስመር አስምሩ፣ እነርሱም ከመስመሩ ውጪ እንደፈለጉ እንዲሆኑ በመተው እርሷቸው።

አዎ! ጀግናዬ..! ትልቁ ጥበብ ንቀትን ንቆ ማለፍ ነው። ጉዳይህ በማታውቀው ሳይሆን በምታውቀው ሰው እንኳን ስትናቅ ስለምትሰጠው ምላሽ መጨነቅ አይደለም፣ ጉዳይህ በምርጫና በፍላጎት ስለመገፋትህ ተቀምጦ መቆዘም አይደለም። ዋናው ጉዳይህ በሰውነትህ የሚገባህን ክብር ማግኘትህ ነው። የሰው ልጅ ምንም ባይኖረው፣ የትም ባይደርስ፣ ምንም ቢጎድለው ሰውነቱ ብቻ፣ በአምላኩ አምሳል መፈጠሩ ብቻ ክብርንና ትኩረትን ያሰጠዋል። ቦታ በሰጠውት ሰው ቦታ አልተሰጠኝም፣ በወደድኩት ሰው ተጠላው፣ ትኩረት በሰጠውት ሰው ትኩረት ተነፈኩ፣ ባከበርኩት ሰው ተናቅኩ ብለህ እራስህን አታጨናንቅ። ክብርህን ያልተረዳ ሰው ቢንቅህና ቢገፋህ ምን እንዳጣ ማሳየት የምትችለው አንተ እንደሆንክ አስተውል። የበዛ ስምና ዝና ተቆልሎብህ ከምትወድቅ ተንቀህና ተገፍተህ በስራህ ከፍ ብትል ይሻልሃል። ሰው ያንኑ የለመደውንና ያደገበትን ያደርግብሃልና አትሸበር። አንተ አድናቂና ደጋፊ ስመሆንህ አስብ እንጂ ሲሔድ ለሚሔደው ባዶ ንቀትና ጥላቻ ቦታ አትስጥ፣ አንተም ንቀህ ተወው።
ውብ ምሽት ይሁንልን! 🌘🌒💫✨
(Epha A.)
ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ! 🦋

YouTube አማራጭ ይቀላቀሉን!
🔺🔻 SUBSCRIBE NOW
https://www.youtube.com/channel/UCIZv4h3iDx2C7CGbv9WIkVg?sub_confirmation=1
ምክረ-አዕምሮ/ @MentalCounsel 😊 💪


ከሃዲ አትሁን!
፨፨፨////፨፨፨
አንድ ነገር አስተውሱ፦ "የምትኖሩት ከሰዎች ጋር ነው፣ ሰዎችም ስህተትን የሚሰሩት ፍጡራን ናቸው፣ ስህተታቸውም ክህደት እስከተባለ ከባድ ጥፋት ሊያደርሳቸው ይችላልና በመከዳታችሁ ብዙ አትሸበሩ።" በሰው ከመከዳት በላይ የሚጎዳችሁ እራስን መካድ እንደሆነ አስተውሉ። እግዚአብሔር አምላክ በብዙ መንገድ ያስተምረናል። ከእርሱ በላይ በሰው ስንታመን ሰውየውን መጥፎና ጎጂ ያደርገዋል፣ ከእርሱ በላይ ሰውን ስንደገፍ ሰውዬውን ከሃዲና ጨካኝ ያደርገዋል። አንድ ቀን የሚክደንን ሰው አምልኮት የቀረውን ቦታ ሰጥተን ስንከተለው፣ ለፈጣሪያችን መስጠት የሚገባንን ክብርና ጊዜ ለእርሱ ስንሰጠው፣ ለአምላካችን ሊኖረን የሚገባውን ጥብቅ ግንኙነት ከእርሱ ጋር ስናደርግ ትልቁ የህይወት ትምህርት በእግዚአብሔር መልካም ፍቃድ ይሰጠናል። በስቃይ እንድንማር፣ አምኖ በመከዳት እንድንነቃ፣ አግኝቶ በማጣት ወደ እራሳችን እንድንመለስ፣ ብቻችንን በመቅረት ወደ ፈጣሪያችን እንድንመለስ እንደረጋለን። ክህደት ብርቅ አይደለም። እንኳን ሰው ሰውን ይቅርና የሰው ልጅ አምላኩን ይክደዋል፣ እርሱ እያኖረው መኖሩን እርግፍ አድርጎ ይክዳል፣ ህልውናው ላይ ተደጋጋሚ ጥያቄዎችን ያነሳል። ሰው ምኞቱ አያልቅምና ክህደቱንም እራሱ ካልገታው መቋጫ የለውም።

አዎ! በክህደት አትሸበሩ! ዘመን በዘመን ሲተካ ከሃዲውም ታማኙም እኩል አዲሱን ዘመን ለመመልከት ይበቃሉ፣ ፈጣሪ እንደ ሰው አይደለምና ለሁሉም እኩል የመመለሻ ጊዜ ይሰጣል። ጥፋተኛ በጥፋቱ አይዘልቅም፣ ከሃዲውም እንዲሁ ዘመኑን ሙሉ በክህደቱ ሰውን እያስለቀሰ፣ በሰው ህይወት እየተጫወተና ደጋግሞ ሰውን እየጎዳ አይኖርም። ቢዘገይም ማንም የዘራውን ያንኑ ያጭዳል፣ በሰው ላይ ካደረገው በላይ እራሱ ተደርጎበት ይመለከታል። ዛሬ በጥፋት ዘመን ማስተዋል ሊያጣ ይችላል፣ በመጥፎ ልማዱና በጎጂ ማንነቱ ሊተማመን ይችላል። አንዴ ሲወድቅ ግን ወድቀቱ የከፋ ይሆናል፣ አንዴ መንገዱን ሲስት ግን የሚከፍለው ዋጋ እጅግ የበዛ ይሆናል። መከዳታችሁ ጊዜያዊ ህመምን ሊያስከትልባችሁ ይችላል፣ ባመናችሁት መዋሸታችሁና መታለላችሁ ትልቅ ጠባሳን ሊጥልባችሁ ይችላል ነገር ግን ከከሃዲነት ፀፀትና እረፍት ከማይሰጠው የጥፋተኝነት ስሜት ነፃ ናችሁ። ህመማችሁ ይድናል ያሳመሟችሁ ሰዎች ግን መጥፎ ስራቸው ሲያቅበዘብዛቸው ይኖራል፣ ጉዳታችሁ ይሻራል ሁን ብለው የጎዷችሁና ሰላም ያሳጧችሁ ግን በጥፋተኝነት ስሜታቸው ዘመናቸውን በሙሉ እራሳቸውን ሲወቀሱ ይኖራሉ።

አዎ! ጀግናዬ..! ከሃዲ አትሁን! እምነትን ከመብላት፣ ቃልን ከማጠፍ፣ ባሉት ካለመገኘት ተቆጠብ። ክህደት ምንያህል ጎጂ እንደሆነ ለማወቅ የግድ ተከድተህ ማየት አይኖርብህም፣ ቃልን ማጠፍ ምንያህል እንደሚያቆስል ለማወቅ በሌሎች ቃል ታጥፎብህ መጎዳት አይኖርብህም። ጥቂት የማይባል ሰው በክህደት ምክንያት ህይወቱ እንዳልነበር ሆኗል፣ በቃል በሊታዎች ምክንያት ከባድ የህይወት ፈተና ውስጥ ገብቷል፣ በአስመሳዮችና በውሸታሞች ምክንያት ያልጠበቀው አጣብቂኝ ውስጥ ገብቷል። ከቻልክ አስቀድሞ የማይመችህ ነገር ውስጥ አትግባ፣ ገብተህም ቢሆን ነገሮችን በግልፅ ለማስረዳት ሞክር እንጂ የክህደትን መዘዝ እያወክ በፍፁም ከሃዲ አትሁን፣ በድብቅ አታሲር፣ በውሸት አትደልል። እራስህ በዘረጋሀው ገመድ እራስህ ተጠልፈህ እንዳትወድቅ ተጠንቀቅ፣ በገዛ ሴራህ መቀመቅ ከመግባት እራስህን ጠብቅ። ክፉዎች በይቅርታና በንሰሃ እስካልተመለሱ ድረስ ሁሌም ቢሆን መጨረሻቸው ጥፋት ነው። ከሃዲዎችም ቢሆኑ ከፈጣሪያቸው ጀምረው መካድን ሲለማመዱ አወዳደቃቸው እጅግ የከፋ ይሆናል። የፈጣሪህን ቦታ ለማንም አትስጥ፣ ክህደትን ተጠየፍ፣ በታማኝነትህ እራስህን አስከብር።
ግሩም ድንቅ ቀን ይሁንልን! 🌅🌞🏞
(Epha A.)
ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ! 🦋

🔺🔻በYouTube ቤተሰብ ስለሚሆኑ እናመሰግናለን!
SUBSCRIBE NOW! 👇
https://www.youtube.com/channel/UCIZv4h3iDx2C7CGbv9WIkVg?sub_confirmation=1
ምክረ-አዕምሮ/ @MentalCounsel 😊💪


መሔድ አለብህ!
፨፨፨////////፨፨፨
እውነት ነው፦ ፈርተሃል፣ ውስጥህ ተጨንቋል፣ ልብህ ደጋግሞ ይመታል፣ እግርህ ተሳስሯል፣ እጆችህ ይንቀጠቀጣል፣ ፊትህ በላብ ተጠምቋል ነገር በዚህ ሁኔታ ውስጥ ሆነህም መሔድ አለብህ፣ ወፊት መጓዝ አለብህ፣ ጉዞህን መቀጠል ይኖርብሃል። እነዚህን ከባባድ ሁኔታዎች ልታሸንፋቸው የምትችለው በመቆም ወይም በመሸሸ አይደለም አሸናፊነትህ በብቸኝነት ያለው ጉዞህ ውስጥ ብቻ ነው። ብዙ ሰው ቆሞ ባለበት ዓለም መቆም ብርቅ ሆኖ አያውቅም፤ ብዙ ሰው በሚፈራበት ሀገር ፍረሃት አጀንዳ ሆኖ አያውቅም፣ መሸሽና መደበቅ እንደ ጨዋነት በሚቆጠርበት ማህበረሰብ ሁሉም ስፍራ አንገት መድፋት እንደ ጥሩነት እንጂ እንደ ጎጂ ፍረሃት ተወስዶ አያውቅም። ዓለም የተስማማበት የትኛውም እሳቤ ላንተ ከመስራት በላይ አንተ ላይ የሚሰራ፣ አንተን ከመጥቀም በላይ ባንተ የሚጠቀም ከሆነ ቆም ብለህ እራስህን መጠየቅ ያለብህ ትክክለኛ ጊዜ ያ ነው። ጥያቄህ ከተቀመጥክበት የሚያነሳህ ነው፣ ጥያቄህ ፍረሃትህን ፈንቅለህ እንድትወጣ የሚያደርግህ ነው፣ ጥያቄህ ወደፊት የሚያስጉዝህና አቋምህን የሚቀይር ነው። ጥያቄህም ይሔ ነው፦ "ቆሞ መቅረት ብቸኛ ምርጫዬ ነውን?"

አዎ! ጀግናዬ..! መሔድ አለብህ፣ መጓዝ አለብህ፣ እንቅስቃሴን መምረጥ፣ ጥረትህን መቀጠል፣ ለመጪው ጊዜ ዋጋ መክፈል ይኖርብሃል። መድረስ የምትፈልገው ቦታ ይኖረል፣ የህይወት ዘመን ምኞት ይኖርሃል፣ ቢሆንልኝ ብለህ የምትለው የህይወት ከፍታ አለ። ያለምንም እንቅስቃሴና ያለምንም ጉዞ መኖሩ ብቻ ግን እውን ለመሆኑ ዋስትና አይደለም። አሸናፊዎች የሚያሸንፉት አሸናፊነት መጥቶላቸው ሳይሆን እራሳቸው ሂደው፣ አሳደው፣ ለዘመናት ሌትከቀን ሰርተውበት አግኝተውት ነው። ልብህ የሚያምንበት የህይወት አቅጣጫ ካለ በእርሱ መንገድ ለመጓዝ አትፍራ። ስራ የዘላለም አይደለም፣ ጉዞህ ማብቂያ የሌለው አይደለም፣ ጥረትህ መጨረሻ አልባ አይደለም። ትሔዳለህ፣ ትሔዳለህ፣ ትጓዛለህ መድረስ የሚገባህ ቦታ ስትደርስ ከመዳረሻህ ቦሃላ እርፍት አድርገህ ዳግም ወደ አዲሱ መዳረሻህ ትጓዛለህ። አቅምህ እስከፈቀደ፣ እድሜህ እስካስቻለህ ትጓዛለህ፣ ትሞክራለህ፣ ትሰራለህ የሚገባህ ህይወትህም በዛው ልክ ይሰጥሃል።

አዎ! ጉዞህ በማንም እይታ ውስጥ የመግባት ግዴታ የለበትም፣ ጥረትህ በማንም ዘንድ ተቀባይነት የማግኘት ግዴታ የለበትም፣ እንቅልፍህን ማጣትህ፣ በጨለማ መሞከርህ፣ ብቻህን መጋፈጥህ ለማንም የመታየት ግዴታ የለበትም። የምትጓዘው ማንም ሳያይህ ብቻህን ነው፣ ስትደርስ ግን ብዙዎች ያዩሃል፣ ብዙዎች ይደነቁብሃል፣ ጥረትህን አላዩምና ብዙዎች እዛው የበቀልክ ይመስላቸዋል። ጉዞ ላይ እንደሆንክ ከተሰማህ ስለመድረስህ አትጠራጠር፣ እየሔድክ ከሆነ በማደግህ አትጠራጠር። እርግጥ ነው በአንድ ጀምበር አትደርስም፣ እንዲሁ አንድ ቀን ስለሞከርክ፣ ሁለት ቀን ስለጣርክ፣ ሶስት ቀን ስለለፋህ፣ ለሳምንታት፣ ለወራት፣ ለአመታት ስለተጋህ ላታሳካው ትችላለህ። ነገር ግን ይህንን እውነት አስታውስ፦ ጥረትህን ካላቆምክ በእርግጥም አንድ ቀን ታሳካዋለህ፣ አንድ ቀን እዛ ስታልመው የነበርከው፣ እዛ ልብህ የሚያሞቀው፣ እዛ ልዩ ስሜት የሚሰጥህ ስፍራ ትደርሳለህ። ምንም ውስጥ ብትሆን መጓዝ አለብህ፣ ምንም ቢገጥምህ እንዳቅምህ መንቀሳቀስ ይኖርብሃል። ተቀምጠህ ሳይሆን ተነስተህ አግኘው፣ ቆመህ ሳይሆን ሔደህ በእጅህ አስገባው።
ውብ ምሽት ይሁንልን! 🌘🌒💫✨
(Epha A.)
ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ! 🦋

🔺🔻በYouTube ቤተሰብ ስለሚሆኑ እናመሰግናለን!
SUBSCRIBE NOW! 👇
https://www.youtube.com/channel/UCIZv4h3iDx2C7CGbv9WIkVg?sub_confirmation=1
ምክረ-አዕምሮ/ @MentalCounsel 😊💪


አንድ ውሳኔ ብቻ!
፨፨፨////////፨፨፨
በህይወት ከባዱ ነገር ብረት ወይም ወርቅ አይደለም ይልቅ ያልተወሰኑ ውሳኔዎች ናቸው። የጭንቀታችሁ ትልቁ ምክንያት መወሰን ያለባችሁ ውሳኔ አለ ነገር ግን መወሰን አልቻላችሁም።
- Alex Hormozi

ኬትም ተነስተን ወዴትም እንሂድ የምንሔድበት ስፍራ የሚያደርሱን ተግባራዊ ውሳኔዎቻችን ናቸው። ወስናችሁ ማቆም ወይም ወስናችሁ መጀመር ያለባችሁ ጉዳይ እያለ እናንተ ግን ለመወሰን ካንገራገራችሁና በየሰዓቱ የውሳኔ ጊዜያችሁን የምታራዝሙ ከሆነ የውሳኔ ሃሳባችሁ ከሸክምም በላይ የጭንቀት ምንጭ መሆኑ የግድ ነው። ይብዛም ይነስም ነፃነታችን ያለው በምንወስናቸው እያንዳንዶቹ የህይወት ውሳኔዎች ውስጥ ነው። ሀላፊነት መውሰድ የሚፈሩ፣ አዲስ ነገር መሞከር የሚያስጨንቃቸው፣ እራሳቸውን ቻሌንጅ ማድረግና አደጋን መጋፈጥ የማይወዱ ሰዎች ሁሌም ቆራጥ ውሳኔ የመወሰን ችግር ይኖርባቸዋል። ውሳኔያቸው ብዙ ነገር እንደሚቀይርላቸው ያውቃሉ ነገር ግን ለመወሰን ድፍረቱ የላቸውም፣ ወደፊት ለመጓዝ ከባባድ ውሳኔዎች እንደሚያስፈልጉ በሚገባ ይረዳሉ ነገር ግን ለረጅም ጊዜ ውሳኔን እየሸሹ ህይወታቸውን በሙሉ በፍረሃትና በስጋት ጥግ ላይ ያሳልፋሉ። የውሳኔ ሰው እስካልሆናችሁ ድረስ ባላችሁበት ስፍራ ከመቅረትና በቁጪት ሸክም እራሳችሁን ከመጉዳት በቀር ምንም የምታተርፉት ነገር የለም።

አዎ! ወስናችሁ ውጡ፣ ወስናችሁ ሸክማችሁን አራግፉ፣ በውሳኔያችሁ ነፃ ውጡ፣ በውሳኔያችሁ የሚጠቅማችሁን ጀብድ ፈፅሙ። መወሰን እያለባችሁ ሳትወስኑ በቀራችሁ ቁጥር ከትርፋችሁ በላይ ኪሳራችሁና የምታጡት ነገር እየበዛ ይመጣል። ዛሬ ከምትኖሩት ህይወት በይዘቱ፣ በጥራቱ፣ በትርፋማነቱም ሆነ በደስተኝነቱ የተለየው ህይወት ያለው ከአንዱ ወሳኝ ውሳኔያችሁ ጀርባ እንደሆነ አስታውሱ። ዛሬ የምትኖሩት ህይወት ወዳችሁም ሆነ ተገዳችሁ የወሰናችሁት ውሳኔያችሁ ውጤት ነው። ሀገር ብትቀይሩ፣ ስራ ብትቀይሩ፣ የምትከታተሉትን መርሃግብር ብትቀይሩ እንዲሁም ውሏችሁን፣ አስተሳሰባችሁንና የህይወት መርሆቻችሁን ብትቀይሩ ከለውጣችሁ ጀርባ ያለው ሁነኛ ግበዓት ቆራጥ ውሳኔያችሁ ነው። አሁን ወደፊት መጓዝ እንዳለባችሁ እያወቃችሁ እስካሁን ግን ወደፊት የሚያራምዳችሁን ውሳኔ ካልወሰናችሁ ከዚህ በላይ ጊዜ አታጥፉ፣ ልባችሁን አሸንፉ፣ ልማዳችሁን ተገዳደሩት፣ ለማንም ሳይሆን ለራሳችሁ ብላችሁ ወስኑ።

አዎ! ጀግናዬ..! አንድ ውሳኔ ብቻ! የማቆም ወይም የመጀመር ውሳኔ፣ ህብረት የመፍጠር ወይም ከሚጎዳህ አካባቢ ነቆሎ የመውጣት ውሳኔ፣ ትምህርትን በአግባቡ መማር ካልሆነም ጨክኖ ፊትን ወደሌላ የማዞር ውሳኔ፣ በሱስ ላይ መጨከን ወይም ሱሱ ጨክኖ እንዲያጠፋህ የመፍቀድ ውሳኔ። ለሌላው የሆነው ሁሉ ላንተም ይሆናል ማለት አይደለም፣ ብዙ ሰውን ትርፋማ ያደረገ ቢዝነስ አንተንም ትርፋማ ያደርግሃል ማለት አይደለም፣ ጥቂቶችን ትልቅ ደረጃ ላይ ያደረሰ ትምህርት አንተንም ያደርስሃል ማለት አይደለም። ማንም ሰው ነፃ የሚወጣው የሰዎችን ተግባር በመከተል ሳይሆን የእራሱ የማያወላዳ ፅኑ አቋም ሲኖረው ብቻ ነው። የመጣው ቢመጣም ከውድቀትና በሰዎች ከመተቸት በቀር የሚመጣ ነገር የለምና በአዕምሮህ ተሸክመህ የምትሔደውን ውሳኔ በድፍረት ምድር ላይ አውርደው፣ አዕምሮህን ከግብ አልባው የማያባራ ሃሳብ ገላግለው። ጭንቀት ኖሮበት የተሻለ የህይወት ደረጃን የሚመኝ ሰው የለምና በቅድሚያ ባልተወሰኑ ውሳኔዎች የታጠረውን ጨንቀትህን ለመቀነስ ወስን፣ ለውሳኔህ ታመን፣ ወደምትመኘው የተለየ ህይወትም በድፍረት ጉዞ ጀምር።
ግሩም ድንቅ ቀን ይሁንልን! 🌅🌞🏞
(Epha A.)
ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ! 🦋

🔺🔻በYouTube ቤተሰብ ስለሚሆኑ እናመሰግናለን!
SUBSCRIBE NOW! 👇
https://www.youtube.com/channel/UCIZv4h3iDx2C7CGbv9WIkVg?sub_confirmation=1
ምክረ-አዕምሮ/ @MentalCounsel 😊💪


የደስተኛነት ምርጫ!
፨፨፨፨///////፨፨፨፨
አንደኛው ምርጫህ በኑሮህ የጎደለውን ነገር እየቆጠርክ ማዘንና መነጫነጭ ነው፡፡ ሌላኛው ምርጫህ ግን ከሌለህና ከጎደለህ ነገር ላይ ትኩረትህን በማንሳት ባለህ ነገር ደስተኛ ሕይወትን ለመምራት መወሰን ነው፡፡  

አንድ ሰው እንዲህ ሲል ተናገረ …

"ከ13ኛው ክፍለ-ዘመን በፊት የነበሩ አባቶቻችን ስኳር የሚባል ነገር አያውቁም ነበር - ነገር ግን ደስተኞች ነበሩ …
ከ14ኛው ክፍለ-ዘመን በፊት አባቶቻችን የኤሌክትሪክ ምድጃ ቀርቶ ከሰል የሚባል ነገር እንኳን አያውቁም ነበር - ነገር ግን ደስተኞች  ነበሩ … 
ከ15ኛው ክፍለ-ዘመን በፊት የነበሩ አባቶቻችን በቅጡ የተጋገረ ዳቦ የሚባል ነገር አያውቁም ነበር - ነገር ግን ደስተኞች ነበሩ …
ከ16ኛው ክፍለ-ዘመን በፊት የነበሩ አባቶቻችን ድንች የሚባል ነገር አያውቁም ነበር - ነገር ግን ደስተኞች ነበሩ …
ከ17ኛው ክፍለ-ዘመን በፊት የነበሩ አባቶቻችን ቡና፣ ሻይና ሾርባ የሚባሉ ትኩስ ነገሮች አያውቁም ነበር - ነገር ግን ደስተኞች ነበሩ …
ከ18ኛው ክፍለ-ዘመን በፊት የነበሩ አባቶቻችን ኬክና የመሳሰሉት ጣፋጭ ምግቦች የሚባል ነገር አያውቁም ነበር - ነገር ግን ደስተኞች ነበሩ …
ከ19ኛው ክፍለ-ዘመን በፊት የነበሩ አባቶቻችን እንቁላል፣ ክብሪትና የኤሌክትሪክ ኃይል የሚባል ነገር አያውቁም ነበር - ነገር ግን ደስተኞች ነበሩ …
ከ20ኛው ክፍለ-ዘመን በፊት የነበሩ አባቶቻችን ተዘጋጅቶ የታሸገ ምግብ የሚባል ነገር አያውቁም ነበር - ነገር ግን ደስተኞች ነበሩ …"
(Unknown Source)

በዚህ ላይ መጨመር ካለብን ከላይ በተዘረዘሩት ክፍለ-ዘመናት ይኖሩ የነበሩ አባቶቻችንና እናቶቻችን ዛሬ የምናውቃቸውን የማሕበራዊ መገናኛ ዘዴዎች አያውቁም ነበር - ነገር ግን ደስተኞች ነበሩ፡፡

ምናልባት ይህንን ጽሑፍ እያነበብክ ያለህበት የዓመቱ ስንተኛው ወር ላይ እንደሆነ ባላውቅም፣ እስቲ ዓመቱ ከገባ ጀምሮ እስከዛሬዋ ቀን ድረስ አለኝ በምትለውና ጎድሎኛል በምትለው ነገር አንጻር የነበረህን ዝንባሌ ለማስታወስ ሞክር፡፡ ምናልባት ስለሌለህ ነገር ስትበሳጭና ስሜትህ ሲቃወስ ራስህን አግኝተኸዋል ብዬ እገምታለሁ፡፡ አሁን በተያያዝከው ሕይወት ውስጥ የምትፈልገውን ነገር ሁሉ ያለማግኘትህ እውነታ ደስተኛነትህን እንድታዘገየው ከተጫነህ የሕይወት ዘይቤ ምርጫህን ማስተካከል እንዳለብህ ጠቋሚ ነው፡፡

የሆነውን ሳይሆን ያልሆነውን ማሰላሰል በርካታ ጠንቆች አሉት፡፡ ከብዙዎቹ ጥቂቶቹን ለመጥቀስ ያህል፣ በሌለንና በጎደለን ነገር ላይ ብቻ ማተኮር ታላቅ የሆነን የስሜት ቀውስ ያስከትላል፡፡ የመነሳሳትና ወደፊት ለመቀጠል የሚኖረንን ግለት ያበርድብናል፡፡ በሁኔታው የሚኖረንን የመነጫነጭ ባህሪ በመመልከት የቅርብ ወዳጆቻችን ቀስ በቀስ እየራቁንና ከእኛ ጋር ለመሆን ያላቸውን ፍላጎት እያጡ ይሄዳሉ፡፡ እንግዲህ ከእነዚህና ከመሰል አጉል ተጽእኖዎች ለመዳን ትክክለኛውን ምርጫ መከተል የግድ ነው፡፡

ዛሬ ለሌለህ ነገር እየሰራህና መለወጥ ወደምትፈልገው የተሻለ የባህሪይ ማንነት ለመለወጥ እየተጋህ ሳለህ፣ ባለህ ነገር ግን ደስተኛ መሆን ትችላለህ፡፡
/ከምርጫና ውሳኔ መጽሐፍ ገፆች/
ውብ ምሽት ይሁንልን! 🌘🌒💫✨
ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ! 🦋

🔺🔻በYouTube ቤተሰብ ስለሚሆኑ እናመሰግናለን!
SUBSCRIBE NOW! 👇
https://www.youtube.com/channel/UCIZv4h3iDx2C7CGbv9WIkVg?sub_confirmation=1
ምክረ-አዕምሮ/ @MentalCounsel 😊💪


ከሆንከው በላይ ነህ!
፨፨፨፨/////////፨፨፨፨
የቀድሞው ሞነክሴ የአሁኑ ፀሃፊ፣ ፖድካስተርና የህይወት ክህሎት አሰልጣኝ ጄይ ሼቲይ (Jay Shetty) ይህን ይለናል "እንደ አማራጭ ለሚመለከትህ ሰው በፍፁም ቅድሚያ አትስጠው።"

አዎ! ከሰዎች ጋር ባለን ግነኙነት ብዙዎቻችንን ከምናተርፈው ነገር የምናጠውና የምንከስርበት ሁኔታ ይበልጣል። ያላንተ ፍቃድ ማንም ሊጎዳህ ቢፈልግ ሊጎዳህ አይችልም። ለመጎዳት የምትፈቅደው፣ ሁን ብለህ የምትጠጋው፣ የምትቀርበው፣ የማይገባውን ስፍራ የምትሰጠው አንተ እራስህ ነህ። ለደቂቃ የማያስታውስህን ሰው ቀኑን ሙሉ እያሰቡ መዋል፣ ለአፍታም ትኩረት የማይሰጥህን ሰው በሙሉ ትኩረት መከታተል፣ አንዴም ሊያናግርህ ያልፈቀደን ሰው ደጋግመህ ደጅ መጥናት፣ መለመን፣ መለማመጥ ጤነኝነት ይመስልሃልን? እኔን ለማኝ እርሱን ተለማኝ፣ እኔን መራጭ እርሱን ተመራጭ፣ እኔን አሳቢ እርሱን ታሳቢ ያደረገው ነገር ምንድነው ብለህ እራስህን ጠይቅ። ምናልባትም ምላሽህ ደረጃህን እንድታውቅ ይረዳህ ይሆናል፤ እግረመንገዱንም እራስህን ለማግኘት ይጠቅምህ ይሆናል። ቻይ ነኝ ብለህ የማትወጣው ፉክክር ውስጥ አትግባ፤ ጊዜ አለኝ ብለህ የማይፈልግህን በመለማመጥ ጊዜህን አታባክን፤ ለምን አልተወደድኩም ብለህ እራስህን አትጣ።

አዎ! ጀግናዬ..! አንተ ከሆንከው በላይ ነህ፤ ሰዎች ከሚሰጡህ ክብር በላይ ይገባሃል፤ ካለህበት ስፍራ የተሻለ ቦታ ትደርሳለህ፤ ዛሬ ከናቁህ ሰዎች በላይ የሚያከብረህ ይመጣሉ፤ ዛሬ ሊያስቡህ ደቂቃ ካጠራቸው በላይ ለደቂቃዎች በመገኘትህ ትልቅ ተፅዕና የምትፈጥርበት ወቅት ይመጣል። ማንም እንደ አማራጭ ቢመለከትህ፣ ወደኋላ ቢገፋህ ቀዳሚ ምርጫው የሚያደርግህም እራስህን ያስቀደምክ እለት ከተፍ ይላል። ማንንም ልትወድ፣ ልታፈቅር፣ ልትወዳጅ፣ ልታደንቅ ትችላለህ በክብርህ እንዲመጣ፣ ማንነትህን እንዲገዳደር፣ አንተነትህን እንዲጋፋ ግን በፍፁም እንዳትፈቅድ። ሲቀር ለሚቀር ነገር የምትቃጠልበትና ሃፍረት የምትከናነብበት ምክንያት የለም። ክብር ያልወደደለት በገዛ ፍቃዱ ከክብሩ ይወርድ ዘንድ የግድ ነው። እያሳመመህ፣ እያሰቃየህ፣ እየገደለህ የምትሸከመው አላስፈላጊ ሸክም አይኖርም። የሚጣለውን ለመጣል፣ አላስፈላጊውን ለመራቅ፣ ጎጂውን ለመነጠል ድፍረት ይኑርህ።

አዎ! ትልቁ ሃይል በእጅህ አለ። በእራስህ ጉዳይ ፈላጭ ቆራጩ፣ ወሳኙ አንተ ነህ። ክብርህ፣ ጥንካሬህ፣ ኩራትህ፣ ስብዕናህ፣ ማንነትህ አንተ ጋር ነው። ስትፈልግ የምታነሳው፣ ሳትፈልግ የምትጥለው እድገትና ውድቀቱ በእራስህ መልካም ፍቃድ ላይ የተመሰረተ ወሳኝ የአንተነትህ መለኪያ ነገር አለህ። የእራስህን ክልል አብጅ፣ ቀዩን መስመር አብጅ፣ አልሚ መሳይ አፍራሽ፣ ወዳጅ መሳይ ጠላት፣ አፍቃሪ መሳይ ጎጂ እንዳይሻገረው በጥንቃቄ ጠብቀው። ማንነትህ የፍቃድህ ነፀብራቅ እንደሆነ አስተውል፤ የህይወት መርህህ አንተነትህንና ስብዕናህን እንደሚገነባ ተረዳ።
ውብ ቀን ይሁንልን! 🏞🌞🌅
(Epha A)
ምክረ-አዕምሮ ለተሻለ ነገ! 🦋

YouTube አማራጭ ይቀላቀሉን!
🔺🔻 SUBSCRIBE NOW
https://www.youtube.com/channel/UCIZv4h3iDx2C7CGbv9WIkVg?sub_confirmation=1
ምክረ-አዕምሮ/ @MentalCounsel 😊 💪


❤️❤️❤️🙏🙏🙏
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች እንኳን ለስቅለት በዓል በሰላም አደረሳችሁ እንላለን :: ውዶች መልካም በዓል ::🙏🙏🙏❤️❤️❤️


በመኪና የተገጨችው ላም ከመሬት ወድቃ ታቃስታለች ። ሰውነቷ ተልጧል ። እግሯም ተሰብሯል ። መነሳት አቅቷት ተዘርራለች ። መኪናው የደረሰበትን ጉዳት ለማየት ሰዎቹ ዙርያውን ከበው ቆመዋል ። ላሟ ብቻዋን ናት ። ማንም ወደ እሷ ዞሮ ያያት ፣ ጉዳቷንም ከቁብ የቆጠረ አልነበረም ። እሷ የተሰማትን ህመምና ስቃይ መኪናው አልተሰማውም ። ሰዎቹ የከበቡት ግን መኪናውን ነበር ። ላሟ የሰው ልጅን ጭካኔ በገፅታዋ በኩል ትነግረናለች ። የማወራችሁ ስለ ህሊና ነው ።

6.3k 0 17 15 150
20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.