የእንጅባራ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሰረተ ልማትጽ/ቤት ከሙሀመድ ኮምፒውተር ቴክኖሎጂ የከተማ መሬት አስተዳደር ስርዓት ትግበራ ፕሮግራም ከሚመለከታቸው አካላት ጋር የውይይት መድረክ አካሄደ።
እንጅባራ ግንቦት 08/2017ዓ/ም በአዊ ብሔረሰብ አስተዳደር እንጅባራ ከተማ አስተዳደር ከተማና መሠረተ ልማት ጽ/ቤት የከተማ መሬት አስተዳደር ስርዓት እና የሲቪል ሰርቪስና የሰው ሃብት ልማት ጽ/ቤት የሰው ሃብት ልማት መረጃ አስተዳደር ስርዓትን ለማዘመን የድጅታላይዜሽን ተግባር የማስጀመሪያ ፕሮግራም ተካሄደ።
በፕሮግራሙ የአዊ ብሔ/አስ/ም/አስተዳዳሪ እና የከተማና መሠረተ ልማት መምሪያ ሀላፊ አቶ አይተነው ታዴ፣የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ሲቪል ሰርቢስና የሰው ሃብት ልማት መምሪያ ሃላፊ ወ/ሮ ትግስት መኩሪያውን ጨምሮ የእንጅባራ ከተማ አስተዳደር አመራሮች፣ የሚመለከታቸው ወካይ የከተማው ነዋሪዎች እንዲሁም ባለሙያዎች ተገኝተዋል።
የአዊ ብሄረሰብ አስተዳደር ም/አስተዳዳሪና ከተማና መሠረተ ልማት መምሪያ ኃላፊ አቶ አይተነው ታዴ እንደገለፁት ዜጎች ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ፣ የመንግስት አገልግሎት ከብልሹ አሠራር የፀዳ እንዲሆን፣ የመልካም አስተዳደር ችግርን የሚያስቀር እንደሆነ ዓላማ አድርጎ የተነሳ የዲጂታላይዜሽ ፕሮግራም ነው ብለዋል። አያይዘውም ለዲጂታላይዜሽን ተግባር የከተማው ነዋሪና ባለሀብቶች መደገፍና ባለቤት መሆን እንዳለባቸው አሳስበዋል ። በተጨማሪም አሁን ላይ አለም ወረቀት አልባ የመረጃ ስርዓት እየዘረጋ ባለበት ወቅት የዲጅታላይዜሽንን ተግባር ማዘመን የግድ መተግበር አለበት ብለዋል።
በመጨረሻም የከተማው አገልግሎት አሰጣጥ ቀልጣፋና ከብልሹ አሠራር የፀዳ እንዲሆን የዲጅታላይዜሽን ትግበራው በተፋጠነ ሁኔታ እንዲጠናቀቅ የከተማው ባለሀብቶች የበኩላቸውን አስተዋፅኦ አደረጉ።
1. ካርኒድ ሆቴልና ስፓ 20,000ብር
2. በላይነህ አቡኑ 15,000ብር
3. ግሬስ ሆቴል 10,000ብር
4. ጉድ ሆፕ ሆቴል 10,000ብር
5. ቴወድሮስ ወርቁ 15,000ብር
6. አለማየሁ ጫኔ 10,000ብር
7. አለኸኝ ልየው 5,000ብር
8. በጋሻው ቢተው 10,000ብር
9. ደሴ ተገኘ/ደሴ ሎጅ/ 5,000ብር
10. ቦጋለ አይናለም/ደላላ/ 5,000ብር
11. ኢንጅነር አዱኛ አሳዬ ከእንጅባራ ዩንቨርስቲ 5,000ብር
12. ዳዊት ባንቲሁን/እናት ዱቄት ፋብሪካ 10,000ብር
13. ኢንጅነር አለኸኝ መኩሪያ ከዚህ በፊት 5,000ብር
14. ቻሌ ግሻጉም 5,000ብር
✅ ጊዜው የዲጅታል የቴክኖሎጂ ነው፡፡
ህልምዎን እውን የሚያደርጉ ሲስተሞችን, ድረ-ገጾችን (ዌብሳይቶችን) ለማሰራት ይደውሉ። አሰራርዎን ዘመናዊ ያድርጉ!
🔴አድራሻ:-
✅ ስ.ቁ: 0929273364
✅ ዌብሳይት
www.mctplc.com✅ቴሌግራም አካውንት:
https://t.me/mctplc✅ በቴሌግራም ቻናል:
https://t.me/MuhammedComputerTechnology✅ email: mct16plc@gmail.com
✅ Facebook:-
https://m.facebook.com/MuhammedComputerTechnology/✅ ቲክቶክ አካውንት
tiktok.com/@mctplc✅ የYouTube ቻናልን ሰብስካራይብ በማድረግ ወቅታዊ የቴክኖሎጂ መረጃን ያግኙ!
👇👇👇Subscribe👇👇👇
https://youtube.com/@muhammedcomputertechnologyየተቋምዎን መረጃን ዲጅታላይዝ እናድርግልዎ ስንል በደስታ ነው!