Mesafint Tefera


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


አስተማሪ የሆኑ የጤና፣ የሳይንስ፣ ድንቃድንቅና ስነጽሁፉዊ ይዘታቸው ከፍ ያሉ ጽሁፎችን እናጋራዎታለን።

Связанные каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


ኮሎምበስን ከረሀብ የታደገች ግርዶሽ
**************************

ከ500 ዓመታት በፊት ያጋጠመ ፈገግ የሚያሰኝ እውነተኛ ታሪክ ነው።

ብዙዎቻችን እንደምናውቀው ክርስቶፈር ኮሎምበስ ዝነኛ መርከበኛ ነበር። በዋናነትም 'አሜሪካን ለመጀመርያ ጊዜ ያገኛት ሰው' በሚል ይታወቃል። ያኔ የሁሉ ነገር እምብርት አውሮፓ ስለነበረች አሜሪካንን ማንም ነገሬ ብሎ አያውቃትም ነበር!!

ታዲያ ይሄ ትውልዱ ጣልያን የሆነ የስፔን መርከበኛ እንደተለመደው ከተቀጠረበት ሀገር ከስፔን ተነስቶ ዓለምን ሲዞር ሲያስስ ከአራቱ መርከቦቹ ሁለቱ በጉዞ ወቅት ሙሉ ለሙሉ ከጥቅም ውጭ ይሆኑበታል። ደግሞ ብቻውን አልነበረም፤ ብዙ ሰዎች አብረውት ነበሩ። የተቀሩት ሁለቱ መርከቦቹም በውቂያኖሱ ጨው እንጨታቸው እየተበላ በስብሰው አላስኬድ ማለት ሲጀምሩ ወደ አንድ ጠረፍ ተጠግተው ለማረፍ ግድ ሆነባቸው። በእንቅርት ላይ ጆሮ ደግፍ እንዲሉ እነዚያ ተጓዦች ስንቃቸውም ማለቅ ጀመረ።

ያረፉበት ቦታ ያሁኑዋ ጃማይካ የምትገኝበት አካባቢ ነበር። መቸም ያካባቢው ሰዎች እንዴት ያሉ ደጋጎች ነበሩ መሰላችሁ፤ በጥሩ አቀባበል አስተናገዷቸው፤ የሚበሉትን ቀለብ፣ የሚለብሱትን ቃጫ መሰል ልብስ እና የሚያርፉበትን ድንኳን መሳይ ቤት ሰጧቸው። ታዲያ ከዚህ በላይ ምን ይፈልጋሉ?!

ኮሎምበስና ጀሌዎቹ በዚህ መልኩ ያገራቸው መንግስት መርከብ ልኮ እስኪወስዳቸው ድረስ በጃማይካ በእንግድነት ለወራት ሲጠባበቁ ከረሙ። ታዲያ በቆይታቸው ወቅት ግጭት መፈጠር ጀመረ። ለነገሩስ እንኳን ሰውና ሰው ድንጋይ ከድንጋይ ይጋጭ የለ፤ የተደበቀ አመልም ቀስ በቀስ ይወጣል።

ጃማይካውያኑ ባስተናገዷቸው የኮለምበስ ጀሌዎች ሴቶቻቸውን መጎምጀት፣ ንብረታቸውን መዝረፍ፣ ያይኑ ቀለም ያላማራቸውን በቡጢ መጠለዝ ሲጀምሩ ግጭት ተፈጠረ። በዚሁ መነሾ ጃማይካውያኑ ምግብና መጠጥ ከለከሏቸው። ኮሎምበስ ጨነቀው! ሰዎቹ በርሀብ ሊያልቁበት ሆነ። መፍትሄ ፍለጋ ሲያወጣ ሲያወርድ ቆይቶ አንድ ዘዴ መጣለት።

የዚያን እለት ማታ ከአካባቢው ሰዎች እና የጎሳ መሪው ጋር ቀጠሮ ያዘ። እናም ሲመጡ፣

"በምግብ እየቀጣችሁን በመሆኑ እግዚአብሔር ተቆጥቷል። ቁጣ እንደሚያወርድባችሁም ነግሮኛል። ዛሬ ማታ ጨረቃዋን በማንደድ ቁጣውንም ያሳያችሁዋል" አላቸው።

ይሄን ንግግር ሲሰሙ ከመደንገጥ ይልቅ ሰዎቹ ተሳለቁበት። የጎሳውም መሪ አላመነውም፤ በፍጹም ሊሸወድለት አልፈቀደም። እናም 'ሞኝህን ፈልግ' ሲል መለሰለት።

ደቂቃዎች ተቆጠሩ፤ ኮሎምበስና ጓደኞቹ በተስፋ እየጠበቁ ነው፤ ቀኑን ሙሉ ምግብ ባፋቸው ስላልዞረ በርሃብ ተጎሳቁለዋል፤ አንዴ መሽቶ ጨረቃ ከተራራው ጀርባ ወጥታ የሚበሉትን ነገር እስኪያገኙ ድረስ የዓመት ያህል ረዘመባቸው።

በመጨረሻም ጨረቃ ወጣች።

ጃማይካውያኑ ጨረቃን ሲያይዋት በፍርሀት ይርዱ ጀመር። በጣም ተደናገጡ። እንደተባለው ጨረቃ ደም ለብሳለች። ደሞም ከጎን በኩል የሆነ ነገር የገመጣት ትመስላለች። ያካቢው ነዋሪዎች ተሸበሩ፤ የሚያደርጉት ነገር ጠፋቸው።

ቢጨንቃቸው ኮሎምበስን መለመን ጀመሩ። ከፈጣሪ ቁጣ እንዲገላግላቸው ተማጸኑት። የጠየቃቸውን ምግብና መጠለያ እንደሚሰጡትም ቃል ገቡለት። ቅድም 'ሞኝህን ፈልግ' ሲል በኮሎምበስ የተሳለቀው ያ የጎሳ መሪ በተረበሸ ስሜት ሆኖ የተማጽኖ ድምጹን አሰማ።

"የፈለከውን ያህል ምግብ ላንተና ለጓደኞችህ መውሰድ ትችላለህ፤ ብትፈልግ ቤታችንን እንለቅልሃለን፤ አገልጋዮችም እንመድብልሃለን፤ ብቻ ከፈጣሪ አስታርቀን!" አለው።

ከብዙ ልመናና ጉትጎታ በሁዋላ ኮሎምበስ ተናገረ።

"እስኪ ፈጣሪ ከሰማኝ ጸሎት ላድርስ" አለና ወደ ድንኳኑ ገብቶ ቆየ።

ኮሎምበስ፣ ከዓመታት በፊት ጀርመናዊው የስነ-ክዋክብት አጥኝ ቮን ኮኒስበርግ ያዘጋጀውን የአስትሮኖሚ ሰንጠረዥ አንብቧል። ስለዚህም በዚያን እለት፣ የካቲት 29 1504 ዓ.ም (እ.አ.አ)፣ ለ48 ደቂቃ የሚቆይ የጨረቃ ግርዶሽ እንደሚያጋጥም ቀድሞ ያውቅ ነበር። እናም ወደ ድንኳኑ ገብቶ ያንን የአስትሮኖሚ ሰንጠረዥ ተመልክቶ የጨረቃው ግርዶሽ የሚያበቃበትን ትክክለኛ ደቂቃ ካልኩሌት አድጎ አረጋገጠ። ከዚያም ሁለት ደቂቃ ያህል ቀድሞ ወደ ጃማይካውያኑ ተመለሰና፣

"እግዚአብሔር ጸሎቴን ሰምቷል፤ ምህረት እንደሚያደርግላችሁም ነግሮኛል" አላቸው።

ወዲያው ጨረቃ በደም የተነከረ ክንብንቧን አወለቀች። ይሄን ጊዜ ያካባቢው ነዋሪዎች በእንባ ተሞልተው "ክብር ለፈጣሪ ይሁን" እያሉ ጨፈሩ። ኮሎምበስም በፈገግታ ተሞልቶ "ክብር ለሣይንስ" አለ፤ በሆዱ ነው ታዲያ።

በዚህ መልኩ ኮሎምበስና ጓደኞቹ ያካባቢው ሰዎች ሸውድው ምቹ መኝታና መጠለያ ከብዙ ምግብና መጠጥ ጋር አግኝተው ቆዩ። ከሦስት ወር በሁዋላም የስፔን መንግስት መርከበኛ ልኮ ወደ ሀገራቸው እስኪመልሳቸው ድረስ የጨረቃ ግርዶሽን እያመሰገኑ ተቀማጥለው ኖሩ።

(©መሳፍንት ተፈራ፣ ሰኔ 2012 ዓ.ም)

👉 በነገራችን ላይ ቆየት ያሉና ከገበያ የጠፉ መጽሐፍትን ማግኘት ከፈለጉ ቀጣዩን ቴሌግራም ይቀላቀሉ፣ ሜክሲኮ አምደ መጻሕፍት በማፋለግ ይረዳዎታል!!

https://t.me/mexibooks






ረዳት ፕሮፌሰር ነብዩ ባዬ🙏🙏
#ፈገግታሽን_ፍለጋ ❤️❤️


#ፈገግታሽን_ፍለጋ 💙💛
ፈገግ ብለው ከሚያነብቡኝ መካከል 🙏🙏

ጽዮን መኮንን


ወዳጆቼ፣ መጽሐፌ ገበያ ላይ ስለዋለ ደስ ብሎኛል። 😊ከነገ ጀምሮ በሁሉም መጽሐፍ መደብሮችና በአዟሪዎች እጅ ማግኘት ይቻላል።

👉 አከፋፋይ - ኤዞፕ መጽሐፍ መደብር
👉 አድራሻ - ፒያሳ (አቡነ ጴጥሮስ አደባባይ)፣ 0911723656

አራት ኪሎ አካባቢ፣ ከቱሪስት ሆቴል ጀርባ፣ ኢክላስ ህንጻ ላይ ወደ ተዘጋጀው የመጽሐፍ አውደ ርዕይ ጎራ ብትሉም መጽሐፉን ታገኙታላችሁ...

Cheers!! 💛💙
✍መሳፍንት ተፈራ


በነገራችን ላይ የለሜቻ ግርማ የብር ሜዳልያ በዘርፉ ለኢትዮጵያ ሁለተኛዋ ነው፤ ትልቅ ድል ተደርጎ መታየት አለበት፡፡ ከ1980 በኋላ በታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ነው በ3ሺህ መሰናክል የብር ሜዳልያ ያገኘነው፡፡ ለዘመናት ኬኒያውያን ባህላዊ ጨዋታችን እያሉ ሲኩራሩበት እንዳልኖሩ አሁን ሀገራችን የሜዳልያ ሰንጠረዥ ውስጥ በመግባት ወሳኝ ተቀናቃኝ መሆን ጀምራለች፡፡
ድል ለሀገራችን! 💚💛❤️


ተመልከቱልኝማ - ትውልድ ላይ ምን እንደሚሠራ... 'ኳንተም ፊዚክስ ለልጆች' ሲገርመኝ ጭራሽ ለህጻናትም እንዲስማማ አድርገው አዘጋጅተውታል። ምስኪን እኛ፥ ፊዚክስ የቋጥኝ ያህል ለምን እንደከበደን አሁን ገባኝ። እንኳን ኳንተም ፊዚክስ የተረት መጽሐፍ ቅንጦት እየሆነብን እንዴት ብሎ ይግባን? እኔ በበኩሌ ፊዚክስ የሚለውን ቃል ለመጀመሪያ ጊዜ የሰማሁት ሰባተኛ ክፍል ስደርስ ነበር።

እዩት ደግሞ በፎቶ ላይ ማን እንዳለ... ዙከርበርግ። እኛን በፌስቡክ አጨናንቆ እሱ፥ ልጁ የቀጣዩ ዓለም ገዥ እንዲሆንለት፣ ጠፈርን እንዲቆጣጠር ከወዲሁ ያዘጋጀዋል። የእኛ ሰው ፌስቡክ ላይ ተጥዶ ዘር እየቆጠረ የልጁን ተስፋ ያጨልማል!!

ሰናይ ጊዜ!
✍መሳፍንት ተፈራ








የአሌክስ አብርሃም " ከዕለታት ግማሽ ቀን " የተሰኘው መጽሐፍ ለንባብ በቃ።

📚 መልካም ቅዳሜ ይሁንልን !!


መጽሀፉን በpdf ከላይ ያገኙታል




ገምቱ! ማን ነው?😂








ኢትዮጵያውያን እናቶች ከሚጠቀሙባቸው ባህላዊ መድኃኒቶች ጥቂቶቹን (ሼር ይደረግ!)

ከእነዚህ ውስጥ አብዛኞቹን በየቤታችን እናቶችን
ይጠቀሙበታል።

✅ #ጤና_አዳም

ቅጠሉም ሆነ ፍሬው ለሆድ መታወክ፣ ለቁርጥማትና ለሌሎች መሰል ሕመሞች መድኃኒት ነው።

✅ #ዳማከሴ

ለጉንፋን ፣ ለከባድ ራስ ምታት (ማይግሬን) በአፍንጫ ተስቦ የሚወሰድ ፣ ለመተንፈሻ ቧንቧ ችግርና አጠቃላይ ለምች ፍቱን መድኃኒት ነው።

✅ #ፌጦ

ለድንገተኛ ህመምና ውጋት ተወቅጦና ተበጥብጦ በመጠጣት ከህመም መፈወስ ይቻላል።

✅ #ጣዝማ_ማር

ከመሬት ተቆፍሮ የሚገኝ የማር ዓይነት ሲሆን ከነጭ አዝሙድና ኮረሪማ ጋር በመቀላቀል ጠዋት ጠዋት ሁለት ማንኪያ በመውሰድ ከሳል ፣ ከአስም ፣ ከቁርጥማት ወዘተ ህመም መገላገል ይቻላል። ይህንን መድኃኒት የወሰደ አንድ ሰው መድኃኒቱ እንዲሠራ ቢያነስ ከአንድ ሰዓት እስከ አንድ ሰዓት ተኩል ጊዜ ድረስ ሌላ ተጨማሪ ነገር እንዳይጠጣ ይመክራል።

✅ #ቀበርቾ

ከስራስር ክፍል የሚመደብ ሲሆን አገልግሎቱም ለድንገተኛ ህመም፣ ውጋት ወዘተ በማኘክ የሚወሰድ ፈዋሽ መድኃኒት ነው።

✅ #የነጭ_ባህርዛፍ_ቅጠሉ

ቅጠሉን በውሃ ተፈልቶ ቢታጠኑት የመተንፈሻ አካል ችግርም ሆነ የትኛውም የጉንፋን ዓይነትን ያለ ኪኒን በሁለት ቀን ውስጥ ፈውስ ያገኛል።

✅ #ነጭ_ሽንኩርት

ለደም ዝውውር ፣ ለጨጓራ ፣ ለውስጥ ካንሰር፣ ለመተንፈሻ አካል፣ ለወሲብ ማነቃቂያነት እና በሰውነት ውስጥ ምግብ እንዲንሸራሸር ፍቱን መድኃኒት እንደሆነ አዋቂዎች አብነት በመጥቀስ ይናገራሉ።

✅ #share አድርጉን... ያተርፉበታል


ወርቃማ ህጎች
*********
አንብቡት ይጠቅማል--- አንብበው ሼር ያድርጉት!!

❇ የሚሞትለት ዓላማ የሌለው ሰው ለመኖር ብቁ አይደለም
❇ ብቸኛው ጥሩ ነገር ማወቅ ሲሆን፤ ብቸኛው መጥፎ ነገር ደግሞ መሃይምነት ነው።

❇ ባለው ነገር የሚረካ ሰው ሃብታም ነው
❇ በዚች ምድር ሁሉም ነገር ያልፋልና ስታገኝም ከልክ በላይ አትደሰት፤ ስታጣም? አብዝተህአትከፋ።

❇ በአስቸጋሪ ፈተና መሃል እድል ተቀምጣ ሊሆን ይችላል።
❇ ታላቁ ክብራችን አለመውደቃችን ሳይሆን፤ በወደቅን ቁጥርመነሳታችን ነው።

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.

2 901

obunachilar
Kanal statistikasi