Hidaya Info dan repost
🪷 ልጆችዎን በማሳደግ ረገድ ስኬትዎን የሚወስኑ አምስት ነገሮች፡-
1. ከመስተጋብር አንፃር፡
ልጆች እንዲወዱህ፣ ወዳንተ ሲቀርቡ ምቾት እንዲሰማቸው፣ ሳትኖር ስትቀር እንዲናፍቁህ፣ ምስጢራቸውን እንዲያጫውቱህ፣ ወደ ቤትህ ስትመለስ ደስተኛ እንዲሆኑ አድርግ። በቤት ውስጥ መረጋጋትና ስምምነት እንዲሰፍን ያደርጋል።
2. ከሥነ ምግባር አንፃር:
ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ ሥነ ምግባራቸው ለማስተካከል ተገቢውን ጥረት ማድረግ። ይህ ሲባል ልጆች ስህተት እንዳይሠሩና ፍፁም እንዲሆኑ ማድረግ ማለት አይደለም፤ ይልቁን ክፍተቱ ያነሰ እንዲሆን መጣር ነው።
ከውብ ሥነ ምግባራቸው መካከል፡- ጀግንነት፣ ሐፍረት፣ ጥብቅነት፣ ታማኝነት፣ እውነተኝነት፣ ጨዋነት፣ መተናነስ እና ትሕትና ይገኙበታል።
3. ከአምልኮ አንፃር፡
ጠንካራ ኢማን በውስጣቸው ማስረጽ፤ እምነታቸውን ከሽርክ ማጽዳት፣ ዒባዳቸውን በዕውቀት ላይ የተመረከዞ ማድረግ፤ በተለይ በሰላታቸው ላይ ቀጥ እንዲሉ ማበርታት እና የአላህን ቃል ቁርኣን ማስተማር።
4. ወንድማማችነት / እህትማማችነት መፍጠር፡-
በልጆች መካከላል የመከባበር፣ የመተሳሰብ እና የመተዛዘን መንፈስ እንዲኖር ማድረግ።
5. ከትምህርት (ዕውቀት) አንፃር፡-
ልጆች እንደፍላጎታቸው እንደ አቅምና ተሰጥዖዋቸው የሚፈልጉትን እንዲያሳኩ ማገዝ እንጂ የናንተን ሕልም እንዲያሳኩ አለመጫን፤ ስኬትን በዶክተርነት እና ፓይለትነት ብቻ የተገደበ አይደለም።
አላህ ሆይ ልጆቻችንን አስተካክልንን፤ እኛ ማስተካከል አንችልምና።
#የሂዳያ_ትውልድ #ለወላጆች #ምክር_ለተርቢያ
📮 የመጪው ትውልድ ሃላፊነት የጋራችን ነው!
መልዕክቱን ሼር በማድረግ ለብዙዎች እናድርስ!
💫 https://t.me/HidayaTerbiya 💫
1. ከመስተጋብር አንፃር፡
ልጆች እንዲወዱህ፣ ወዳንተ ሲቀርቡ ምቾት እንዲሰማቸው፣ ሳትኖር ስትቀር እንዲናፍቁህ፣ ምስጢራቸውን እንዲያጫውቱህ፣ ወደ ቤትህ ስትመለስ ደስተኛ እንዲሆኑ አድርግ። በቤት ውስጥ መረጋጋትና ስምምነት እንዲሰፍን ያደርጋል።
2. ከሥነ ምግባር አንፃር:
ሁለንተናዊ በሆነ መልኩ ሥነ ምግባራቸው ለማስተካከል ተገቢውን ጥረት ማድረግ። ይህ ሲባል ልጆች ስህተት እንዳይሠሩና ፍፁም እንዲሆኑ ማድረግ ማለት አይደለም፤ ይልቁን ክፍተቱ ያነሰ እንዲሆን መጣር ነው።
ከውብ ሥነ ምግባራቸው መካከል፡- ጀግንነት፣ ሐፍረት፣ ጥብቅነት፣ ታማኝነት፣ እውነተኝነት፣ ጨዋነት፣ መተናነስ እና ትሕትና ይገኙበታል።
3. ከአምልኮ አንፃር፡
ጠንካራ ኢማን በውስጣቸው ማስረጽ፤ እምነታቸውን ከሽርክ ማጽዳት፣ ዒባዳቸውን በዕውቀት ላይ የተመረከዞ ማድረግ፤ በተለይ በሰላታቸው ላይ ቀጥ እንዲሉ ማበርታት እና የአላህን ቃል ቁርኣን ማስተማር።
4. ወንድማማችነት / እህትማማችነት መፍጠር፡-
በልጆች መካከላል የመከባበር፣ የመተሳሰብ እና የመተዛዘን መንፈስ እንዲኖር ማድረግ።
5. ከትምህርት (ዕውቀት) አንፃር፡-
ልጆች እንደፍላጎታቸው እንደ አቅምና ተሰጥዖዋቸው የሚፈልጉትን እንዲያሳኩ ማገዝ እንጂ የናንተን ሕልም እንዲያሳኩ አለመጫን፤ ስኬትን በዶክተርነት እና ፓይለትነት ብቻ የተገደበ አይደለም።
አላህ ሆይ ልጆቻችንን አስተካክልንን፤ እኛ ማስተካከል አንችልምና።
#የሂዳያ_ትውልድ #ለወላጆች #ምክር_ለተርቢያ
📮 የመጪው ትውልድ ሃላፊነት የጋራችን ነው!
መልዕክቱን ሼር በማድረግ ለብዙዎች እናድርስ!
💫 https://t.me/HidayaTerbiya 💫