የአሜሪካ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ቲክቶክ የብሔራዊ ጸጥታ አደጋ በመደቀኑ እንዲዘጋ ካልሆነም እዲሸጥ ለሚጠይቀው የፌደራል ህግ ድጋፍ መስጠቱ ተሰማ፡፡
በፍርድ ቤቱ ዛሬ በተካሄደው የቃል ክርክር የቻይናው ባይትዳንስ ንብረት የሆነው ቲክቶክ እንዲታገድ በሙሉ የድምጽ ድጋፍ ማሳለፉን አሶሺየትድ ፕሬስ ዘግቧል።
በአሜሪካ ከ170 ሚሊየን በላይ ተጠቃሚ ያለው ቲክቶክ የተጠቃሚዎችን የግል መረጃ ለቻይና መንግስት አሳልፎ ይሰጣል በሚል ነው እንዲሸጥ ካልሆነም እንዲዘጋ የሚል ክስ የቀረበበት።
ዛሬ በተላለፈው ውሳኔ መሰረት ቲክቶክ ከእሁድ ጀምሮ የሚታገድ ሲሆን እግዱ ተግባራዊ ሲሆን መተግበሪያውን አዳዲስ ተጠቃሚዎች ማውረድ እንደማይችሉ እና ነባር ተጠቃሚዎች ደግሞ ማዘመን (አፕዴት) እንደማችሉ በመረጃው ተገልጿል።
ዶናልድ ትራምፕ የቲክቶክን ጠቀሜታ መገንዘባቸውና ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን እንዲያዘገይ ጠይቀው የነበረ ሲሆን ጉዳዩን በድርድር እፈታዋለሁ ማለታቸው ይታወሳል።
የአሜሪካ ጠቅላይ ፍርድ ቤት 9 ዳኞች ያሉት ሲሆን የሀገሪቱን ህገ መንግስት የሚጻረሩ ጉዳዮችን የመስማት፣ ለህግ ትርጓሜ የመስጠት፣ የሲቪል መብቶችን የማስጠበቅ፣ በግዛቶች መካከል የተፈጠሩ አለመግባባቶችን የመፍታት፣ ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን የሚመለከቱ ጉዳዮች የመምራት ስልጣን አለው፡፡
በፍርድ ቤቱ ዛሬ በተካሄደው የቃል ክርክር የቻይናው ባይትዳንስ ንብረት የሆነው ቲክቶክ እንዲታገድ በሙሉ የድምጽ ድጋፍ ማሳለፉን አሶሺየትድ ፕሬስ ዘግቧል።
በአሜሪካ ከ170 ሚሊየን በላይ ተጠቃሚ ያለው ቲክቶክ የተጠቃሚዎችን የግል መረጃ ለቻይና መንግስት አሳልፎ ይሰጣል በሚል ነው እንዲሸጥ ካልሆነም እንዲዘጋ የሚል ክስ የቀረበበት።
ዛሬ በተላለፈው ውሳኔ መሰረት ቲክቶክ ከእሁድ ጀምሮ የሚታገድ ሲሆን እግዱ ተግባራዊ ሲሆን መተግበሪያውን አዳዲስ ተጠቃሚዎች ማውረድ እንደማይችሉ እና ነባር ተጠቃሚዎች ደግሞ ማዘመን (አፕዴት) እንደማችሉ በመረጃው ተገልጿል።
ዶናልድ ትራምፕ የቲክቶክን ጠቀሜታ መገንዘባቸውና ጠቅላይ ፍርድ ቤቱ ውሳኔውን እንዲያዘገይ ጠይቀው የነበረ ሲሆን ጉዳዩን በድርድር እፈታዋለሁ ማለታቸው ይታወሳል።
የአሜሪካ ጠቅላይ ፍርድ ቤት 9 ዳኞች ያሉት ሲሆን የሀገሪቱን ህገ መንግስት የሚጻረሩ ጉዳዮችን የመስማት፣ ለህግ ትርጓሜ የመስጠት፣ የሲቪል መብቶችን የማስጠበቅ፣ በግዛቶች መካከል የተፈጠሩ አለመግባባቶችን የመፍታት፣ ዓለም አቀፍ ስምምነቶችን የሚመለከቱ ጉዳዮች የመምራት ስልጣን አለው፡፡