ሚዛን አማን
#ከተሞቻችን
የሚዛን አማን ከተማ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አንዷ መቀመጫና የቤንች ሸኮ ዞን ዋና መቀመጫ ሆና በማገልገል ላይ ትገኛለች፡፡
ከተማዋ ከርዕሠ መድናችን አዲስ አበባ በ568 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ ስትሆን በ1930 ዓ.ም እንደተቆረቆረች ይነገራል።
ሚዛን አማን ከተማ የቀድሞ ሚዛን ተፈሪ የሚለውን ስያሜ ያገኘችው በንጉሱ አፄ ኃይሌ ስላሴ ዘመነ መንግሥት አካባቢውን እንዲያስተዳድሩ ተሹመው በተላኩት በእንደራሴው ፊታውራሪ አለማየሁ ፍላቴ መሆኑ ይነገራል፡፡
የንጉስ አፄ ኃይሌ ስላሴ ልደት እየተከበረ በነበረበት ወቅት ከተማዋ በመመስረቷ የልደት መታሰቢያ ለማድረግ እንደሆነም ታሪክ ይጠቅሳል።
በ1ሺሕ 451 ሜትር ከባህር ጠለል በላይ ከፍታ ላይ የምትገኘው ሚዛን አማን በአረንጓዴ መልክዓ ምድር የተሸፈነች እና ወይናደጋ የአየር ንብረት ያላት ከተማ ነች።
እምቅ የተፈጥሮ ሀብት ያላት ሚዛን አማን በዙሪያዋ ከፍተኛ የደን ክምችት ያላት ሲሆን ቡናን ጨምሮ፣ በፍራፍሬ እና በቅመማቅመም ምርቶች ትታወቃለች፡፡ የአረንጓዴ ልማት ፈርጥ ተብላም ትጠራለች።
https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/posts/pfbid0NMmjbVppnwZjZ9NxBEeKkDnjSQ26t2A9oaG6xmD6MCFc7FEwdAG1pXAJxreKrLnJl