AddisWalta - AW


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha


This is Walta Media and Communication Corporate’s official Telegram channel.
For more updates please visit https://shorturl.at/ehosX https://www.youtube.com/c/WaltaTV/featured

Связанные каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


የፓፓዬ የጤና ጥቅሞች

#ጤና #health_tips #ፓፓዬ
#አዲስ_ዋልታ


በድንገተኛ አጋጣሚ የራስ ያልሆነን ንብረት ለመውሰድ መሞከር
#ሕግ_ይዳኘኝ

የራስ ያልሆነን ገንዘብ መጠቀም ወይም በሌላ ሰው ሀብት ያለአግባብ መገልገል ለህሊና እዳ በሕጉም ቅጣትን የሚያስከትል ድርጊት ነው። ይሁን እንጂ ብዙዎች የራሳቸው ያልሆነን ንብረት በድፍረት ለመጠቀም ተኝተው አያድሩም።

እነዚህን ሰዎች በተመለከተ የወንጀለኛ መቅጫ ሕጉ ላይ በግልጽ ሕጋዊ ቅጣት ተቀምጧል። በዛሬው “ሕግ ይዳኘኝ” መረኃ ግብራችን ይህንኑ ጉዳይ እንዳስሰዋለን።

በሰው ሀብት ንብረት ያለአግባብ መጠቀም ከየትኛውም ሃይማኖታዊ አስተምህሮም ሆነ ከህሊና የራቀ መጥፎ ልማድ እና ተግባር ነው።

በኢፌዲሪ የወንጀል ሕግ አንቀጽ 678 መሰረት ማንም ሰው ራሱን ወይም ሌላውን ሰው ያለአግባብ ለማበልጸግ በማሰብ፣ የንብረቱ ባለቤት በመብቱ እንዳይጠቀምበት ለማድረግ፣ በማታለል ወይም ለራሱ ወይም ለሌላ ሰው ለጊዜው መጠቀሚያ ለማድረግ የሌላውን ሰው ንብረት የወሰደ እንደሆነ የግል አቤቱታ ሲቀርብበት ከአምስት ሺሕ ብር በማይበልጥ መቀጮ ወይም ነገሩ ከባድ በሆነ ጊዜ ከአንድ ዓመት በማይበልጥ ቀላል እስራት ይቀጣል።

ማንም ሰው የማይገባውን ብልጽግና ለማግኘት ወይም ለሌላ ሰው ለማስገኘት በማሰብ የሌላ ሰው ንብረት ሆኖ በስህተት፣ ባልታሰብ ድንገተኛ አጋጣሚ ነገር፣ እንደ ውሃ ማዕበልና እንደነፋስ ባለ የተፈጥሮ ጠባይ በመጣ ኃይል ወይም ከባለቤቱ ፈቃድ ውጭ በሆነ በማናቸውም ሌላ ዓይነት ሁኔታ ከባለቤቱ እጅ ወጥቶ በእጁ የሚገኘውን ነገር (እቃ) ለራሱ ወይም ለሌላ ሰው ያደረገ እንደሆነ የግል አቤቱታ ሲቀርብበት በቀላል እስራት ወይም መቀጮ እንደሚቀጣ በወንጀል ሕጉ አንቀጽ 679 ላይ ተደንግጓል።

በብርሃኑ አበራ


አጓጊው ደሞ አዲስ መጋቢት 22 እሁድ #በቀጥታ ስርጭት ለእናንተ ለተመልካቾቻችን ተወዳዳሪዎቹን ይዞላችሁ ይቀርባል።

በቀጥታ ስርጭትም ዳኞችና ተወዳዳሪዎች በተመልካቾች ድምፅ ይዳኛሉ። በዕለቱም በተሰጣቸው ኮድ በ8970 SMS ድምጽ ይስጡ!

ኤፍሬም አየለ በB4
እንግዳው አስፋው በB5
ኃ/ኢየሱስ ታደገ በB6

#ደሞ_አዲስ #አዲስ_ዋልታ #music

እሁድ ከቀኑ 9 ሰዓት ጀምሮ በቀጥታ ስርጭት ይጠብቁን 🎼🎹🥁🎤🎺🎷🎸🎻


አጓጊው ደሞ አዲስ መጋቢት 22 እሁድ #በቀጥታ ስርጭት ለእናንተ ለተመልካቾቻችን ተወዳዳሪዎቹን ይዞላችሁ ይቀርባል።

በቀጥታ ስርጭትም ዳኞችና ተወዳዳሪዎች በተመልካቾች ድምፅ ይዳኛሉ። በዕለቱም በተሰጣቸው ኮድ በ8970 SMS ድምጽ ይስጡ!

ያሬድ አበበ በB1
አክሊሉ መለሰ በB2
ታረቀኝ ረጃው በB3

#ደሞ_አዲስ #አዲስ_ዋልታ #music

እሁድ ከቀኑ 9 ሰዓት ጀምሮ በቀጥታ ስርጭት ይጠብቁን 🎼🎹🥁🎤🎺🎷🎸🎻


ባህርዳር ከነማ የአለልኝ አዘነን 23 ቁጥር ማሊያ ቁጥር በክብር እንዲቀመጥ ወሰነ

መጋቢት 19/2016 (አዲስ ዋልታ) በድንገት ህይወቱ ያለፈው ወጣቱ አማካይ የእግር ኳስ ተጨዋች አለልኝ አዘነ የሚለብሰው የማሊያ ቁጥር በክብር እንዲቀመጥ መወሰኑን የባህርዳር ከነማ ስፖርት ክለብ አስታወቀ።

የጣና ሞገዶቹ ተጫዋቾች በኮከብ ተጫዋቻቸው ህልፈተ ህይወት የተሰማቸውን ሀዘን በትውልድ ስፍራው በመገኘት ገልፀዋል።

በዚህም አለልኝ አዘነ በባህር ዳር ከነማ ስፖርት ክለብ ይለብሰው የነበረው የማልያ ቁጥር 23 ከዚህ በኋላ ማንም የክለቡ ተጫዋች የማይለብሰው ሆኖ በክብር እንዲቀመጥ የባህርዳር ከነማ ስፖርት ክለብ ወስኗል።


ኃይል የተቋረጠው ከማመንጫው ወደ ግሪድ በሚያስገባበት ሥርዓት ላይ ባጋጠመ ችግር ነው - የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል

መጋቢት 19 /2016 (አዲስ ዋልታ) የኃይል መቋረጥ የተፈጠረው ከኃይል ማመንጫዎች የሚመነጨውን ኃይል ወደ ግሪድ የሚያስገባበት ሥርዓት ላይ ባጋጠመ ችግር መሆኑን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ።

የተቋሙ ሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ሞገስ መኮንን ከአዲስ ዋልታ ቴሌቪዥን ጋር ባደረጉት ቆይታ ችግሩ በምን ምክንያት እንደመጣ እስካሁን አለመታወቁን ገልጸዋል።

አሁን ባለው ሁኔታ አዲስ አበባን ጨምሮ በአብዛኛው የሀገሪቱ ክፍል ኃይል መልሶ ማግኘት የሚቻልበት ሁኔታ ተፈጥሯል ነው ያሉት።

በባህርዳር እና አካባቢ ላይ ከበለስ ኃይል ማመንጫ ኃይል ማግኘት የሚችሉበት ሁኔታ በመፈጠሩ እዛ አካባቢ የኃይል መቋረጥ አለመከሰቱን የገለጹት ኃላፊው በሌላው የሀገሪቱ ክፍል የኃይል መቋረጥ ሲያጋጥም ደግሞ መልሶ ኃይል ለማገናኘት ጊዜ ይወስዳል ብለዋል። ይሁን እንጂ በተደረገው ርብርብ ሁለት ሰዓት ባልሞላ ጊዜ መልሶ ማገናኘት መቻሉን አመልክተዋል።

እንደዚህ ዓይነት የኃይል መቆራረጥ ባለፉት ጊዜያት በተደጋጋሚ እንደሚያጋጥም አስታውሰው አሁን ላይ ግን በዓመት ውስጥ አንድ ጊዜ የሚያጋጥምበት ሁኔታ እንዳለ ገልጸዋል።

አሁን ላይ በብዙ አካባቢዎች ማገናኘት ስለተቻለ የቀሩት አካባቢዎች ላይ መልሶ ለማገናኘት ብዙም ጊዜ እንደማይወስድ ጠቁመዋል።

የኤሌክትሪክ ኃይል ዛሬ ከቀኑ 9:46 ጀምሮ ከባህርዳርና አካባቢው በስተቀር በመላው ኢትዮጵያ ተቋርጦ እንደነበር ቀደም ሲል መዘገባችን ይታወቃል።


በመላ ሀገሪቱ ኃይል መቋረጡ ተገለጸ

መጋቢት 19 /2016 (አዲስ ዋልታ) ዛሬ ከቀኑ 9 ሰዓት ከ46 ደቂቃ ጀምሮ ከባህርዳርና አካባቢው በስተቀር በመላው ኢትዮጵያ የኤሌክትሪክ ኃይል ሙሉ በሙሉ መቋረጡን የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ ኃይል አስታወቀ።

በሲስተሙ ላይ በገጠመው ችግር ኃይል የተቋረጠ መሆኑን ያስታወቀው ተቋሙ ለጊዜው የችግሩን ምክንያት ለማወቅ ጥረት እየተደረገ መሆኑን በማኅበራዊ ትስስር ገጹ ላይ ባወጣው መረጃ አመልክቷል።

የተቋረጠውን ኤሌክትሪክ መልሶ የማገናኘት ሥራ የተጀመረ ሲሆን ችግሩን በመቅረፍ ዳግም ሲስተሙን መልሰን እስከምናገናኝ በትዕግስት እንድትጠብቁን በትህትና እንጠይቃለን ብሏል።


“በዛሬው ውይይት ከተለያየ የማኅበረሰብ ዳራ የተውጣጡ ከመላው ኢትዮጵያ የመጡ ሴቶችን ሀሳብ አዳምጫለሁ። በኅብረተሰባችን ውስጥ የሴቶች ሚና ብዙ መልክ እና ብዙ ገፅ ያለው ነው።"- ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)


ቻይናዊው ወጣት በኪሩቤል ግርማ ተይዞ የነበረውን ክብረ ወሰን ሰበረ

መጋቢት 19/2016 (አዲስ ዋልታ) ቻይናዊው ወጣት ውሃን ከአፍ ለረጅም ጊዜ በማንቆርቆር/መርጨት ተግባር በኪሩቤል ግርማ ተይዞ የነበረውን ክብረ ወሰን በሰፊ ልዩነት ሰብሮታል።

ኪሩቤል ግርማ ውሃን ለ56 ሰከንድ ከ36 ማክሮ ሰከንድ ያክል ከአፉ በመርጨት ነበር በዓለም የጊነስ ቡክ መዝገብ ላይ ስሙ የሰፈረው።

የ35 ዓመቱ ቻይናዊ ማ ሁዊ ለ5 ደቂቃ ከ51 ሰከንድ ከ88 ማይክሮ ሰከንድ ያህል ያለማቋረጥ ውሃ ከአፉ በመርጨት ተዓምር አስብሏል። የማ ሁዊ ድርጊት በሰው ልጅ ታሪክ ተወዳዳሪ የሌለው አስብሎታል።

ውሃን ለረጅም ጊዜ በአፍ የመርጨት ተግባር ከ17ኛው ክፍለ ዘመን ጀምሮ የነበረ ጥበብ ሲሆን በብዛት የተጠጣን ውሃ በአፍ በኩል መልሶ በማውጣት ወደ ውጭ የመርጨት ስልት ነው።

ድርጊቱን በማንኛውም ሰው ሊከወን የማይቻል መሆኑ የተገለጸ ሲሆን ከፍተኛ የጡንቻ ቁጥጥርና ምጠና ክህሎት እንደሚያስፈልገው ባለሙያዎች ይናገራሉ።

ቻይናዊው ወጣት ይህን ክብረ ወሰን ለመስበር 4 ሊትር ተኩል ውሃ መጠጣቱን ኦዲቲ ሴንትራል ዘግቧል።


ከተማ አስተዳደሩ በ90 ቀን 108 ቤቶችን ገንብቶ ለአቅመ ደካሞች ለማስረከብ ግንባታ አስጀመረ

መጋቢት 19/2016 (አዲስ ዋልታ) የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በ90 ቀን 108 ቤቶችን ገንብቶ ለአቅመ ደካሞች ለማስረከብ በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ግንባታ አስጀመረ።

የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ አዳነች አቤቤ በክፍለ ክተማ የሚገነባውን 108 ቤቶችን የሚይዝ ባለአምስት ወለል ሦስት የመኖሪያ ቤት ህንፃ ግንባታ የመሰረት ድንጋይ በማስቀመጥ ነው ዛሬ ግንባታውን ያስጀመሩት።

ከተማ አስተዳደሩ በከተማው ያለውን የመኖሪያ ቤት ችግር ለመፍታት ህብረተሰቡን በማህበር በማደራጀት የቤት መስሪያ ቦታ ከመስጠት ጎን ለጎን የአቅመ ደካሞችን የቤት ችግር ለማቃለል እየሰራ መሆኑንም ከንቲባ አዳነች አቤቤ ገልጸዋል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ መኖሪያ ቤት ለሌላቸውና ተከራይተው መኖር ለማይችሉ አቅመ ደካሞች ቤት ገንብቶ ለማስረከብ ግንባታውን አስጀምሯል ብለዋል፡፡

የከተማ አስተዳደሩ የህዝቡን ተስፋ ለማለምለም፣ በኑሮ ውድነትና በቤት እጦት የሚሰቃየውን ህዝብ በምንችለው ለማገዝ ጥረት እያደረግን እንገኛለን ሲሉም አክለዋል፡፡

የጋራ መኖሪያ ቤት በህብረተሰብ ተሳትፎ እና ባለሃብቶች የሚገነባ መሆኑም ተገልጿል።

በግዛቸው ግርማዬ




"ኢፍጣራችን ለአንድነታችን" ታላቅ የጎዳና ላይ ኢፍጣር ስነ ስርዓት - በምስል

📷 ልዑል ማስረሻ
#አዲስ_ዋልታ

ተጨማሪ ምስሎችን ለመመልከት የፌስቡክ ገፃችንን ይቀላቀሉ 👇
https://shorturl.at/fQVX5




የባሕር ዳር ከነማ እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች የነበረው አለልኝ አዘነ በድንገት አረፈ

መጋቢት 18/2016 (አዲስ ዋልታ) የባሕር ዳር ከነማ እና የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ተጫዋች የነበረው አለልኝ አዘነ በድንገት ህይወቱ ማለፉ ተሰምቷል።

ተጫዋቹ በጉዳት ምክንያት ከክለቡ ስብስብ ጋር ያልነበረ ሲሆን በትውልድ ቦታው አርባ ምንጭ ሌሊት በድንገት ማረፉ ተገልጿል።

በቅርቡ የተሞሸረው አለልኝ አዘነ፤ ላለፉት ሁለት አመታት በጣና ሞገዶቹ ቤት ድንቅ ብቃቱን ሲያሳይ ቆይቷል። ከዚህ በተጨማሪም ለኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ጥሪ ተደርጎለት አገልግሎት መስጠቱ ይታወሳል።

ስርዓተ ቀብሩ ዛሬ መጋቢት 18, 2016 በአርባ ምንጭ እንደሚፈፀም ከክለቡ ማህበራዊ ትስስር ገፅ ያገኘነው መረጃ ያመለክታል።

አዲስ ዋልታ ቴሌቪዥን በአለልኝ አዘነ ድንገተኛ ህልፈት የተሰማውን ሀዘን እየገለፀ ለቤተሰቦቹ፣ ለወዳጅ ዘመዶቹና ለመላው የስፖርት ቤተሰብ መፅናናትን ይመኛል።


ንግድ ባንክ ያለአግባብ የተወሰደውን ገንዘብ ያልመለሱ ሰዎችን ስም ዝርዝር ይፋ አደረገ

መጋቢት 17/2016 (አዲስ ዋልታ) የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ መጋቢት 6 ቀን 2016 ዓ.ም ሌሊት ባጋጠመው ችግር ምክንያት ያለአግባብ የተወሰደውን ገንዘብ ያልመለሱ ሰዎችን ስም ዝርዝር ይፋ አደረገ።

ባንኩ ይፋ ያደረገውን የስም ዝርዝሩን ለማየት የሚከተለውን ማስፈንጠሪያ ይጠቀሙ👇
https://shorturl.at/ftBG0


እንግሊዝ ከቤልጂየም እና ጀርመን ከሆላንድ የወዳጅነት ጨዋታ ያካሂዳሉ

መጋቢት 17/2016 (አዲስ ዋልታ) ዛሬ ምሽት 4 ሰዓት ከ45 ላይ እንግሊዝ ከቤልጂየም እንዲሁም ጀርመን ከሆላንድ የወዳጅነት ጨዋታ ያደርጋሉ።

እንግሊዝ ባለፈው ቅዳሜ በብራዚል 1 ለ 0 የተሸነፈች ሲሆን ቤልጂየም በበኩሏ ከአየርላንድ ጋር 0 ለ 0 መለያዬታቸው ይታወሳል።

ጀርመን በበኩሏ ቅዳሜ ዕለት ከፈረንሳይ ጋር ያደረገችውን ጨዋታ 2 ለ 0 ስታሸንፍ፣ ሆላንድ ስኮትላንድን 4 ለ 0 በሆነ ሰፊ ውጤት አሸንፋለች።

ከሁለቱ የወዳጅነት ጨዋታዎች በተጨማሪ ሌሎች በርካታ ጨዋታዎች የሚካሄዱ ሲሆን ስሎቬንያ ከፖርቱጋል፣ ኡራጓይ ከአይቮሪ ኮስት፣ ሮማንያ ከኮሎምቢያ፣ አየርላንድ ከሲውዘርላንድ ምሽት 4 ከ 45 ላይ ከሚካሄዱ ግጥሚያዎች ተጠቃሽ ናቸው።

ምሽት 5 ሰዓት ላይ ግብፅ በሜዳዋ ክሮሺያን እንደምታስተናግድ ሲጠበቅ ፈረንሳይ ከቺሊ እንዲሁም ስፔን ጀብራዚል 5 ሰዓት 30 ላይ የሚደርጉት ተጠባቂ ጨዋታዎች ናቸው


የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዟችንን ከጀመርንበት ጊዜ ጀምሮ እንደ ሀገር ወሳኝ ርምጃዎችን ተራምደናል - ጠ/ሚ ዐቢይ አሕመድ

መጋቢት 17/2016 (አዲስ ዋልታ) የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ጉዟችንን ከጀመርንበት ጊዜ ጀምሮ እንደ ሀገር ወሳኝ ርምጃዎችን ተራምደናል ሲሉ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ገለጹ።

ጠቅላይ ሚኒስትሩ "ዲጂታል ኢትዮጵያ 2025" ለፈጠራ ሰዎች ድጋፍ በማስገኘት እና ለዲጂታል ጉዞ አስቻይ ሁኔታዎችን በመፍጠር በዲጂታል ኢኮኖሚ እንድንበረታ ዐቅም ሆኖናል ሲሉም በማኅበራዊ ትስስር ገጻቸው አስፍረዋል።

“ዛሬ ያደረግነው የመካከለኛ ዘመን ግምገማ ተግዳሮቶቻችንን ለመፈተሽ ብሎም የጉዟችንን ስኬታማ እጥፋቶች ለማክበር ዕድል ፈጥሮልናል።” ብለዋል።


ሚዛን አማን

#ከተሞቻችን

የሚዛን አማን ከተማ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል አንዷ መቀመጫና የቤንች ሸኮ ዞን ዋና መቀመጫ ሆና በማገልገል ላይ ትገኛለች፡፡

ከተማዋ ከርዕሠ መድናችን አዲስ አበባ በ568 ኪሎ ሜትር ርቀት ላይ የምትገኝ ስትሆን በ1930 ዓ.ም እንደተቆረቆረች ይነገራል።

ሚዛን አማን ከተማ የቀድሞ ሚዛን ተፈሪ የሚለውን ስያሜ ያገኘችው በንጉሱ አፄ ኃይሌ ስላሴ ዘመነ መንግሥት አካባቢውን እንዲያስተዳድሩ ተሹመው በተላኩት በእንደራሴው ፊታውራሪ አለማየሁ ፍላቴ መሆኑ ይነገራል፡፡

የንጉስ አፄ ኃይሌ ስላሴ ልደት እየተከበረ በነበረበት ወቅት ከተማዋ በመመስረቷ የልደት መታሰቢያ ለማድረግ እንደሆነም ታሪክ ይጠቅሳል።

በ1ሺሕ 451 ሜትር ከባህር ጠለል በላይ ከፍታ ላይ የምትገኘው ሚዛን አማን በአረንጓዴ መልክዓ ምድር የተሸፈነች እና ወይናደጋ የአየር ንብረት ያላት ከተማ ነች።

እምቅ የተፈጥሮ ሀብት ያላት ሚዛን አማን በዙሪያዋ ከፍተኛ የደን ክምችት ያላት ሲሆን ቡናን ጨምሮ፣ በፍራፍሬ እና በቅመማቅመም ምርቶች ትታወቃለች፡፡ የአረንጓዴ ልማት ፈርጥ ተብላም ትጠራለች።
https://www.facebook.com/wmccwaltamediaandcommunicationcorporate/posts/pfbid0NMmjbVppnwZjZ9NxBEeKkDnjSQ26t2A9oaG6xmD6MCFc7FEwdAG1pXAJxreKrLnJl


ገንዘቡን ከወሰዱት ግለሰቦች መካከል 560 ሰዎች አልተገኙም

ከዛሬ ጀምሮም ማንነታቸው በባንኩ ማህበራዊ ትስስር ገፅ ይለቀቃል ተብሏል

ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በተያያዘ ከ9 ሺሕ በላይ የሚሆኑ ግለሰቦች በፈቃደኝነት ገንዘቡን መመለሳቸው ተገለፀ

መጋቢት 17/2016 (አዲስ ዋልታ) ከኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ጋር በተያያዘ 9 ሺሕ 200 ያህሉ ግለሰቦች በፈቃደኝነት ገንዘቡን መመለሳቸው ተገለፀ፡፡

ባንኩ ካጋጠመው ችግር ጋር ተያይዞ የተከናወኑ ዐበይት ተግባራትን ለመገናኛ ብዙሀን መግለጫ ሰጥቷል።

የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ፕሬዘደንት አቤ ሳኖ በመግለጫቸው ባንኩ ባጋጠመው ችግር ምክንያት 801 ሚሊየን ብር ያለአግባብ ተወስዶ እንደነበር ገልፀዋል።

ነገር ግን በጉዳዩ ላይ ተሳትፎ ከነበራቸው ውስጥ 9 ሺሕ 200 ያህሉ በፈቃደኝነት የወሰዱትን ገንዘብ መልሰዋል ሲሉ ፕሬዝዳንቱ አስታውቀዋል፡፡ በዚህም 223 ሚሊየን 475 ሺህ 369 ብር ተመላሽ መደረጉን አንስተዋል።

ከዚህ ባሻገር 5 ሺሕ 160 ያህል ግለሰቦች ደግሞ በፈቃደኝነት የወሰዱትን 148 ሚሊየን 21 ሺሕ 191 ብር በከፊል መመለሳቸውን አክለዋል፡፡

እንደ አጠቃላይ ባንኩ በአጠቃላይ ወጪ ከተደረገው ገንዘብ 78 በመቶ ያህሉን ገንዘብ ተመላሽ ማድረጉም ተገልጿል፡፡

ባንኩ ገንዘብ ወስደው ያልመለሱ ደንበኞች ከዛሬ ጀምሮ በኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የማህበራዊ ድረገፅ ስማቸው እንደሚለጠፍም የባንኩ ፕሬዝዳንት ገልፀዋል።

በዙፋን አምባቸው


በ13ኛው የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች የተሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑክ አዲስ አበባ ገባ

መጋቢት 16/2016 (አዲስ ዋልታ) በጋና በተካሄደው 13ኛው የመላ አፍሪካ ጨዋታዎች የተሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑክ ዛሬ ማምሻውን አዲስ አበባ ገባ።

ልዑኩ ቦሌ ዓለም አቀፍ አየር ማረፊያ ሲደርስ የባህልና ስፖርት ሚኒስትር ዴዔታ አምባሳደር መስፍን ቸርነት እና የኢትዮጵያ አትሌቲክስ ፌዴሬሽን ፕሬዝዳንት ረዳት ኮሚሽነር ደራርቱ ቱሉ አቀባበል አድርገውለታል።

የአፍሪካ ጨዋታዎች ከየካቲት 29 እስከ መጋቢት 14 ቀን 2016 ዓ.ም በጋና አክራ የተካሄደ ሲሆን በውድድሩ ከ53 ሀገራት የተወጣጡ ከ5 ሺሕ በላይ ስፖርተኞች በ29 የስፖርት አይነቶች ተሳትፈዋል።

ኢትዮጵያም በ165 ስፖርተኞች በአምስት የኦሊምፒክ ውድድሮችና አራቱ ኦሊምፒክ ያልሆኑ ስፖርቶች በድምሩ በዘጠኝ የስፖርት አይነቶች ተሳትፋለች፡፡

በአትሌቲክስ፣ እግር ኳስ፣ ውሃ ዋና፣ የጠረጴዛና ሜዳ ቴኒስ፣ ቦክስ፣ ቅርጫት ኳስ፣ ብስክሌትና ወርልድ ቴኳንዶ ኢትዮጵያ የተሳተፈችባቸው የውድድር አይነቶች ናቸው።

ኢትዮጵያ 9 የወርቅ፣ 8 የብር፣ 5 የነሐስ በአጠቃላይ 22 ሜዳሊያዎችን በማግኘት በሁሉም የስፖርት አይነቶች ስምንተኛ ደረጃን ይዛ አጠናቅቃለች።

በ13ኛው የአፍሪካ ጨዋታዎች ለተሳተፈው የኢትዮጵያ ልዑካን ቡድን የእውቅናና የሽልማት መርኃ ግብር እንደሚካሄድም ኢዜአ ዘግቧል፡፡

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.