ሞኖጌኔስ
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
3፥47 ፡-"ጌታዬ ሆይ! ሰው ያልነካኝ ስኾን ለኔ እንዴት ልጅ ይኖረኛል? አለች፡፡ ነገሩ እንዳልሽው ነው፡፡ አሏህ የሚሻውን ይፈጥራል፡፡ አንዳችን በሻ ጊዜ ለእርሱ ኹን ይለዋል፤ ወዲውኑም ይኾናል" አላት፡፡ قَالَتْ رَبِّ أَنَّىٰ يَكُونُ لِي وَلَدٌ وَلَمْ يَمْسَسْنِي بَشَرٌ ۖ قَالَ كَذَٰلِكِ اللَّهُ يَخْلُقُ مَا يَشَاءُ ۚ إِذَا قَضَىٰ أَمْرًا فَإِنَّمَا يَقُولُ لَهُ كُن فَيَكُونُ
"ዘ" ማለት በግዕዝ "የ" ማለት ሲሆን "ዘ-"ፍጥረት" ማለት "የ-ፍጥረት" እንዲሁ "ዘ-"ልደት" ማለት "የ-ልደት" ማለት ነው። ኦሪት ዘፍጥረት በግዕዙ "ዘልደት" ሲባል፣ በእንግሊዝኛ "Genesis" ሲባል፣ በግሪክ ሰፕቱአጀንት "ጌነሲስ" Γένεσις ይባላል፥ ትርጉሙ "ልደት" ማለት ነው። ሰማይ እና ምድር ደግሞ የተፈጠሩ እንጂ በእማሬአዊ የተወለዱ አይደሉም፥ ልደቱ በፍካሬአዊ ፍጥረቱን የሚያሳይ ነው፦
ዘፍጥረት 2፥4 የሰማይ እና የምድር "ልደት" መጽሐፍ ይህ ነው። Αὕτη ἡ βίβλος γενέσεως οὐρανοῦ καὶ γῆς,
"ጌኔሲስ" γένεσις የሚለው ቃል "ጊኖማይ" γίνομαι ማለትም "የሆነ" ማለት ሲሆን "ልደት" ማለት ነው። ኢየሱስ "ልደት" ያለው ፍጡር ሲሆን ይህ ልደቱ እናቱ ማርያም ማኅፀን ውስጥ ከመንፈስ ቅዱስ መፀነሱ ነው፦
ማቴዎስ 1፥18 የኢየሱስ ክርስቶስም ልደት እንዲህ ነበረ። እናቱ ማርያም ለዮሴፍ በታጨች ጊዜ ሳይገናኙ ከመንፈስ ቅዱስ ፀንሳ ተገኘች። Τοῦ δὲ Ἰησοῦ Χριστοῦ ἡ γένεσις οὕτως ἦν. μνηστευθείσης τῆς μητρὸς αὐτοῦ Μαρίας τῷ Ἰωσήφ, πρὶν ἢ συνελθεῖν αὐτοὺς εὑρέθη ἐν γαστρὶ ἔχουσα ἐκ πνεύματος ἁγίου.
በተመሳሳይ እዚህ አንቀጽ ላይ "ልደት" ለሚለው የገባው ቃል "ጌኔሲስ" γένεσις ሲሆን ሥርወ ቃሉ "ጊኖማይ" γίνομαι ማለትም "የሆነ" ማለት ነው፥ ኢየሱስ ያለ ወንድ ዘር ከማርያም የማኅፀን ፍሬ "የሆነ" ተአምር ነው፦
ማቴዎስ 1፥20 ከእርስዋ የተፀነሰው ከመንፈስ ቅዱስ ነውና። τὸ γὰρ ἐν αὐτῇ γεννηθὲν ἐκ Πνεύματός ἐστιν Ἁγίου·
"የተፀነሰው" ለሚለው የገባው ቃል "ጌኔቴን" γεννηθὲν ሲሆን ሥርወ ቃሉ "ጌናኦ" γεννάω ነው፥ የቀጥታ ትርጉም የሚባሉት "Literal Standard Version" እና "Young's Literal Translation" በግልጽ "begotten" ብለው አስቀምጠውታል። "የተወለደው" ከመንፈስ ቅዱስ አሠራር ስለሆነ አምላክ ያ የተወለደውን ሰው "ወልጄሃለሁ" ብሎታል፦
ዕብራውያን 1፥5 እኔ ዛሬ "ወልጄሃለሁ"። ἐγὼ σήμερον γεγέννηκά σε;
እዚህ አንቀጽ ላይ "ወልጄሃለሁ" ለሚለው የገባው የግሥ መደብ "ጌኔካ" γεγέννηκά ሲሆን ሥርወ ቃሉ በተመሳሳይ "ጌናኦ" γεννάω ነው፦
"ጌታም አለኝ፦ "አንተ ልጄ ነህ፥ እኔ ዛሬ ወለድሁ" መዝሙር 2፥7 ምንም እንኳን ያ ቀን በትንቢት የተነገረ ቢመስልም ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ እንደ ተወለደ በእርሱም ይነገር ዘንድ ነው"።
Expositions on the Psalms (Augustine) Psalm Chapter 2 Number 7
"እኔ ዛሬ ወለድሁ" የሚለው እምቅድመ ዓለም ሳይሆን ከድንግል መፈጠሩን ካሳየ ዘንዳ አምላክ "አባት" ሰው "ልጅ" የተባለበት ከዚህ አንጻር ነው፦
ዕብራውያን 1፥5 እኔ አባት እሆነዋለሁ፥ እርሱም ልጅ ይሆነኛል። καὶ πάλιν Ἐγὼ ἔσομαι αὐτῷ εἰς Πατέρα, καὶ αὐτὸς ἔσται μοι εἰς Υἱόν;
"ፓቴራ" Πατέρα ማለት "አባት" ማለት ሲሆን "ሁዮን" Υἱόν ማለት "ልጅ" ማለት ነው፥ በግዕዝ አባት "አብ" ሲባል ልጅ "ወልድ" ይባላል። አምላክ አባት የሚሆነው ከዳዊት ወገብ ለሚወጣ ዘር እንጂ ለመለኮት በፍጹም አይደለም፦
2ኛ ሳሙኤል 7፥12 ከወገብህ የሚወጣውን ዘርህን ከአንተ በኋላ አስነሣለሁ፥
2ኛ ሳሙኤል 7፥14 እኔም አባት እሆነዋለሁ፥ እርሱም ልጅ ይሆነኛል።
በአሏህ ስም እጅግ በጣም ሩኅሩህ እጅግ በጣም አዛኝ በሆነው።
3፥47 ፡-"ጌታዬ ሆይ! ሰው ያልነካኝ ስኾን ለኔ እንዴት ልጅ ይኖረኛል? አለች፡፡ ነገሩ እንዳልሽው ነው፡፡ አሏህ የሚሻውን ይፈጥራል፡፡ አንዳችን በሻ ጊዜ ለእርሱ ኹን ይለዋል፤ ወዲውኑም ይኾናል" አላት፡፡ قَالَتْ رَبِّ أَنَّىٰ يَكُونُ لِي وَلَدٌ وَلَمْ يَمْسَسْنِي بَشَرٌ ۖ قَالَ كَذَٰلِكِ اللَّهُ يَخْلُقُ مَا يَشَاءُ ۚ إِذَا قَضَىٰ أَمْرًا فَإِنَّمَا يَقُولُ لَهُ كُن فَيَكُونُ
"ዘ" ማለት በግዕዝ "የ" ማለት ሲሆን "ዘ-"ፍጥረት" ማለት "የ-ፍጥረት" እንዲሁ "ዘ-"ልደት" ማለት "የ-ልደት" ማለት ነው። ኦሪት ዘፍጥረት በግዕዙ "ዘልደት" ሲባል፣ በእንግሊዝኛ "Genesis" ሲባል፣ በግሪክ ሰፕቱአጀንት "ጌነሲስ" Γένεσις ይባላል፥ ትርጉሙ "ልደት" ማለት ነው። ሰማይ እና ምድር ደግሞ የተፈጠሩ እንጂ በእማሬአዊ የተወለዱ አይደሉም፥ ልደቱ በፍካሬአዊ ፍጥረቱን የሚያሳይ ነው፦
ዘፍጥረት 2፥4 የሰማይ እና የምድር "ልደት" መጽሐፍ ይህ ነው። Αὕτη ἡ βίβλος γενέσεως οὐρανοῦ καὶ γῆς,
"ጌኔሲስ" γένεσις የሚለው ቃል "ጊኖማይ" γίνομαι ማለትም "የሆነ" ማለት ሲሆን "ልደት" ማለት ነው። ኢየሱስ "ልደት" ያለው ፍጡር ሲሆን ይህ ልደቱ እናቱ ማርያም ማኅፀን ውስጥ ከመንፈስ ቅዱስ መፀነሱ ነው፦
ማቴዎስ 1፥18 የኢየሱስ ክርስቶስም ልደት እንዲህ ነበረ። እናቱ ማርያም ለዮሴፍ በታጨች ጊዜ ሳይገናኙ ከመንፈስ ቅዱስ ፀንሳ ተገኘች። Τοῦ δὲ Ἰησοῦ Χριστοῦ ἡ γένεσις οὕτως ἦν. μνηστευθείσης τῆς μητρὸς αὐτοῦ Μαρίας τῷ Ἰωσήφ, πρὶν ἢ συνελθεῖν αὐτοὺς εὑρέθη ἐν γαστρὶ ἔχουσα ἐκ πνεύματος ἁγίου.
በተመሳሳይ እዚህ አንቀጽ ላይ "ልደት" ለሚለው የገባው ቃል "ጌኔሲስ" γένεσις ሲሆን ሥርወ ቃሉ "ጊኖማይ" γίνομαι ማለትም "የሆነ" ማለት ነው፥ ኢየሱስ ያለ ወንድ ዘር ከማርያም የማኅፀን ፍሬ "የሆነ" ተአምር ነው፦
ማቴዎስ 1፥20 ከእርስዋ የተፀነሰው ከመንፈስ ቅዱስ ነውና። τὸ γὰρ ἐν αὐτῇ γεννηθὲν ἐκ Πνεύματός ἐστιν Ἁγίου·
"የተፀነሰው" ለሚለው የገባው ቃል "ጌኔቴን" γεννηθὲν ሲሆን ሥርወ ቃሉ "ጌናኦ" γεννάω ነው፥ የቀጥታ ትርጉም የሚባሉት "Literal Standard Version" እና "Young's Literal Translation" በግልጽ "begotten" ብለው አስቀምጠውታል። "የተወለደው" ከመንፈስ ቅዱስ አሠራር ስለሆነ አምላክ ያ የተወለደውን ሰው "ወልጄሃለሁ" ብሎታል፦
ዕብራውያን 1፥5 እኔ ዛሬ "ወልጄሃለሁ"። ἐγὼ σήμερον γεγέννηκά σε;
እዚህ አንቀጽ ላይ "ወልጄሃለሁ" ለሚለው የገባው የግሥ መደብ "ጌኔካ" γεγέννηκά ሲሆን ሥርወ ቃሉ በተመሳሳይ "ጌናኦ" γεννάω ነው፦
"ጌታም አለኝ፦ "አንተ ልጄ ነህ፥ እኔ ዛሬ ወለድሁ" መዝሙር 2፥7 ምንም እንኳን ያ ቀን በትንቢት የተነገረ ቢመስልም ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋ እንደ ተወለደ በእርሱም ይነገር ዘንድ ነው"።
Expositions on the Psalms (Augustine) Psalm Chapter 2 Number 7
"እኔ ዛሬ ወለድሁ" የሚለው እምቅድመ ዓለም ሳይሆን ከድንግል መፈጠሩን ካሳየ ዘንዳ አምላክ "አባት" ሰው "ልጅ" የተባለበት ከዚህ አንጻር ነው፦
ዕብራውያን 1፥5 እኔ አባት እሆነዋለሁ፥ እርሱም ልጅ ይሆነኛል። καὶ πάλιν Ἐγὼ ἔσομαι αὐτῷ εἰς Πατέρα, καὶ αὐτὸς ἔσται μοι εἰς Υἱόν;
"ፓቴራ" Πατέρα ማለት "አባት" ማለት ሲሆን "ሁዮን" Υἱόν ማለት "ልጅ" ማለት ነው፥ በግዕዝ አባት "አብ" ሲባል ልጅ "ወልድ" ይባላል። አምላክ አባት የሚሆነው ከዳዊት ወገብ ለሚወጣ ዘር እንጂ ለመለኮት በፍጹም አይደለም፦
2ኛ ሳሙኤል 7፥12 ከወገብህ የሚወጣውን ዘርህን ከአንተ በኋላ አስነሣለሁ፥
2ኛ ሳሙኤል 7፥14 እኔም አባት እሆነዋለሁ፥ እርሱም ልጅ ይሆነኛል።