አንድ የቤት ግንበኛ ሰዉዬ ነበር አሉ ሚስቱ መንታ አረገዘችለትና ደስ አለው ነገር ግን ልጆቹን ለማኖር ሌላ ስራ መፈለግ ነበረበትና አሰሪው ጋር ሄዶ እንዲ ይለዋል
"ሚስቴ መንታ ልጆች ስላረገዘች ልጆቼን ለማኖር ስራ ፍለጋ ወደ ሌላ ሀገር መሄድ ይኖርበኛል አለው
ግን አለቃው እሺ አንድ ነገር ብቻ ላስችግርህ አንድ ቤት ብቻ ስራልኝ እባክህ ይለዋል እሱም እሺ አለና አንደ ነገሩ እንደ ነገሩ አድርጎ ሰርቶ ሲያስረክበው አለቃው ይሄን እንደ ስጦታ ልሰጥህ ነው ያሰራሁ እንካ አለው ቁልፉን
ሰዉየውም ይሄን ባውቅ ኖሮማ እንደ ነገሩ እንደ ነገሩ አድርጌ ባልሰራው ነበር አለ ይባላል
ሕይወት ብዙ ግዜ የሚሰጣቹ እንደ ነገሩ እንደ ነገሩ አድርጋቹ የሰራቹትን ነው
ደና ዋሉ ✌️