Abrham2319 dan repost
#ዕረቡ
በማቴዎስና በማርቆስ ወንጌል መሠረት በዚህ እለት ሦስት ነገሮች ተደርገዋል።
1. የካህናት አለቆች ጸሀፍትና ፈሪሳውያን በጌታ ላይ ተማክረዋል ሊያስገድሉትም ወስነዋ።
2. ጌታችን በስምኦን ዘለምጽ ቤት ተገኝቶ አንዲት ሴት(ማርያም እንተ ዕፍረት) ዋጋው የከበረ የአልባስጥሮስ ሽቱ ቀብታዋለች።
3. ይሁዳ ጌታን ለመሸጥ ወደ ጸሀፍት ካህናት ጋር በመሄድ ተዋውሏል።
በአይሁድ ዘንድ 72 አባላት የነበሩት ሸንጎ ነበር። "ሲናድርየም " ይባላል።አብዛኛዎቹ ሰዱቃውያን ሲሆኑ ጥቂቶቹ ጸሀፎችና ፈሪሳውያን ነበሩ። የተሰበሰቡትና ጌታን እንዴት እንደሚይዙት የተማከሩት በካህናቱ አለቃ በቀያፋ ግቢ ነበር።
በዚ ጊዜ ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ የነበረው ያስቆሮቱ ይሁዳ ወደ ስብሰባው በመሄድ "ምን ትሰጡኛላችሁ እኔ አሳልፌ እሰጣችኋለሁ" በማለት ጌታን ለመሸጥ ተዋዋለ።ይህን ያደረገው በስምኦን ዘለምጽ ቤት እያሉ አንዲት ሴት ጌታን የከበረ ሽቱ ስትቀባው ለድሀ አዛኝ በመምሰል "ይህ ሽቱ ተሽጦ ለድሆች ቢሰጥ መልካም ነበር "ሲል ጌታ የልቡን መሻት አውቆ ስለተቃወመው አኩርፎ ሄዶ ተዋውሎ በ30 ብር የተስማማ። ከዛም ሊያስገድሉት ወስነዋል። እንዲሁም ሐሙስ በአል ስለነበር በአሉን አክብረው ውለው ማታ ላይ አስይዘው አርብ ጠዋት ሸንጎ ሊያቆሙት ተስማምተው ተለያዩ (ማቴ 26÷3.. ማር 14÷1-11 ሉቃ 22÷1-6)
በዚህ እለት በቤተክርስቲያን የሚሰበከው ምስባክ
- አንድ ሰአት መዝ 83÷5
- ሦስት ሰአት መዝ 41÷6
- ስድስት ሰአት መዝ 41÷5
- ዘጠኝ ሰአት መዝ 83÷2
- አስራ አንድ ሰአት መዝ 6÷2
@abrham2319
በማቴዎስና በማርቆስ ወንጌል መሠረት በዚህ እለት ሦስት ነገሮች ተደርገዋል።
1. የካህናት አለቆች ጸሀፍትና ፈሪሳውያን በጌታ ላይ ተማክረዋል ሊያስገድሉትም ወስነዋ።
2. ጌታችን በስምኦን ዘለምጽ ቤት ተገኝቶ አንዲት ሴት(ማርያም እንተ ዕፍረት) ዋጋው የከበረ የአልባስጥሮስ ሽቱ ቀብታዋለች።
3. ይሁዳ ጌታን ለመሸጥ ወደ ጸሀፍት ካህናት ጋር በመሄድ ተዋውሏል።
በአይሁድ ዘንድ 72 አባላት የነበሩት ሸንጎ ነበር። "ሲናድርየም " ይባላል።አብዛኛዎቹ ሰዱቃውያን ሲሆኑ ጥቂቶቹ ጸሀፎችና ፈሪሳውያን ነበሩ። የተሰበሰቡትና ጌታን እንዴት እንደሚይዙት የተማከሩት በካህናቱ አለቃ በቀያፋ ግቢ ነበር።
በዚ ጊዜ ከ12ቱ ሐዋርያት አንዱ የነበረው ያስቆሮቱ ይሁዳ ወደ ስብሰባው በመሄድ "ምን ትሰጡኛላችሁ እኔ አሳልፌ እሰጣችኋለሁ" በማለት ጌታን ለመሸጥ ተዋዋለ።ይህን ያደረገው በስምኦን ዘለምጽ ቤት እያሉ አንዲት ሴት ጌታን የከበረ ሽቱ ስትቀባው ለድሀ አዛኝ በመምሰል "ይህ ሽቱ ተሽጦ ለድሆች ቢሰጥ መልካም ነበር "ሲል ጌታ የልቡን መሻት አውቆ ስለተቃወመው አኩርፎ ሄዶ ተዋውሎ በ30 ብር የተስማማ። ከዛም ሊያስገድሉት ወስነዋል። እንዲሁም ሐሙስ በአል ስለነበር በአሉን አክብረው ውለው ማታ ላይ አስይዘው አርብ ጠዋት ሸንጎ ሊያቆሙት ተስማምተው ተለያዩ (ማቴ 26÷3.. ማር 14÷1-11 ሉቃ 22÷1-6)
በዚህ እለት በቤተክርስቲያን የሚሰበከው ምስባክ
- አንድ ሰአት መዝ 83÷5
- ሦስት ሰአት መዝ 41÷6
- ስድስት ሰአት መዝ 41÷5
- ዘጠኝ ሰአት መዝ 83÷2
- አስራ አንድ ሰአት መዝ 6÷2
@abrham2319