“የፓርቲውን አባላት እና አመራሮች በማስፈራራትና በማሰር ትግሉን ማስቆም አይቻልም”- ኢሕአፓ
ጥር 2 ቀን 2017 (አዲስ ማለዳ) የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ ባወጣው መገለጫ በሐረር ክልል የሚገኙት አባሎቻቸው እና አመራሮች ያለ በቂ ምክንያት በጸጥታ ሀይሎች መወሰዳቸውን አስታውቋል፡፡
በዚህም በክልሉ የሚገኘውን ኢሕአፓ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አመራር የጸጥታ ሀይሎች ከመኖሪያ ቤታቸው ወስደው እንዳሰሯቸው እና ወደ ፍርድ ቤትም እንዳላቀረቧቸው ገልጿል፡፡
እንዲሁም እንደታሠሩ ለመጀመሪያዎቹ ሁለት ቀናት መጠየቅ ይቻል የነበረ ቢሆንም ከጥቂት ቀናት በፊት ግን ከነበሩበት ፖሊስ ጣቢያ አውጥተው ወዴት እንደወሰዷቸው አልታወቀም ተብሏል፡፡
በመሆኑም ሕገ መንግሥትን ማስከበር በሁሉም እርከን ላይ ከሚገኙ የመንግሥት ባለሥልጣኖች የሚጠበቅ ግዴታ ቢሆንም የብልጽግናው መንግሥት አገልጋዮች ሕጉን አላግባብ መጠቀማቸው እና ከስርዓት ውጪ መሆናቸው አሳፋሪ ነው ሲል ፓርቲው ኮንኗል፡፡
በተጨማሪም አባላቶቹ በአስቸኳይ እንዲለቀቁ እና በፓርቲው አባሎች ላይ የሚደረገው ማስፈራራት፣ ማፈንና ማሰር በአስቸኳይ እንዲቆም አሳስቧል፡፡
ጥር 2 ቀን 2017 (አዲስ ማለዳ) የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አብዮታዊ ፓርቲ ባወጣው መገለጫ በሐረር ክልል የሚገኙት አባሎቻቸው እና አመራሮች ያለ በቂ ምክንያት በጸጥታ ሀይሎች መወሰዳቸውን አስታውቋል፡፡
በዚህም በክልሉ የሚገኘውን ኢሕአፓ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት አመራር የጸጥታ ሀይሎች ከመኖሪያ ቤታቸው ወስደው እንዳሰሯቸው እና ወደ ፍርድ ቤትም እንዳላቀረቧቸው ገልጿል፡፡
እንዲሁም እንደታሠሩ ለመጀመሪያዎቹ ሁለት ቀናት መጠየቅ ይቻል የነበረ ቢሆንም ከጥቂት ቀናት በፊት ግን ከነበሩበት ፖሊስ ጣቢያ አውጥተው ወዴት እንደወሰዷቸው አልታወቀም ተብሏል፡፡
በመሆኑም ሕገ መንግሥትን ማስከበር በሁሉም እርከን ላይ ከሚገኙ የመንግሥት ባለሥልጣኖች የሚጠበቅ ግዴታ ቢሆንም የብልጽግናው መንግሥት አገልጋዮች ሕጉን አላግባብ መጠቀማቸው እና ከስርዓት ውጪ መሆናቸው አሳፋሪ ነው ሲል ፓርቲው ኮንኗል፡፡
በተጨማሪም አባላቶቹ በአስቸኳይ እንዲለቀቁ እና በፓርቲው አባሎች ላይ የሚደረገው ማስፈራራት፣ ማፈንና ማሰር በአስቸኳይ እንዲቆም አሳስቧል፡፡