“የማዳበሪያ አቅርቦት ከገበሬው የመሬት ዝግጅት አንጻር አይመጣጠንም ”- የፓርላማ አባላት
ሰኞ ጥር 19 ቀን 2017(አዲስ ማለዳ)በተለያዩ ክልሎች የአፈር እና የማዳበሪያ አቅርቦት ከገበሬው የመሬት ዝግጅት አንጻር እንደማይመጣጠንና በገበሬው ዘንድ በተደጋጋሚ የሚነሳ ጥያቄ መሆኑ መንግስት ምን አይነት የመፍትሄ ሀሳብ እንዳለው የምክር ቤት አባል ወርቅነሽ መሀመድ ጠይቀዋል፡፡
ይህም የተጠየቀው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 1ኛ ልዩ ስብሰባ እየተካሄደ ባለበት ወቅት ነው፡፡
በተመሳሳይ ጥያቄ ያቀረቡት ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ስንዴ አምራች ገበሬዎች ምርቶቻቸውን በመንግስት የዋጋ ተመን እንዲሸጡ የሚገደዱበት አግባብ ምክንያቱ ምን እንደሆነ እና በነጻ ገበያ እንዳይገበያዩ መሆኑ በውድ ዋጋ ማዳበሪያ እየገዛ የሚያመርተውን ገበሬ የሚያሳድርበትን ጫና የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንዴት እንደሚመለከተው ጠይቀል፡፡
በተጨማሪም የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ከዘመቻ ነት ወጥቶ ወደ ተቋማዊ የችግኝ ማልማት እና የተራቆቱ አካባቢዎችን የማልማት ስራ የሚካሄድበትን ጊዜ እንዲገለጽ አመላክተዋል፡፡
በአባላቱ ለተነሱ ሀሳብ እና ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት የግብርና ሚኒስቴር ሚንስትር ግርማ አመንቴ 5.7 ሚሊዮን ማዳበሪያ ለመስኖ ወቅት እንደተዘጋጀ እና ስርጭቱ ላይ መስተጓጎሎች እንዳይኖሩም የመቆጣጠር ስራ እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡
በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚታረሰው መሬት 43 ከመቶ የሚሆነው በአሲዳማ አፈር የተጠቃ መሆኑን እና 7 ሚሊዮን ሄክታር የሚሆነው የአሲዳማ አፈር መሆኑን ሚኒስትሩ አስታውቀዋል፡፡
እንዲሁም መሬቱን ለግብርና ስራ ለማዋል በዓመት 6.2 ሚልየን ኩንታል ማዳበሪያ ጥቅም ላይ የሚውል ሲሆን 70 ከመቶ የሚሆነው የአፈር ማዳበሪያ ይባክናል ተብሏል።
ሰኞ ጥር 19 ቀን 2017(አዲስ ማለዳ)በተለያዩ ክልሎች የአፈር እና የማዳበሪያ አቅርቦት ከገበሬው የመሬት ዝግጅት አንጻር እንደማይመጣጠንና በገበሬው ዘንድ በተደጋጋሚ የሚነሳ ጥያቄ መሆኑ መንግስት ምን አይነት የመፍትሄ ሀሳብ እንዳለው የምክር ቤት አባል ወርቅነሽ መሀመድ ጠይቀዋል፡፡
ይህም የተጠየቀው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 6ኛው የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት 4ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 1ኛ ልዩ ስብሰባ እየተካሄደ ባለበት ወቅት ነው፡፡
በተመሳሳይ ጥያቄ ያቀረቡት ዶ/ር ደሳለኝ ጫኔ ስንዴ አምራች ገበሬዎች ምርቶቻቸውን በመንግስት የዋጋ ተመን እንዲሸጡ የሚገደዱበት አግባብ ምክንያቱ ምን እንደሆነ እና በነጻ ገበያ እንዳይገበያዩ መሆኑ በውድ ዋጋ ማዳበሪያ እየገዛ የሚያመርተውን ገበሬ የሚያሳድርበትን ጫና የሚኒስቴር መስሪያ ቤቱ እንዴት እንደሚመለከተው ጠይቀል፡፡
በተጨማሪም የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ ከዘመቻ ነት ወጥቶ ወደ ተቋማዊ የችግኝ ማልማት እና የተራቆቱ አካባቢዎችን የማልማት ስራ የሚካሄድበትን ጊዜ እንዲገለጽ አመላክተዋል፡፡
በአባላቱ ለተነሱ ሀሳብ እና ጥያቄዎች ምላሽ የሰጡት የግብርና ሚኒስቴር ሚንስትር ግርማ አመንቴ 5.7 ሚሊዮን ማዳበሪያ ለመስኖ ወቅት እንደተዘጋጀ እና ስርጭቱ ላይ መስተጓጎሎች እንዳይኖሩም የመቆጣጠር ስራ እንደሚሰራ ገልጸዋል፡፡
በሌላ በኩል ኢትዮጵያ ውስጥ ከሚታረሰው መሬት 43 ከመቶ የሚሆነው በአሲዳማ አፈር የተጠቃ መሆኑን እና 7 ሚሊዮን ሄክታር የሚሆነው የአሲዳማ አፈር መሆኑን ሚኒስትሩ አስታውቀዋል፡፡
እንዲሁም መሬቱን ለግብርና ስራ ለማዋል በዓመት 6.2 ሚልየን ኩንታል ማዳበሪያ ጥቅም ላይ የሚውል ሲሆን 70 ከመቶ የሚሆነው የአፈር ማዳበሪያ ይባክናል ተብሏል።