አብን በቀጣዩ ምርጫ የመሳተፍ አቅም አይኖረውም-አባላቱ
ቅዳሜ ጥር 24 ቀን 2017 (አዲስ ማለዳ) የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) 300 የሚደርሱ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶቹ በሥራ ላይ ባለመኾናቸው በቀጣዩ ጠቅላላ ምርጫ የመሳተፍ አቅም አይኖረውም ሲሉ አንዳንድ አባላቶቹ ለዋዜማ ተናግረዋል።
ከፓርቲው አባላት የተወሰኑት መንግሥትን ለመግልበጥ ሙከራ አያደረጋችኋል ተብለው ለ6 ወራት ከታሠሩ በኋላ፣ ባለፈው ሳምንት እንደተፈቱም በዘገባው ተመላክቷል።
አብን መጋቢት 11 ቀን፣ 2014 ዓ፣ም በባሕርዳር ከተማ ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባኤ በምርጫ ቦርድ ተቀባይነት ባለማግኘቱ ጉባኤው በድጋሚ እንዲካሄድ ቦርዱ ቢያዝም፣ እስካኹን ድረስ ፓርቲው ጉባኤውን ማካሄድ አልቻለም።
የፓርቲው አመራሮች ከምርጫ ቦርድ ጋር ያላቸው ንግግር በግልጽ የማይታወቅ መኾኑ፣ የፓርቲውን ሕልውና አሳሳቢ እንዳደረገው አባላቱ ገልጸዋል።
የአብን አባላት በፓርቲው ወቅታዊ ቁመና ዙሪያ ላነሱት ቅሬታ፣ የፓርቲው አመራሮች ምላሽ እንዲሠጡ ዋዜማ ያደረገው ጥረት እንዳልተሳካም አስታውቋል።
ቅዳሜ ጥር 24 ቀን 2017 (አዲስ ማለዳ) የአማራ ብሄራዊ ንቅናቄ (አብን) 300 የሚደርሱ ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤቶቹ በሥራ ላይ ባለመኾናቸው በቀጣዩ ጠቅላላ ምርጫ የመሳተፍ አቅም አይኖረውም ሲሉ አንዳንድ አባላቶቹ ለዋዜማ ተናግረዋል።
ከፓርቲው አባላት የተወሰኑት መንግሥትን ለመግልበጥ ሙከራ አያደረጋችኋል ተብለው ለ6 ወራት ከታሠሩ በኋላ፣ ባለፈው ሳምንት እንደተፈቱም በዘገባው ተመላክቷል።
አብን መጋቢት 11 ቀን፣ 2014 ዓ፣ም በባሕርዳር ከተማ ያካሄደውን ጠቅላላ ጉባኤ በምርጫ ቦርድ ተቀባይነት ባለማግኘቱ ጉባኤው በድጋሚ እንዲካሄድ ቦርዱ ቢያዝም፣ እስካኹን ድረስ ፓርቲው ጉባኤውን ማካሄድ አልቻለም።
የፓርቲው አመራሮች ከምርጫ ቦርድ ጋር ያላቸው ንግግር በግልጽ የማይታወቅ መኾኑ፣ የፓርቲውን ሕልውና አሳሳቢ እንዳደረገው አባላቱ ገልጸዋል።
የአብን አባላት በፓርቲው ወቅታዊ ቁመና ዙሪያ ላነሱት ቅሬታ፣ የፓርቲው አመራሮች ምላሽ እንዲሠጡ ዋዜማ ያደረገው ጥረት እንዳልተሳካም አስታውቋል።