ኤልሮኢ:(⚜ምክር⚜)
ዝምተኛው መነኩሴ (#ራስአገዝ)
ከዝምተኛው መነኩሴ አባ ዮስጦስ ፀሎት አንዱ "ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ቅዱሳን በተጓዙበት ጎዳና ምራኝ" ነበር፡፡ የዚህ ጸሎት ትርጉም ቅዱስ አድርገኝ ማለት እንደነበር በህይወታቸው ፍፃሜ በሚገባ ተረድተናል፡፡ ቅዱስ እንደሆኑ ማሰብ እንጂ ቅዱስ ለመሆን ማሰብ ወይም በቅድስና መንገድ ለመጓዝ መሻትና መጸለይ መልካም ነው፤ ምክንያቱም ከፈጣሪያችን ትእዛዛትና ፈቃድ አንዱን ለመፈጸም መመኘት ነውና እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘዋል፡፡ እግዚአብሔር በቃሉ "እኔ ቅዱስ ነኝና እናንተም ቅዱሳን ሁኑ" እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስም "እኔ ክርስቶስን እንደምመስል እኔን ምሰሉ" በማለት የቅድስናን ህይወት እንድንኖር እንደመከረን ስናስተውል ቅዱስ የመሆን ትእዛዝ እንዳለብን እንረዳለን፡፡ ስለቅድስና ሲነሳ እኛ ቅዱሳን ልንሆን ይገባል ማለቱ በራሱ ወደር የማይገኝለት ድፍረት ሆኖ ሳይሰማን አይቀርም፡፡ነገር ግን መሻቱ ሳይሆን የቅድስና ቁምነገር ነኝ አለማለቱ እና በጭራሽም ነኝ ብሎ አለማሰቡ ላይ ነው፡፡ ሰው ቅዱስ የሚሆነውም ከእግዚአብሔር ፈቃድ ባሻገር በምርጫውና በፍላጎቱ ነውና ይህን የሚያስረዳን ነው።
ዲያቢሎስ ስለመረጠ ከቅድስና ጎድሏል፥ ቅዱሳን መላእክት ደሞ በምርጫቸው ቅዱሳን ሆነዋል ፡፡ሰውም እንዲሁ ነው፡፡ ስለዚህ ለቅድስና መጠራታችንን እና መታዘዛችን እንዲፈጸምልን መጸለይ መሻት መጣር ያስፈልገናል፡፡የጌታችን አማናዊ ቃሉ "ለምኑ፥ ይሰጣችሁማል፤ ፈልጉ፥ ታገኙማላችሁ፤ መዝጊያን አንኳኩ፥ ይከፈትላችሁማል።"ይለናልና።(ማቴ 7:7)
ስለዚህ ቅዱስ የመሆን ፍላጎት ቅዱስ ነውና በማሰባችን ወይም በመመኘታችን ድፍረት መስሎን መጨነቅ አይደገፍም፡፡ ነገር ግን በትህትና መለመንና ሁሉም ነገር በእግዚአብሔር ቸርነት እንደሚፈጸም ማመን ነው፡፡ ያለ እግዚአብሔር ቸርነት (ሰጪነት) በጥረታችን የምናገኘው ምንም ነገር የለም፡፡ "እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ። ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉምና በእኔ የሚኖር እኔም በእርሱ፥ እርሱ ብዙ ፍሬ ያፈራል።" (ዮሐ 15:5) እንዳለ ያለእርሱ ቅዱስ መሆን ቀርቶ ቅድስናን ማሰብም እንኳን አይቻልም፤ ከእርሱጋ ግን ሁሉ ይቻላል፡፡ ወደቅድስና ከሚመሩን በርካታ ነገሮች እጅግ ጥቂቶቹ በመቀጠል ቀርበዋል፡፡
✞የእግዚአብሔርን ቸርነት እና ፍቅር ማሰላሰል
✞ህዋሳትን ኃጢአት ከመስራት መጠበቅ
✞ ለሰሩት በደል በቶሎ መፀፀት
✞ከሰው ክብርን አለመፈለግ
✞ምስጋናን አለመሻት
✞ ጥላቻንና ትችትን በፍቅር መቀበል
✞ መጸሐፍቅዱስን አዘውትሮ ማንበብ
✞ ያለማቋረጥ መጸለይ
✞በምስጢራት መካፈል
✞ትእዛዛቱን ለመፈጸም መጣጣር
✞በምክረ ንስሀ መጓዝ
✞ራስን እንደተለየ ነገር አለመቁጠር
✞ራስን መገምገም መመልከት
✞ቃለእግዚአብሔርን ማዳመጥና
✞የምንሰማዉን ቃል መፈጸም
✞ከልብ የሆነ ጾምን መጾምና መጸለይ
✞በጎ አድራጎትን መፈጸም
ማንኛውም የምንሰራው ሥራ እግዚአብሔርን ደስ እንዲያሰኝ ብሎ እንጂ አንዳች ጥቅም አገኝበታለሁ በማለት አይደለም፡፡ መሪ ምክንያቱ ፍቅር እንጂ ጥቅም መሆን የለበትም፡፡ ለቅድስና መጋደል እንጂ ቅዱስ እንደሆኑ ማሰብ መጀመር የውድቀት መጀመሪያው ሳይሆን መጨረሻ መሆኑን ማስመር ይገባል፡፡ እነኚህ በየጥቂቱ ልናድግባቸው የምንችላቸው መንፈሳዊ ተጋድሎ የሚጠይቁ ልምምዶች ናቸው ፡፡
ይቆየን!
@aleroe
@AleroeBot
ዝምተኛው መነኩሴ (#ራስአገዝ)
ከዝምተኛው መነኩሴ አባ ዮስጦስ ፀሎት አንዱ "ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ ሆይ ቅዱሳን በተጓዙበት ጎዳና ምራኝ" ነበር፡፡ የዚህ ጸሎት ትርጉም ቅዱስ አድርገኝ ማለት እንደነበር በህይወታቸው ፍፃሜ በሚገባ ተረድተናል፡፡ ቅዱስ እንደሆኑ ማሰብ እንጂ ቅዱስ ለመሆን ማሰብ ወይም በቅድስና መንገድ ለመጓዝ መሻትና መጸለይ መልካም ነው፤ ምክንያቱም ከፈጣሪያችን ትእዛዛትና ፈቃድ አንዱን ለመፈጸም መመኘት ነውና እግዚአብሔርን ደስ ያሰኘዋል፡፡ እግዚአብሔር በቃሉ "እኔ ቅዱስ ነኝና እናንተም ቅዱሳን ሁኑ" እንዳለ ቅዱስ ጳውሎስም "እኔ ክርስቶስን እንደምመስል እኔን ምሰሉ" በማለት የቅድስናን ህይወት እንድንኖር እንደመከረን ስናስተውል ቅዱስ የመሆን ትእዛዝ እንዳለብን እንረዳለን፡፡ ስለቅድስና ሲነሳ እኛ ቅዱሳን ልንሆን ይገባል ማለቱ በራሱ ወደር የማይገኝለት ድፍረት ሆኖ ሳይሰማን አይቀርም፡፡ነገር ግን መሻቱ ሳይሆን የቅድስና ቁምነገር ነኝ አለማለቱ እና በጭራሽም ነኝ ብሎ አለማሰቡ ላይ ነው፡፡ ሰው ቅዱስ የሚሆነውም ከእግዚአብሔር ፈቃድ ባሻገር በምርጫውና በፍላጎቱ ነውና ይህን የሚያስረዳን ነው።
ዲያቢሎስ ስለመረጠ ከቅድስና ጎድሏል፥ ቅዱሳን መላእክት ደሞ በምርጫቸው ቅዱሳን ሆነዋል ፡፡ሰውም እንዲሁ ነው፡፡ ስለዚህ ለቅድስና መጠራታችንን እና መታዘዛችን እንዲፈጸምልን መጸለይ መሻት መጣር ያስፈልገናል፡፡የጌታችን አማናዊ ቃሉ "ለምኑ፥ ይሰጣችሁማል፤ ፈልጉ፥ ታገኙማላችሁ፤ መዝጊያን አንኳኩ፥ ይከፈትላችሁማል።"ይለናልና።(ማቴ 7:7)
ስለዚህ ቅዱስ የመሆን ፍላጎት ቅዱስ ነውና በማሰባችን ወይም በመመኘታችን ድፍረት መስሎን መጨነቅ አይደገፍም፡፡ ነገር ግን በትህትና መለመንና ሁሉም ነገር በእግዚአብሔር ቸርነት እንደሚፈጸም ማመን ነው፡፡ ያለ እግዚአብሔር ቸርነት (ሰጪነት) በጥረታችን የምናገኘው ምንም ነገር የለም፡፡ "እኔ የወይን ግንድ ነኝ እናንተም ቅርንጫፎች ናችሁ። ያለ እኔ ምንም ልታደርጉ አትችሉምና በእኔ የሚኖር እኔም በእርሱ፥ እርሱ ብዙ ፍሬ ያፈራል።" (ዮሐ 15:5) እንዳለ ያለእርሱ ቅዱስ መሆን ቀርቶ ቅድስናን ማሰብም እንኳን አይቻልም፤ ከእርሱጋ ግን ሁሉ ይቻላል፡፡ ወደቅድስና ከሚመሩን በርካታ ነገሮች እጅግ ጥቂቶቹ በመቀጠል ቀርበዋል፡፡
✞የእግዚአብሔርን ቸርነት እና ፍቅር ማሰላሰል
✞ህዋሳትን ኃጢአት ከመስራት መጠበቅ
✞ ለሰሩት በደል በቶሎ መፀፀት
✞ከሰው ክብርን አለመፈለግ
✞ምስጋናን አለመሻት
✞ ጥላቻንና ትችትን በፍቅር መቀበል
✞ መጸሐፍቅዱስን አዘውትሮ ማንበብ
✞ ያለማቋረጥ መጸለይ
✞በምስጢራት መካፈል
✞ትእዛዛቱን ለመፈጸም መጣጣር
✞በምክረ ንስሀ መጓዝ
✞ራስን እንደተለየ ነገር አለመቁጠር
✞ራስን መገምገም መመልከት
✞ቃለእግዚአብሔርን ማዳመጥና
✞የምንሰማዉን ቃል መፈጸም
✞ከልብ የሆነ ጾምን መጾምና መጸለይ
✞በጎ አድራጎትን መፈጸም
ማንኛውም የምንሰራው ሥራ እግዚአብሔርን ደስ እንዲያሰኝ ብሎ እንጂ አንዳች ጥቅም አገኝበታለሁ በማለት አይደለም፡፡ መሪ ምክንያቱ ፍቅር እንጂ ጥቅም መሆን የለበትም፡፡ ለቅድስና መጋደል እንጂ ቅዱስ እንደሆኑ ማሰብ መጀመር የውድቀት መጀመሪያው ሳይሆን መጨረሻ መሆኑን ማስመር ይገባል፡፡ እነኚህ በየጥቂቱ ልናድግባቸው የምንችላቸው መንፈሳዊ ተጋድሎ የሚጠይቁ ልምምዶች ናቸው ፡፡
ይቆየን!
@aleroe
@AleroeBot