የጠፈር ጉዞው ወጪ 55 ሚሊዮን ዶላር‼️
'ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደ ጠፈር ለሚያደርጉት ጉዞ 55 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ይደርግበታል‼️
መሠረት ሚድያ ከሀገር ውስጥ እንዲሁም በዋናነት በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ከሚገኙ ምንጮቹ ለበርካታ ቀናት ሲያሰባስበው የነበረው መረጃ እንደሚጠቁመው በአለም ታሪክ ለመጀመርያ ግዜ የአንድ የሀገር መሪ ወደ ጠፈር ሊጓዝ ሰፊ እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው፣ መንገደኛውም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ናቸው።
በኤምሬቶች የሚገኙ ምንጮቻችን እንዳረጋገጡልን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ጠፈር የመጓዛቸው አላማ በርካታ ግቦችን አካቷል፣ ከእነዚህም መሀል የሰላም እና የአንድነት መልዕክት ለአለም ብሎም ለኢትዮጵያውያን ማስተላለፍ እንዲሁም ወጣቶች ወደ ቴክኖሎጂው ዘርፍ እንዲሳቡ እና እንዲነሳሱ ለማድሩግ ታስቧል።
"ውይይቱ በኢትዮጵያ መንግስት እንዲሁም በተባበሩት ኤምሬቶች በኩል በስፋት ንግግር እየተደረገበት ነው" ያሉት አንዱ በዱባይ የሚገኝ የመረጃ ምንጭ በተለይ ከጠፈር ላይ ሆኖ ለአለም ህዝብ መልዕክት ማስተላለፍ የእቅዱ ዋና ግብ ነው ብለዋል።
'Project X' የሚል ስም ተሰጥቶት እየተሰራበት እንደሆነ የሚነገርለት ይህ የጠፈር ጉዞ ወጪው በተባበሩት ኤምሬቶች የሚሸፈን መሆኑን አንድ ሌላ እዛው ዱባይ የሚገኝ ምንጭ ለሚድያችን ተናግሯል።
ለመዳሰስ የሞከርናቸው ፅሁፎች እንደሚጠቁሙት ወደ ጠፈር የሚደረግ ጉዞ ለአንድ ሰው ከትንሹ 250 ሺህ ዶላር እስከ ከፍተኛው 55 ሚልዮን ዶላር ሊደርስ እንደሚችል ይጠቁማሉ።
ለምሳሌ 'Blue Origin' እና 'Virgin Galactic' የተባሉት መንኩራኩሮች ከንፍቀ ክበብ በታች ለሚደረግ እና ርካሽ የተባለ ጉዞ ከ200 ሺህ ዶላር እስከ 400 ሺህ ዶላር ያስከፍላሉ፣ ራቅ ያሉ እና ከንፍቀ ክበብ ውጪ የሚደረጉ የጠፈር በረራዎችን የሚያከናውኑት እንደ 'Space X' ያሉ ሮኬቶች ደግሞ በአንድ ሰው እስከ 55 ሚልዮን ዶላር (7.3 ቢልዮን ብር) እንደሚያስከፍሉ ታውቋል።
ጠ/ሚር አብይ ሊጓዙ እቅድ የያዙት ከንፍቀ ክበብ ውጪ ወደ አለም አቀፉ የጠፈር ማዕከል (International Space Station) እንደሆነ ታውቋል፣ ወጪውም ከላይ እንደተጠቀሰው በአንድ ሰው እስከ 55 ሚልዮን ዶላር እንደሚደርስ እና በኤምሬቶች እንደሚሸፈን ታውቋል።
====================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
'ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ወደ ጠፈር ለሚያደርጉት ጉዞ 55 ሚሊዮን ዶላር ወጪ ይደርግበታል‼️
መሠረት ሚድያ ከሀገር ውስጥ እንዲሁም በዋናነት በተባበሩት አረብ ኤምሬቶች ከሚገኙ ምንጮቹ ለበርካታ ቀናት ሲያሰባስበው የነበረው መረጃ እንደሚጠቁመው በአለም ታሪክ ለመጀመርያ ግዜ የአንድ የሀገር መሪ ወደ ጠፈር ሊጓዝ ሰፊ እንቅስቃሴ እየተደረገ ነው፣ መንገደኛውም ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ ናቸው።
በኤምሬቶች የሚገኙ ምንጮቻችን እንዳረጋገጡልን ጠቅላይ ሚኒስትሩ ወደ ጠፈር የመጓዛቸው አላማ በርካታ ግቦችን አካቷል፣ ከእነዚህም መሀል የሰላም እና የአንድነት መልዕክት ለአለም ብሎም ለኢትዮጵያውያን ማስተላለፍ እንዲሁም ወጣቶች ወደ ቴክኖሎጂው ዘርፍ እንዲሳቡ እና እንዲነሳሱ ለማድሩግ ታስቧል።
"ውይይቱ በኢትዮጵያ መንግስት እንዲሁም በተባበሩት ኤምሬቶች በኩል በስፋት ንግግር እየተደረገበት ነው" ያሉት አንዱ በዱባይ የሚገኝ የመረጃ ምንጭ በተለይ ከጠፈር ላይ ሆኖ ለአለም ህዝብ መልዕክት ማስተላለፍ የእቅዱ ዋና ግብ ነው ብለዋል።
'Project X' የሚል ስም ተሰጥቶት እየተሰራበት እንደሆነ የሚነገርለት ይህ የጠፈር ጉዞ ወጪው በተባበሩት ኤምሬቶች የሚሸፈን መሆኑን አንድ ሌላ እዛው ዱባይ የሚገኝ ምንጭ ለሚድያችን ተናግሯል።
ለመዳሰስ የሞከርናቸው ፅሁፎች እንደሚጠቁሙት ወደ ጠፈር የሚደረግ ጉዞ ለአንድ ሰው ከትንሹ 250 ሺህ ዶላር እስከ ከፍተኛው 55 ሚልዮን ዶላር ሊደርስ እንደሚችል ይጠቁማሉ።
ለምሳሌ 'Blue Origin' እና 'Virgin Galactic' የተባሉት መንኩራኩሮች ከንፍቀ ክበብ በታች ለሚደረግ እና ርካሽ የተባለ ጉዞ ከ200 ሺህ ዶላር እስከ 400 ሺህ ዶላር ያስከፍላሉ፣ ራቅ ያሉ እና ከንፍቀ ክበብ ውጪ የሚደረጉ የጠፈር በረራዎችን የሚያከናውኑት እንደ 'Space X' ያሉ ሮኬቶች ደግሞ በአንድ ሰው እስከ 55 ሚልዮን ዶላር (7.3 ቢልዮን ብር) እንደሚያስከፍሉ ታውቋል።
ጠ/ሚር አብይ ሊጓዙ እቅድ የያዙት ከንፍቀ ክበብ ውጪ ወደ አለም አቀፉ የጠፈር ማዕከል (International Space Station) እንደሆነ ታውቋል፣ ወጪውም ከላይ እንደተጠቀሰው በአንድ ሰው እስከ 55 ሚልዮን ዶላር እንደሚደርስ እና በኤምሬቶች እንደሚሸፈን ታውቋል።
====================
💎⬇️⬇️⬇️👇👇👇👇👇👇
የቴሌግራም ቻናላችንን join በማድረግ ወቅታዊ መረጃዎችን በቀላሉ ይከታተሉ፣ሊንክ👇
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s
https://t.me/+Vl6V8k9V3YNEOp2s