"ወንጌል ስለ ኢየሱስ ብቻ ነው" ያለ ማን ነው?
ተሳስቷል።
የፍቅሩና ቤዛነቱ ምስክር የኾኑ ቅዱሳትና ቅዱሳን መታሰቢያቸው በወንጌል እንዲጻፍ ያዘዘ እርሱ ራሱ ኢየሱስ ነውና።
በዝሙት የኖረች አንዲት ሴት ነበረች። ማርያም ዘናይን/ኀጥእት ትባላለች።
የጌታችን ክርስቶስን የእጁን ተአምራት አላየችም። የቃሉን ትምህርት አልሰማችም። እንደወትሮዋ በመስታወት ፊት ቆማ ስትኳኳል፥ ውበቷን የሚያጠፋ ሞት ትዝ አላት።
ይቅርታና ምሕረት ለማግኘት ወደ መሐሪው ጌታ ፈጥና ኼደች። በስምዖን ፈሪሳዊ ቤት አገኘችው።
"የረከሰ ነገርን የነካችኹ እጆቼ ሆይ፥
የጌታ ክርስቶስን እግር ትዳስሱ ዘንድ ታደላችኹ።" እያለች የጌታዋን እግር በዕንባ አጠበች።
ጌታችን ክርስቶስም "እምነትሽ አድኖሻል በሰላም ሂጂ አላት"
ደቀ መዛሙርቱንም እንዲህ ሲል አዘዛቸው።
“እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ወንጌል በዓለም ሁሉ በማናቸውም ስፍራ በሚሰበክበት እርስዋ ያደረገችው ደግሞ ለእርስዋ መታሰቢያ እንዲሆን ይነገራል።”
ማቴዎስ 26፥13
በሰላም ሂጂ ያላት ጌታ፥ ዛሬ የካቲት ስድስት ወደ ጻድቃን ከተማ ወሰዳት።
ይኽች ማርያም፥ የአልዐዛር እኅት ማርያም ወይም ማርያም መግደላዊት አይደለችም።
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮
@dnzema
@dnzema
@dnzema
╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯
ተሳስቷል።
የፍቅሩና ቤዛነቱ ምስክር የኾኑ ቅዱሳትና ቅዱሳን መታሰቢያቸው በወንጌል እንዲጻፍ ያዘዘ እርሱ ራሱ ኢየሱስ ነውና።
በዝሙት የኖረች አንዲት ሴት ነበረች። ማርያም ዘናይን/ኀጥእት ትባላለች።
የጌታችን ክርስቶስን የእጁን ተአምራት አላየችም። የቃሉን ትምህርት አልሰማችም። እንደወትሮዋ በመስታወት ፊት ቆማ ስትኳኳል፥ ውበቷን የሚያጠፋ ሞት ትዝ አላት።
ይቅርታና ምሕረት ለማግኘት ወደ መሐሪው ጌታ ፈጥና ኼደች። በስምዖን ፈሪሳዊ ቤት አገኘችው።
"የረከሰ ነገርን የነካችኹ እጆቼ ሆይ፥
የጌታ ክርስቶስን እግር ትዳስሱ ዘንድ ታደላችኹ።" እያለች የጌታዋን እግር በዕንባ አጠበች።
ጌታችን ክርስቶስም "እምነትሽ አድኖሻል በሰላም ሂጂ አላት"
ደቀ መዛሙርቱንም እንዲህ ሲል አዘዛቸው።
“እውነት እላችኋለሁ፥ ይህ ወንጌል በዓለም ሁሉ በማናቸውም ስፍራ በሚሰበክበት እርስዋ ያደረገችው ደግሞ ለእርስዋ መታሰቢያ እንዲሆን ይነገራል።”
ማቴዎስ 26፥13
በሰላም ሂጂ ያላት ጌታ፥ ዛሬ የካቲት ስድስት ወደ ጻድቃን ከተማ ወሰዳት።
ይኽች ማርያም፥ የአልዐዛር እኅት ማርያም ወይም ማርያም መግደላዊት አይደለችም።
ለኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ልጆች👇
•➢ ሼር // SHARE
╭══•|❀:✞✟✞❀|•══╮
@dnzema
@dnzema
@dnzema
╰══•|❀:✞✟✞❀|•══╯