ይህ ጽሑፍ፣ አንድ ወንድም ፊተኛ መጽሐፌን አንብቦ የሰጠኝ ሰፋ ያለ አስተያየት ነው፤ ምናልባት ለመማማር ይጠቅማል በማለት ከተሰጡ ብዙ አስተያየቶች ይህን መርጫለኹ፤ አንብቡና አስተያየት ስጡበት፤ አስተያየቱ የአስተያየት ሰጪው ወንድም መኾኑን መግለጥ ወዳለኹ፡፡
ይድረስ ለዲያቆን አቤን ኤዘር ተክሉ
የእምነት እንቅስቃሴ የዛሬዪቱ ቤተ ክርስቲያን ፈተና ነው ያሉትን መጻሕፍዎን እያየሁ ነኝ፡፡ መጀመሪያ በርዕስ፣ ቀጥሎም በፍሬ፡፡ በጥሩ እንቅስቃሴ ውስጥ መሆንዎ ይሰማኛል፡፡አንዳንዴም እጅግ ቀላሉንና ፍቺ የማያስፈልገውን ቃል አፌ ታሪካዊ ትምህርት አደርገውት ጎርጎጭ እንዲል እንዳደረጉትም በግል ግንዛቤዬ ታይቶኛል፡፡ እንደ እኔ ላለው ተራ ሕዝብ የማንረዳቸው ቃላት በመጠቀምዎም እኔም ተቸግረበታለሁ፡፡ አዳዲስ ቃላትም ተምሬበታለሁ፡፡ የተቀረውን እንደሚከተለው ልመስክር፡፡
የሐ*ሰት መምህራን ብለው ካቀረቡአቸው አንዳንዶቹ እጅግ የታወቁ ሆኖ ስለማውቃቸው የጋራ ግንዛቤ አለን፡፡ ማስረጃ አሰባሰብዎ እጅግ ጊዜ የፈጀ መሆኑ አያጠራጥርም፡፡ ለስኬት ተነሳሽነትዎ ውስጣዊ ቅናትዎን አሳይቷልና አስደናቂ ነው፣ ተወዳጅም ነው፡፡ የተመሩበት መሪ ሥነ መለኮት ነው፣፡ እርሱ የሰው ጥበብ ፍልስፍናን፣ ወግንና አመክንዮን የተላበሰ ሐ*ሰትን እውነት ለማስመሰልም ኃይል ያለው ነው፡፡ በመጽሐፉ ይዘት ብቻ ነው ምመሰክርና ስለ አስቀሩአቸው የዘመኑ ክፉ እንቅስቃሴዎች ለማንሳት መነሻ አይሆነኝም በስተ ኋላ ላይ የማክለው ይኖረኛል፡፡ እንደርስዎ የሚተጉትን ቢስቱ እንኳ ክፉኛ ከመንቀፍ እጠነቀቃለሁ፡፡ በቸር እመለከታለሁ፡፡ ድርቅ ብለው ክችች በለው አይቀሩምና፡፡ ኦርቶዶክስ ምን ትላለች ከሚል ድምጽ ይልቅ ‹‹እግዚአብሄር እንዲህ ይላል፣›› አዋጭ ነው፡፡ ድንቅ መልሶች የሰጡባቸው ነገሮች ብዙ ናቸውና ማስጠንቀቂያዎ ተነሳሽነትንም ይቀሰቅሳል፡፡ በራስዎ ሂደት እና በእውነት ብርሃን የራስዎን ስህተት ለማስተከሳል አቅም ስላለዎ ቃሉን ከወደዱ ሊመለሱ ለመታረም አይከብዶዎትም፣፡ በጥረትዎ ላይ አድናቆት አለኝ፡፡
በዓላማው ፣ በጌታ የሱስ መድኃኒትነት ማመንን፣ መጽሐፍ ቅዱስ በእግዚአብሄር መንፈስ መጻፉንና፣ በሥላሴዎች ስም የማጥመቅን የጋራ እምነት እንካፈል በሚል Ecumenism (የክርስቲያን ሕብረት) ብሎ ራሱን ፈጥሮ የሰ*የመውን አያውቁትምን? ፡፡ እነዚህ ሦስት ቃሎች ለሕብረቱ በጋራ የተያዘው የመግባቢያ ነጥብ ሽፋን ነው፡፡ ዋናው ስኬቱ ቤተ ክርስቲያንን ከክርስቶስ በላይ ማውጣት ነው፡፡ ሕገ እግዚአብሄርን መርገጥ ነው፡፡ የልተቀደሰውን በመቀደስ መር*ገምን መፍጠር ነው፡፡ እግዚአብሄር እንዲህ ይላል በቤተ ክርስቲያን እንዲህ ትላለች ለመተካትና፣ የመንግስትና የቤተ ክርስቲያን ቅልቅልነት በሚፈጠረው አቅም ጻድቃንን ለመሳደድ ነው፡፡ ይህ ዋና ነገር እርስዎ በቅናት ማስጠንቀቂያ ከሰጡባቸው የሐሰት መምህራን ሲተያይ በእጅጉ አይተልቅምን? እዚህ ላይ የቀደመ ትጋትዎን ይቀጥሉበት፡፡ የህብረቱ ውጤት ግን ኤርሚ 8፡11 እና 1ተሰሎንቄ 5፡ 3 ወደ መፍጠር መጥቶ የዓለምን ዕድሜ አሳጥሮ፣ ሃሳባቸውንም ገለብጦ ያከስማል፡፡፡
የህብረቱ አባል ዋና ቤተ ክርስቲያናት ዝርዝር እነሆ!
ክርስቶስ አልባውን ሕብረት
የወገኑ ማህበርተኞች
1. Old Catholic churches
2. Orthodox church {eastern}
3. Orthodox church {oriental}
4. Pentecostal churches
5. Reformed churches
6. Seventh Adventist church
7. The Assyrian church
8. The Salvation Army
9. The {Roman} Catholic church
10. United and Uniting churches.
{Source
www.oikoumene.org/ church families
ከነዚህ ውስጥ ነው ክርስቶስ ልጆቹን አበጥሮ የሚያጣቸውና መጥቶም የሞቱትን አስነስቶ በሕይወት ያሉትን በዐይን- ውልብታ ፍጥነት ለውጦ ወደ አብ የሚወስዳቸው ብዬ አምናለሁ፡፡ቲዎሎጂዎን ወደጎን አድርገው መጽሐፍ ቅዱስን ብቻ ቢያነቡ ብዙ ነገር ያመጡልናል ብዬ አምናለሁ፡፡ አይሆንምን? በየቤተ ክርስቲያኑ ርኩ*ስና ርኩ*ሰት ገብቷል፣ አለ፡፡ ከላይ በተዘረዘረው በማህበሩ ካሉቱ ባለ10 አባላት ቤተ ክርስቲያናት ሕብረት ወገኞች በየቤተ ክርስቲያናቱ ጻድቃን ቅሬታዎች ይኖሩ ይሆናል፡ ምክንያቱም ክርስቶስ ‹‹ከዚህ ያልሆኑ በጎች አሉኝ፣ ሂጄ ላመጣቸው ይገባኛል፣ ያለበት ቦታ ስላለ፣ ርኩሱ የበዛ ይሆናል፡፡አሉምም፡፡ በጅምላ በቤተ ክርስቲያን ድርጅት ስም ፍርድ የለምና፣ በስምም መዳን የለምና፣ መመኪያም አይሆንም፡፡ ከጅምላ ፍርድ ይልቅ ስሁቱ ላይ ጠቁሞ ማስተማር ተገቢ ይሆናልን አምናለሁ፣ ለምን ቢባል የፍቅር ጥሪ ነው፤ ተመለስ ማለትም ስለሚሆን፡፡ ለዚሁም እንደ ቤሪያ ሰዎች ቃሉን በቡድን ማጥናት የሚሻል እየመሰለኝ ነው፡፡ ከዚያ የአሸናፊ ቤተ ክርስቲያንን አባሎች ከተበተኑበት በጥበብ ሠርቶ የሚያሰባስብ ድርጅት የክርስቶስ መዝገብ ይሆናል እንበል እንጂ፣ ሕገ እግዚአብሄር ጠሎችንና ከክርስቶስ በላይ ራስዋን የምታስቀምጠውን ክርስቶስ አልባ ቤተ ክርስቲያንን ለማቆም አሥርቱን አሰባስቦና መሥርቶ አንድ ድርጅት ካደረገ በኋላ አለመሆኑን ከወዲሁ እናስብ፡፡ አብዛኛዎቻቸው ለግብረ-ሰዶማውያን መብት ለመፍጠር የሚረዱ፣ሴትን የሚያቀስሱ፣ ክርስቶስ አልባ ሕብረትን (Unity at any cost፣ በምንም ሁኔታ ሕብረቱን አምጣ) እያሉ የካ*ዱ ናቸው፡፡ ሌሎቹ በዝምታ ብቻ ይመለከታሉ፡፡ እነዚህ ናቸው የክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን የሚያዋቅረቱ? ሰይጣን አስርቱን የሚሰባስበው እነርሱ ቅዱሳንን ካሳደዱለትና ካጠፉ በኋላ፣ እርሱ ተመልሶ እነርሱንም እርስ በርስ ሊያነካክታቸው ፣ (በአንድነት ሊወቃቸውም) ነው የሚል ድምዳሜን የያዘ፣ (እርስዎ ላይቀበሉኝ ይችላሉ) መሆኑን ከከዳንኤልና ከራዕይ ትንቢትም አጥንቻለሁ፡፡ ጉዞው የት እንደሚያበቃ ላሳይ በዚሁ አጋጣሚ ይህን ለማከል አሳሰበኝ፡፡ በዚህ ላይ የጥናትዎን ውጤት ለመስማትም እናፍቃለሁኝ፡፡
በሁላችንም ብርሃኑን በልባችን ያግባው፡፡ እርሱ የራሱን ያውቃል ብለን ይበልጥ ታታሪ በመሆን ክርስቶስ መሰል ባህርይን ብንራብና ብንጠማ፣ ቅድስናን በቅጥልፍና በየዕለቱከፍ ብናደርግና ውብ የክርስቶስን አርአያነት ብንከተል ይህ አይበልጥብንምን? ባለንበት እንበርታ፡፡
እውነት ታሰባስበናለች ክርስቶስ እውነትም መንገድም ነውና፡፡ ከክርስቶስ ወዲያ የማንም ቤተ ክርስቲያን ስም መመኪያ አይሁነን፣ ለምድርና ለወንጌል ብለን እያየን ልንጠራበት ያህል ይሁን፡፡ ለሰማይ ግን ሙያ በልብ ይሁን፣ ቃሉን እንያዝ፣፡ የመጽሐፍ ቅዱስ መልዕክት ብቻ አበጥረን እንወቅና እንቀበል፡፡ አጥፊን ማጋለጡ ስሁታንንም ጻድቃንንም ለመታደግ ነው መባሉ ተገቢ ነው፡፡ በጥረትዎ ይትጉልኝ፡፡ አንድ ዜጋ ያድርገን፡፡ ለዚሁ መንገዱን ያሳየን ዘንድ ከልብ እጸልያለሁ፡፡
My telegram Link -
https://t.me/ebenezertek