Postlar filtri


እንናፍቃለን!

ከሰሞኑ ኦርቶዶክሳውያኑን በዋናነት በገድላት፣ “ማርያም ኀጢአት አለባት ወይስ የለባትም?” እና በሌሎችም ጉዳዮች “እየተፈሳፈሱ” ይመስለኛል፡፡ ቀሲስ ዲበኩሉ በላይ የተባሉት “አባት”፣ “ሐዋርያዊ መልሶች” በሚል ስያሜ በተለያዩ ማኅበራዊ ሚዲያዎች ላይ ከሚያገለግለው አክሊል ከሚባል “ወጣት” ጋር በተለይ “ገድልን መርምሬ እንጂ በደፈናው አልቀበልም” በማለቱ ብዙዎች ቲክቶዶክሶች ጥርስ ነክሰውበታል፡፡ በሌላ በኩል ደግሞ፣ “ማርያም ኀጢአት አለባት” ብሎአል በሚል ሌላኛው አባት አስጠንቅቀዋል ተባለ፡፡ ነገሩ እንደ ዘበነ ለማ ያሉ ሰዎችም ፊት ለፊት ስሙን ጠቅሰው ባይናገሩም፣ ነገር ግን “ገድል አልቀበልም የሚል ኦርቶዶክስ አይደለም” በማለት አቋማቸውን አንጸባርቀዋል፡፡

በአጭሩ የገድልና የማርያም “ልዕለ ልዕልትነት” ጉዳይ ይህን ያህል ያጨቃጨቀው እነ ዘበነንም ኾነ ቄስ ዲበ ኩሉን፤ አስጠንቃቂውን አባት ጠቅሞ አይደለም፤ ነገር ግን ቤተ ክርስቲያኒቱ ወደ እውነተኛ ወንጌል ፊቷን እንዳትመልስ ተግተው ስለሚሠሩና ስለሚፈልጉ እንጂ፡፡ ጌታ ኢየሱስ ይገስጻቸው!

እንደ በፊቱ በጥቂቱም ቢኾን፣ ኦርቶዶክሳዊ ተሐድሶ አቋምን የያዙ ሰዎች፣ በዚያው መድረክ ብቅ ማለታቸው ይበል የሚያሰኝ ነው፡፡ እኛም አቋማችን ለኦርቶዶክስ ሌላ ሐዳሲ እንዲመጣ አንሻም፤ የራስዋ ልጆች በትክክልና በእውነት፤ በማያመቻምች አቋም ትክክለኛ ሐዳሲ እንዲኾኑ ነው ናፍቆታችን፤ አክሊል የተባለውም ወጣት “ኹሉን አውቃለሁ ባይነቱን” ትቶ፣ በክርስቶስ ባለው መዳንና ጸጋ ተግቶ፣ በቤቱ ውስጥ ያለውን የተነቀፈ ጽድቅና ቅድስና፤ መካከለኛና አስታራቂ በመናገር፤ በመስበክ ቢተጋ በእግዚአብሔር ሉዓላዊነት ብዙዎች ወደ ወንጌል ይመጣሉ የሚል እምነት አለኝ!
አክሊል፤ ወደ እኛም ኾነ ወደ ወንጌላውያን መምጣት አለበት ብዬ አላምንም፤ ሸክሙ ወገኖቹ፤ ጭንቀቱ ኦርቶዶክሳውያን ሊኾኑ ይገባል፤ ጨርሶ ካልተገፋ በቀር ሊወጣ አይገባውም ከሚሉ አንዱ ነኝ!

ኦርቶዶክሳዊ ተሐድሶ እንደ ቃሉና እንደ መንፈስ ቅዱስ ምሪት ብቻ እንዲኾን እንናፍቃለን!




ሕይወት ቴቪን "የእውነት ቃል አገልግሎት" ሊታደግ?


መጽሐፍ ቅዱስ በግልጥ ቃል፣ “አትሳቱ፤ ክፉ ባልንጀርነት መልካሙን አመል ያጠፋል።” (1ቆሮ. 15፥33) ይላል። “አትሳቱ” የሚባለው ለሚያውቁና ለተረዱ አማኞች ነው። የሚባልበትም ምክንያት፣ የሚያስቱና የሚያሳስቱ ስላሉ ነው። ከክፍሉ እንደምንረዳው በቆሮንቶሳውያን መካከል ትንሣኤ ሙታንን በመናቅና በማቃለል፣ ሕይወትን፤ ዕለታዊ ኑሮን ከመብልና ከመጠጥ ጋር ብቻ ያያያዙትን “አማኞች” ቅዱስ ጳውሎስ እንዲህ ካሉት መራቅና ኅብረታቸውን መተው እንደሚገባ ይናገራል። ምክንያቱም ክፉ ባልንጀርነት የመልካሙን ዐመል ስለሚያጠፋ ነው ይለናል። ከበላተኛ ከጠጪ ወይም የሆድን ነገር ብቻ ከሚያወሩ ጋር መዋል፣ ትንሣኤ ሙታንን እንድንንቅ ያደርጋሉና። በሌላ ንግግር የማይገባ ግንኙነት እንደ ጭንቁር እንደሚባላ ማስተዋል እንችላለን።


ይህን እንድል ያደረገኝ፣ ገና ከመከፈቱ "የታደጉኝ" ጥሪ ያቀረበውና ንብረትነቱ የቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን የኾነው ቴቪ፣ ምን ገጥሞት ታደጉኝ እንዳለ ለመገመትም ለማመንም ይቸግራል። ቤተክርስቲያኒቱ ሚሊዮናትን ያለፈ አባላትና አማኞች እንዳላት አውቃለኹ። ከወንጌላውያን አብያተ ክርስቲያናት የቀደምትነት ሥፍራ ከሚሰጣቸው መካከል ናት። ምናልባትም ለኦርቶዶክሳዊው የመጽሐፍ ቅዱስ ትምህርትና ሕይወት እንዲጸናና እንዳይበረዝ በዕቅበተ እምነት ላይ የሚሠሩ፤ እንዲኹም በማኅበራዊ ሕይወትና በሌሎችም ሥራዎች ላይ የሚሳተፉ እንደ ዶ/ር ተስፋዬ ሮበሌና ጌታሁን ሔራሞ ያሉ “ጉምቱዎችን” ያፈራች ቤተክርስቲያን ናት።

ቤተክርስቲያኒቱ ለተከታዮቿ በቴቪ አገልግሎት መምጣትዋ ይበል የሚያሰኝና እጅግ መልካም ነው። አማኞቿን ይዛ አብነትና ምሳሌነት ያለው ትልቅ ሥራ ትሠራለች፤ በግለኝነትና በከበርቴነት እንደ ፈለጉ ከሚፋንኑ “ነቢይና ሐዋርያ ተብዬዎች” በምታቀርበው ጠንካራ መርሐ ግብር ትኰንናለች፤ በተለየ መንገድ በኅብረትና ብዙዎችን በማሳተፍ የተዋጣለት ሥራ ያቀርባሉ ስንል፤ በጌጃ ያሉትን ከ40 ዓመታት በላይ እስከ ዛሬ ድረስ በዝማሬ የቆዩ እናትና አባቶችን ሕይወትና የአገልግሎት ፍሬአቸውን እንዲሁም በተለያዩ ቦታዎች ያሉትን ውብ የወንጌል ምስክርነቶችን ያቀርባሉ ብለን ገና እየጓጓን ሳለ ... ድንገት “ታደጉን” የሚል የድካም ጩኸት አሰሙን። ግን ለምን?

ሕይወት ቴቪ ከኤልሻዳይ ቴቪ ሊማር ይገባዋል። ኤልሻዳይ ቴቪ እንደ ኃይሉ ዮሐንስ፣ ግርማ በቀለና ዘላለም ጌታቸው ላሉ ሐ*ሰ*ተኛ አስተማሪዎች መድረኩን በመክፈት፣ የኢትዮጵያ ክርስትና እንዲቀየጥና እንዲመረዝ የላቀ ሚና ከተጫወቱት የሚመደብ ነው። ሕይወት ቴቪ ከዚህ ከኤልሻዳይ ቴቪ “ስብራት”፣ “እሳት እንደ ነካ ሕፃን” መማሪያ ካልኾነው ከምንም ሊማር አይችልም። አጉል ባልንጀርነት ዳፋውና ጦሱ ብዙ ነውና።

እኔ በግሌ፦ አስተዳደራዊ መዋቅር ቢያስተካክሉ፣ ወደ ሥራ የሚተገበር ስትራቴጂካዊ ዕቅድ ቢያዘጋጁ፣ አማኞቻቸውን በማስተባበር የገንዘብ አያያዝና አጠቃቀማቸውን ቢያስተካክሉ ... ሌሎችን ታደጉን ከሚል ልመና ነጻ ይወጣሉ ብዬ አምናለኹ። ከዚህ የሚከፋውና የሚያሳዝነው ግን ለትድግና የመጡት አካላት ናቸው። “የእውነት ቃል አገልግሎት” ይባላሉ። መሪያቸው ግርማ በቀለ ይባላል። ስለ “እውነት ቃል አገልግሎት” የተሳ*ሳተ ትምህርትና ልምምድ በአደባባይ ሲናገሩ ከነበሩት አንዱ እኔ ነኝ። እነርሱ ከእነርሱ ውጭ ያሉትን ኹሉ፣ በተለይ ኦርቶዶክስንና ቀደምት ወንጌላውያንን “ጋለሞታዎች” በማለት የሚጣሩ፣ ጤናማ የኾነ የትምህርትም ኾነ፣ የልምምድ ሕይወት የሌላቸው ናቸው። እናም ቃለ ሕይወት ቤተክርስቲያን ከኤልሻዳይ ቴቪ ተምራ ከቅይጥነት ነጻ እንድትወጣ እመኛለኹ። በርግጥ “ጋለሞታ” ወደሚሏት ቤተክርስቲያን ሊጠቅሟት አልመጡም።

የተሐድሶ አገልግሎትን በትምህርታቸውና በልምምዳቸው ከሚያዳክሙና በተጣ*መመ ትምህርታቸው ወደ ዓለማዊነት ከሚነዱት መካከል ቀዳሚዎቹ “የእውነት ቃል አገልግሎት” ቡድኖች ናቸው። የሚያሳዝነውና ልብ ሰባሪ ሥራቸው፣ የሚያጠምዱት “የዳኑትንና ወደ ጌታ የመጡትን” እንጂ ሌሎችን አያጠምዱም። እናም ቃለ ሕይወታውያን በቃለ ጥፋት እንዳትወረሱ ለራሳችኹ ተጠንቀቁ።

“ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን ባለመጥፋት ከሚወዱ ሁሉ ጋር ጸጋ ይሁን፤ አሜን።” (ኤፌ. 6፥24)

My telegram link - https://t.me/ebenezertek
My blog link -http://abenezerteklu.blogspot.com/2025/02/blog-post_68.html
My youtube link - http://www.youtube.com/@-abenezertekludiyakon8842


መላእክት፣ ቅዱሳን ሰዎች፣ ቅድስት ማርያም … ኹሉ እያሉ እግዚአብሔር አንድያ ልጁን ለመዳናችን ሰደደልን።


እኛ ኢትዮጵያውያን እኮ፣ ሚሊዮናትን የፈጀ ጦርነት አካሂደን ምንም ያልመሠለንና እንዲህም ኾነን ፍጹም "አማኝና ጻድቃን" እንደ ኾንን የምንናገር "የአሥራት አገር ሕዝብች ነን"¡ መገን!


"ገድል ካልተቀበልህ ኦርቶዶክስ አይደለህም" (ዘበነ ለማ)
"ገድል ለሃይማኖት ክርክር አንጠቀምም" (ቲክቶዶክሶቹ)
ለመዋሸት እንኳ ተስማሙ እንጂ!


ነክቶ መመለስ፤ ርኩ*ሰት ማስለመጃ መንገድ!

ከአዲስ አበባ አንዱ ትምህርት ቤት፣ የሰዶ*ማ*ዊነት ርኩ*ሰት ሥልጠና ለመስጠት ቀጠሮ መያዙን መናገራችንን ተከትሎ፣ በትር ሲበዛበት ከታች ባለው ደብዳቤ "መሠረዙን" ገልጾአል።

ኢትዮጵያ ሌሎች ዐገራት የወደቁበትን የርኩ*ሰት መንገድ፣ የተያያዘችው ይመስላል። ዐሳቡን ወደ አደባባይ ያወጡትና፣ ወዲያው ደግሞ ተውነው ሲሉ ይሰማል። መተዋቸው ለበጣ ይመስለኛል። ምክንያቱም ሲጀመር አይነኬ ነገር የሚነኩት በዐላማና በዕቅድ ነውና።

ትምህርትና አደባባያዊ ወስ*ላታ*ነት የሚገለጠው፣ ከጀርባ የዳበረ ልምምድ ሲኖር ነው!
ተጠንቀቁ!
ተጠበቁ❗️

የቴሌግራም አድራሻ - https://t.me/ebenezertek


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
Fayyisuun kan Waaqayyooti (Yonas 2:9)


ከአንድ ዐይነትነት የመንፈስ አንድነት ይበልጣል።


ዶግማና ቀኖና የማያሳስባቸውና የማያስጨንቃቸው፣ አንድ ላይ ያሉ አንድ ዐይነት “ኅብረቶች” ብዙ ናቸው። የሕይወት ልምምድና የኑሮ ዘይቤ ግድ የማይሰጣቸው፣ በጋራ ግን "መንፈሳዊ የሚመስል ኅብረት" ያላቸው ጀማዎች፣ በዘመናችን እንደ አሸን የፈሉ ናቸው። በአንድ ወቅት ፈሪሳውያንና ሰዱቃውያን ተስማምተው አንድ ኾነው ነበር፣ ቅዱስ ጳውሎስን ለመክሰስ፤ ነገር ግን አንድነታቸው የትንሣኤ ሙታን የዶግማ ጥያቄ ሲነሣ፣ ብትንትናቸው ወጣ፤ “... ይህንም ባለ ጊዜ በፈሪሳውያንና በሰዱቃውያን መካከል ጥል ሆነ ሸንጎውም ተለያየ።” (ሐ.ሥ. 23፥7) እንዲል።


በዘመናችን ካሉ አያሌ ግዳንግድ ዐንድ ዐይነት አንድነቶች መካከል፣ "አንድነታቸው የቆመው" የዶግማና የቀኖና መርኅ ተረግጦ ወይም ገለል ተደርጎ፤ የሕይወት ልምምድና የኑሮ ዘይቤ ተደፍጥጦ ወይም አይነኬ ርዕስ ኾኖ በተከድኖ ይብሰል ተለባብሶና ተድበስብሶ ነው። እንዲህ ባሉ ኅብረቶች መካከል፣ የኢየሱስ ሕይወት፣ ሥራና ትምህርት አይወሩም፤ አይሰበኩም፤ የውይይት ርዕስ አይደሉም። የመጽሐፍ ቅዱስ ሥልጣን የማይነካ ርዕስ ነው፤ ስለ ኀጢአት ማስተማርና መገሰጽ የማይደፈሩ ናቸው።

እንዲህ ባሉ "ኅብረቶች" ውስጥ ያሉ ሰዎች፣ ምልክቶቻቸው ግልጽና ተመሳሳይ ነው። “ለምን ፍቅር ብቻ አትሰብኩም?” [በሚያሳዝን መልኩ እንዲህ የሚል ሰበብ ያቀረበልኝ፣ በግብረ ሰዶማዊነት የታወቀ አንድ አገልጋይ ነበር] “ለምን ፍቅር ብቻ አትሰብኩም?” የሚሉ ኹሉ አመቻማች፣ አንድ አይነቶች ናቸው ማለት ይከብዳል፤ በብዛት ግን ይህን ሰበብ የሚያቀርቡ ሰዎች፣ ዶግማና ቀኖና የማይመቻቸው፣ ተመሳስለው ኗሪ፣ ፊሪሳዊ ግብዝነትን ገንዘብ ያደረጉ፣ ከማንም ጋር መቀያየም የማይሹ፣ እንደ ገበያ ለሻጭም ለገዢም የሚመቹ … ናቸው፡፡

እውነት ለመናገር፣ ደረት እስከ ቀላ ዶግማ መጣል፣ ሆድ እስከ ሞላ ቀኖና መግፋት፣ ኪስ እስከ ረጠበ ትውፊት መርገጥ፣ ኢየሱስንና ትምህርቱን፤ ሥራውንና ሕይወቱን ትቶ … መጐራበትና የአንድ ዐይነተኝነት ጽዋ መጫለጥ … ይዋል ይደር እንጂ እንክርዳድ ማጨድ፤ መምረርና መርከስ የማይቀር ፍሬ ነው፡፡

ቅዱስ ጳውሎስ፣ ክርስቶስን በማመን ስለሚከተሉን ነገሮች ሲናገር፣ “በሰላም ማሰሪያ የመንፈስን አንድነት ለመጠበቅ ትጉ።” (ኤፌ. 4፥3) ይላል፡፡ ማመን አኗኗርን መለወጥ አለበት፤ ወንጌል ተረድተናል ካልን የወንጌል ኑሮና ዘይቤው በሕይወታችን ሊንጸባረቅ ይገባል፡፡ የመንፈስ አንድነት መጠበቂያውና ማጥበቂያው ልጥ፣ በክርስቶስ ኢየሱስ ላይ ያለን ሕያው እምነት ነው፡፡ ክርስቶስን ገለል አድርገን፤ ትምህርቱንና ሥራውን ችላ ብለን የምናመጣው ኅብረትም ኾነ፤ የምናሳየው መንፈሳዊ ተጽዕኖ የለም፡፡

አንድ የኾንነው አንድ ጌታ፣ አንድ ሃይማኖት፣ አንዲት ጥምቀት፣ አንድ አምላክ ስላለንና አንድ አካል ውስጥ በመንፈሱ ስለ ኾንን ነው፡፡ በኒህ ነገሮች ከተከፋፈልን አንድ ላይ ብንኾንም፣ አንድ አይደለንም፡፡ በአገራችን ክርስትናን ካራከሱትን ካንኳሰሱት ነገሮች ቀዳሚው ተርታ ውስጥ የሚመደበው፣ አንድ ዓይነቶች መብዛታቸው ነው፡፡ ወዳጆች ሆይ፤ በክርስቶስ ኢየሱስ ያለውንና ለእኛም በመንፈስ ቅዱስ የተሰጠውን የመንፈስ አንድነት ጠብቁ፤ ለመጠበቅም ትጉ እንጂ አንድ ዐይነትነትን አትመኙ፤ አትጎምጁም!

“ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን በማይጠፋ ፍቅር ለሚወድዱ ሁሉ ጸጋ ይሁን።” (ኤፌ. 6:24) አሜን።


My blog link - http://abenezerteklu.blogspot.com/2025/02/blog-post.html
My Youtube link - www.youtube.com/@-abenezertekludiyakon8842


የእግዚአብሔርን ቃል በትክክልና በጸሎት መንፈስ ማንበብ ታላቅ ብፅዕና ነው!


ይህ ጽሑፍ፣ አንድ ወንድም ፊተኛ መጽሐፌን አንብቦ የሰጠኝ ሰፋ ያለ አስተያየት ነው፤ ምናልባት ለመማማር ይጠቅማል በማለት ከተሰጡ ብዙ አስተያየቶች ይህን መርጫለኹ፤ አንብቡና አስተያየት ስጡበት፤ አስተያየቱ የአስተያየት ሰጪው ወንድም መኾኑን መግለጥ ወዳለኹ፡፡

ይድረስ ለዲያቆን አቤን ኤዘር ተክሉ
የእምነት እንቅስቃሴ የዛሬዪቱ ቤተ ክርስቲያን ፈተና ነው ያሉትን መጻሕፍዎን እያየሁ ነኝ፡፡ መጀመሪያ በርዕስ፣ ቀጥሎም በፍሬ፡፡ በጥሩ እንቅስቃሴ ውስጥ መሆንዎ ይሰማኛል፡፡አንዳንዴም እጅግ ቀላሉንና ፍቺ የማያስፈልገውን ቃል አፌ ታሪካዊ ትምህርት አደርገውት ጎርጎጭ እንዲል እንዳደረጉትም በግል ግንዛቤዬ ታይቶኛል፡፡ እንደ እኔ ላለው ተራ ሕዝብ የማንረዳቸው ቃላት በመጠቀምዎም እኔም ተቸግረበታለሁ፡፡ አዳዲስ ቃላትም ተምሬበታለሁ፡፡ የተቀረውን እንደሚከተለው ልመስክር፡፡
የሐ*ሰት መምህራን ብለው ካቀረቡአቸው አንዳንዶቹ እጅግ የታወቁ ሆኖ ስለማውቃቸው የጋራ ግንዛቤ አለን፡፡ ማስረጃ አሰባሰብዎ እጅግ ጊዜ የፈጀ መሆኑ አያጠራጥርም፡፡ ለስኬት ተነሳሽነትዎ ውስጣዊ ቅናትዎን አሳይቷልና አስደናቂ ነው፣ ተወዳጅም ነው፡፡ የተመሩበት መሪ ሥነ መለኮት ነው፣፡ እርሱ የሰው ጥበብ ፍልስፍናን፣ ወግንና አመክንዮን የተላበሰ ሐ*ሰትን እውነት ለማስመሰልም ኃይል ያለው ነው፡፡ በመጽሐፉ ይዘት ብቻ ነው ምመሰክርና ስለ አስቀሩአቸው የዘመኑ ክፉ እንቅስቃሴዎች ለማንሳት መነሻ አይሆነኝም በስተ ኋላ ላይ የማክለው ይኖረኛል፡፡ እንደርስዎ የሚተጉትን ቢስቱ እንኳ ክፉኛ ከመንቀፍ እጠነቀቃለሁ፡፡ በቸር እመለከታለሁ፡፡ ድርቅ ብለው ክችች በለው አይቀሩምና፡፡ ኦርቶዶክስ ምን ትላለች ከሚል ድምጽ ይልቅ ‹‹እግዚአብሄር እንዲህ ይላል፣›› አዋጭ ነው፡፡ ድንቅ መልሶች የሰጡባቸው ነገሮች ብዙ ናቸውና ማስጠንቀቂያዎ ተነሳሽነትንም ይቀሰቅሳል፡፡ በራስዎ ሂደት እና በእውነት ብርሃን የራስዎን ስህተት ለማስተከሳል አቅም ስላለዎ ቃሉን ከወደዱ ሊመለሱ ለመታረም አይከብዶዎትም፣፡ በጥረትዎ ላይ አድናቆት አለኝ፡፡

በዓላማው ፣ በጌታ የሱስ መድኃኒትነት ማመንን፣ መጽሐፍ ቅዱስ በእግዚአብሄር መንፈስ መጻፉንና፣ በሥላሴዎች ስም የማጥመቅን የጋራ እምነት እንካፈል በሚል Ecumenism (የክርስቲያን ሕብረት) ብሎ ራሱን ፈጥሮ የሰ*የመውን አያውቁትምን? ፡፡ እነዚህ ሦስት ቃሎች ለሕብረቱ በጋራ የተያዘው የመግባቢያ ነጥብ ሽፋን ነው፡፡ ዋናው ስኬቱ ቤተ ክርስቲያንን ከክርስቶስ በላይ ማውጣት ነው፡፡ ሕገ እግዚአብሄርን መርገጥ ነው፡፡ የልተቀደሰውን በመቀደስ መር*ገምን መፍጠር ነው፡፡ እግዚአብሄር እንዲህ ይላል በቤተ ክርስቲያን እንዲህ ትላለች ለመተካትና፣ የመንግስትና የቤተ ክርስቲያን ቅልቅልነት በሚፈጠረው አቅም ጻድቃንን ለመሳደድ ነው፡፡ ይህ ዋና ነገር እርስዎ በቅናት ማስጠንቀቂያ ከሰጡባቸው የሐሰት መምህራን ሲተያይ በእጅጉ አይተልቅምን? እዚህ ላይ የቀደመ ትጋትዎን ይቀጥሉበት፡፡ የህብረቱ ውጤት ግን ኤርሚ 8፡11 እና 1ተሰሎንቄ 5፡ 3 ወደ መፍጠር መጥቶ የዓለምን ዕድሜ አሳጥሮ፣ ሃሳባቸውንም ገለብጦ ያከስማል፡፡፡
የህብረቱ አባል ዋና ቤተ ክርስቲያናት ዝርዝር እነሆ!
ክርስቶስ አልባውን ሕብረት
የወገኑ ማህበርተኞች
1. Old Catholic churches
2. Orthodox church {eastern}
3. Orthodox church {oriental}
4. Pentecostal churches
5. Reformed churches
6. Seventh Adventist church
7. The Assyrian church
8. The Salvation Army
9. The {Roman} Catholic church
10. United and Uniting churches.
{Source www.oikoumene.org/ church families

ከነዚህ ውስጥ ነው ክርስቶስ ልጆቹን አበጥሮ የሚያጣቸውና መጥቶም የሞቱትን አስነስቶ በሕይወት ያሉትን በዐይን- ውልብታ ፍጥነት ለውጦ ወደ አብ የሚወስዳቸው ብዬ አምናለሁ፡፡ቲዎሎጂዎን ወደጎን አድርገው መጽሐፍ ቅዱስን ብቻ ቢያነቡ ብዙ ነገር ያመጡልናል ብዬ አምናለሁ፡፡ አይሆንምን? በየቤተ ክርስቲያኑ ርኩ*ስና ርኩ*ሰት ገብቷል፣ አለ፡፡ ከላይ በተዘረዘረው በማህበሩ ካሉቱ ባለ10 አባላት ቤተ ክርስቲያናት ሕብረት ወገኞች በየቤተ ክርስቲያናቱ ጻድቃን ቅሬታዎች ይኖሩ ይሆናል፡ ምክንያቱም ክርስቶስ ‹‹ከዚህ ያልሆኑ በጎች አሉኝ፣ ሂጄ ላመጣቸው ይገባኛል፣ ያለበት ቦታ ስላለ፣ ርኩሱ የበዛ ይሆናል፡፡አሉምም፡፡ በጅምላ በቤተ ክርስቲያን ድርጅት ስም ፍርድ የለምና፣ በስምም መዳን የለምና፣ መመኪያም አይሆንም፡፡ ከጅምላ ፍርድ ይልቅ ስሁቱ ላይ ጠቁሞ ማስተማር ተገቢ ይሆናልን አምናለሁ፣ ለምን ቢባል የፍቅር ጥሪ ነው፤ ተመለስ ማለትም ስለሚሆን፡፡ ለዚሁም እንደ ቤሪያ ሰዎች ቃሉን በቡድን ማጥናት የሚሻል እየመሰለኝ ነው፡፡ ከዚያ የአሸናፊ ቤተ ክርስቲያንን አባሎች ከተበተኑበት በጥበብ ሠርቶ የሚያሰባስብ ድርጅት የክርስቶስ መዝገብ ይሆናል እንበል እንጂ፣ ሕገ እግዚአብሄር ጠሎችንና ከክርስቶስ በላይ ራስዋን የምታስቀምጠውን ክርስቶስ አልባ ቤተ ክርስቲያንን ለማቆም አሥርቱን አሰባስቦና መሥርቶ አንድ ድርጅት ካደረገ በኋላ አለመሆኑን ከወዲሁ እናስብ፡፡ አብዛኛዎቻቸው ለግብረ-ሰዶማውያን መብት ለመፍጠር የሚረዱ፣ሴትን የሚያቀስሱ፣ ክርስቶስ አልባ ሕብረትን (Unity at any cost፣ በምንም ሁኔታ ሕብረቱን አምጣ) እያሉ የካ*ዱ ናቸው፡፡ ሌሎቹ በዝምታ ብቻ ይመለከታሉ፡፡ እነዚህ ናቸው የክርስቶስ ቤተ ክርስቲያንን የሚያዋቅረቱ? ሰይጣን አስርቱን የሚሰባስበው እነርሱ ቅዱሳንን ካሳደዱለትና ካጠፉ በኋላ፣ እርሱ ተመልሶ እነርሱንም እርስ በርስ ሊያነካክታቸው ፣ (በአንድነት ሊወቃቸውም) ነው የሚል ድምዳሜን የያዘ፣ (እርስዎ ላይቀበሉኝ ይችላሉ) መሆኑን ከከዳንኤልና ከራዕይ ትንቢትም አጥንቻለሁ፡፡ ጉዞው የት እንደሚያበቃ ላሳይ በዚሁ አጋጣሚ ይህን ለማከል አሳሰበኝ፡፡ በዚህ ላይ የጥናትዎን ውጤት ለመስማትም እናፍቃለሁኝ፡፡
በሁላችንም ብርሃኑን በልባችን ያግባው፡፡ እርሱ የራሱን ያውቃል ብለን ይበልጥ ታታሪ በመሆን ክርስቶስ መሰል ባህርይን ብንራብና ብንጠማ፣ ቅድስናን በቅጥልፍና በየዕለቱከፍ ብናደርግና ውብ የክርስቶስን አርአያነት ብንከተል ይህ አይበልጥብንምን? ባለንበት እንበርታ፡፡

እውነት ታሰባስበናለች ክርስቶስ እውነትም መንገድም ነውና፡፡ ከክርስቶስ ወዲያ የማንም ቤተ ክርስቲያን ስም መመኪያ አይሁነን፣ ለምድርና ለወንጌል ብለን እያየን ልንጠራበት ያህል ይሁን፡፡ ለሰማይ ግን ሙያ በልብ ይሁን፣ ቃሉን እንያዝ፣፡ የመጽሐፍ ቅዱስ መልዕክት ብቻ አበጥረን እንወቅና እንቀበል፡፡ አጥፊን ማጋለጡ ስሁታንንም ጻድቃንንም ለመታደግ ነው መባሉ ተገቢ ነው፡፡ በጥረትዎ ይትጉልኝ፡፡ አንድ ዜጋ ያድርገን፡፡ ለዚሁ መንገዱን ያሳየን ዘንድ ከልብ እጸልያለሁ፡፡

My telegram Link - https://t.me/ebenezertek


ዛሬ ጌታ ሥላሴ፣ ለእኔ በመግቦቱ ወደዚህ ምድር እንድመጣ የፈቀደበትና ደግሞም “ኑር!” ብሎ ዘመን የጨመረልኝ ቀን ነው! በአጭሩ የልደት ቀኔ ነው!
ከዘመኔ የሚበልጠውን ከጌታ ጋር አልኖርኹትም፤ የሚበዛው ዘመኔ ያለመታዘዝና ለርሱ ያለ መሰበር ነው፤ ያ ለርሱ ባለመሰበር የኖርኹበት ዘመኔ እጅግ ይጸጽተኛል፤ ዛሬ ግን በጌታ ክርስቶስ ኢየሱስ ጉብኝትና ምጋቤ “ሎሌና ባሪያው ኹኜለት” እያገለገልኹት ነው! ክብር ይግባው! አሜን!
ወደፊት ከምኖረው ዓመታቴ ይልቅ የኖርኩበት የሚበልጥ ይመስለኛል፡፡ እናም በጌታ ቸርነትና መግቦት ቀሪ ዘመኔ፣ ከጌታ ጋር ብቻ ለመኖር እጨክናለኹ! ጌታ ደግሞ በርሱ የተደፉትን በታሪክ ሲጥል አላውቀውምና፣ አዲስ ዐመሉን በእኔ አይጀምርም! ጌታ ኢየሱስ የራሱ የኾኑትን ያውቃል! የዘመናትና የታሪክ ባለቤት የኾንኸው ልዑል ሆይ፤ በጨመርክልኝ ጊዜ ላንተ ብቻ ኖሬ ማለፍን ስጠን፤ አሜን፡፡

My telegram link - https://t.me/ebenezertek

951 0 0 21 54

የክርስትና ባላንጣ የነበረውን የሮም ቄሳርን በአፍ ጢሙ ወደ ደፋውና በሐዋርያት ሥራ ወደሚታየው አዲስ ኪዳን መመለስ ያሻናል!


ለእኔ ጌታ ኢየሱስን ማገልገል ዕዳ አይደለም፤ ስለ ወደደኝ ምናልባት ጥቂት ካረካው ብዬ እንጂ። ርሱ የማንም ባለዕዳ አይደለም!


እንደ ትዝታው ሳሙኤል ያሉ ሰዎች ግን እንደዘበነ ለማ፣ እንደምሕረተ አብና ሄኖክ ... ላሉ ሰዎች በትክክል እንዲድኑ፤ በፍቅርና በመራራት ስሞቻቸውን ጠርተው በጌታ ፊት ይማልዱላቸዋል?


ወደ አዲስ ኪዳናዊ የመመለስ ተሐድሶ ያስፈልገናል!

ከዚህ ቀደም የጻፍኹትን ልጥቀስ፣

“ተሐድሶ፣ “ሐደሰ” ከሚለው የግዕዝ ቃል የወጣ ሲኾን፣ ትርጕሙ “አዲስ አደረገ” የሚለውን ትርጕም ታሳቢ ያደርጋል። በተገብሮ (Passive) “ተሐድሰ” ከሚለው ቃል ደግሞ፣ “ተሐድሶ” የወጣ ሲኾን፣ ትርጕሙ “አዲስ ኾነ” ማለት ነው። ስለዚህም ስያሜው ድርጊትን እንጂ ተቋማዊነትን ወይም አደረጃጀትን ፈጽሞ አያመለክትም።” [1]

ወደ ርዕሳችን ስንመለስ፣ ወደ አዲስ ኪዳናዊ የመመለስ ተሐድሶ ማለት፣ በጌታችንና በቅዱሳን ሐዋርያት ወደ ተሰጡት ትምህርቶች፣ ወደ ተኖሩ ልምምዶችና ትውፊቶች በመመለስና ብሎም አሠረ ፍኖታቸውን በመከተል እውነተኛ የሕይወትና የኑሮ ተሐድሶ ማምጣት የሚል ፅንሰ ዐሳብ በውስጡ የያዘ ነው። ይህ የሚኾንበት ዋነኛ ምክንያቱ፣ ቤተ ክርስቲያን በተለያዩ ዘመናት፤ በተለያዩ ታሪኮችና በተለያዩ ኹኔታዎች ውስጥ በማለፍዋ ምክንያት፣ ለተለያዩ እንግዳ ትምህርቶችና ልምምዶች ልትጋለጥ ትችላለች ወይም ተጋልጣ ታይታለች።
በአዲስ ኪዳን ምንባባት ውስጥ ጌታችን ኢየሱስ፣

“ከፈሪሳውያንና ከሰዱቃውያን እርሾ ተጠንቀቁና ተጠበቁ” (ማቴ. 16፥6)፣ “ምን ወይም እንዴት እንድትሰሙ ተጠበቁ።” (ማር. 4፥24፤ ሉቃ. 8፥18)

እንዲሁም ቅዱስ ጳውሎስ፣

“በገዛ ደሙ የዋጃትን የእግዚአብሔርን ቤተ ክርስቲያን ትጠብቁአት ዘንድ መንፈስ ቅዱስ እናንተን ጳጳሳት አድርጎ ለሾመባት ለመንጋው ሁሉና ለራሳችሁ ተጠንቀቁ። ከሄድሁ በኋላ ለመንጋው የማይራሩ ጨካኞች ተኩላዎች እንዲገቡባችሁ፥ ደቀ መዛሙርትንም ወደ ኋላቸው ይስቡ ዘንድ ጠማማ ነገርን የሚናገሩ ሰዎች በመካከላችሁ እንዲነሡ እኔ አውቃለሁ።” (ሐ.ሥ. 20፥28-30)

ብለው ሲናገሩ፣ ቤተ ክርስቲያን ባለመጠንቀቅዋ ምክንያት ለተለያዩ እንግዳና ልዩ ልዩ ትምህርቶች ልትጋለጥ እንደምትችል አመልካች ናቸው።

ለዚህም ነው ለተለያዩ እንግዳና ልዩ ልዩ ትምህርቶች ከተጋለጡት አብያተ ክርስቲያናት መካከል ገላትያን እንዲህ በማለት ቅዱስ ጳውሎስ የሚናገረው፤

“በክርስቶስ ጸጋ የጠራችሁን እርሱን ትታችሁ፣ ወደ ተለየ ወንጌል እንዲህ ፈጥናችሁ መዞራችሁ ደንቆኛል፤ እንደ እውነቱ ከሆነ ሌላ ወንጌል የለም። የሚያደነጋግሯችሁና የክርስቶስን ወንጌል ለማጣመም ጥረት የሚያደርጉ አንዳንድ ሰዎች አሉ።” (ገላ. 1፥6-7 ዐመት)።
በዚህ ክፍል ላይ የገላትያ ቤተ ክርስቲያን እንዲህ ባለ ውድቀት ውስጥ መግባትዋን እናስተውላለን። ብዙዎች እንዲህ ስንናገር፣ “ቤተ ክርስቲያን አትሳሳትም፤ ሰዎች እንጂ” የሚል አቋም ያንጸባርቃሉ። ይህን በሌላ ርዕስ እመለስበታለሁ።

ወደ አዲስ ኪዳናዊ የመመለስ ተሐድሶ፣ እውነት ኾኖ በብዙዎች ልብ ያለ ቢኾንም፣ ነገር ግን ለመቀበልና ለመተግበር ብዙዎች ፈቃደኞች የኾኑ አይመስሉም። እንዲያውም፣ ተሐድሶ ሲባል በብዙዎች ልብ ያለው፣ “ኦርቶዶክስን ወደ ወንጌላውያን የመውሰድ ወይም ፕሮቴስታንት የማድረግ ዝንባሌ” እንደ ኾነ ተደርጐ ሲወሰድ ይስተዋላል፤ በርግጥ ይህ ስህተት አልተፈጸመም ማለት አይቻልም። ነገር ግን እውነተኛውና ወደ አዲስ ኪዳናዊ ወይም ወደ ቅዱሳት መጻሕፍት የመመለስ ተሐድሶ፣ ተቋም የመለወጥ አልያም ስፍራ የማቀያየር ተግባር ነው ማለት አንደፍርም።

የዛሬዋ ቤተ ክርስቲያን፣ ባለፉት ኹለት ሺህ አመታት አልፋ በመጣችባቸው ልዩ ልዩ ጎዳናዎች፣ ወድቃም፤ ተሳስታም አሳስታም ኖራ፣ ነገር ግን በጌታ ምሕረትና ጥበቃ፤ በትድግናውና በሉዓላዊ መግቦቱ ግን እስከ አኹን አለች። ስለዚህ ባለፉት ዘመናት በውስጧ የገቡና የሰረጉ፤ በዘመን ርዝመት እውነት የመሰሉ አያሌ ስህተቶችና እንከኖችን አስወግዳ፣ ስትመሠረት በነበረችውና ለመሲሑ ቃልና ሕይወት፤ ትምህርትና ልምምድ በመገዛት በቄሣርና በአላውያን ነገሥታት ፊት ተፈርታና ታፍራ እንደ ነበረችው ቤተ ክርስቲያን ትኾን ዘንድ መመለስ ያስፈልጋታል ብለን እናምናለን። ስለዚህም ደፍረን በዛሬዋ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ የክርስቶስ የኾነው ኹሉ ይንጸባረቅ ዘንድ እንመለስ እንላለን!

በአጭር ቃል፣ የክርስቶስ ሕይወት ሕይወታችን፤ ኑሮው ኑሮአችን፤ ትምህርቱ ትምህርታችን፤ ልምምዱ ልምምዳችን፤ ሥራው ሥራችን ኾኖልን፤ ቅዱሳት መጻሕፍት እንደሚሉን በመመለስና ርሱን በመከተል ሕይወት በመኖር የመንፈሳዊ እውነተኛ የሕይወት ተሐድሶ እናመጣ ዘንድ ወደ አዲስ ኪዳናዊ የመመለስ ተሐድሶን በእውነት እንድርግ እንላለን!
[1] http://abenezerteklu.blogspot.com/2021/09/blog-post_29.html

My blog link - http://abenezerteklu.blogspot.com/2025/01/blog-post_31.html


ተሐድሶ የቀደመውንና የተቀበረውን የጌታና የሐዋርያትን ትምህርት ማውጣትና ማሳየት እንጂ፣ አዲስ ትምህርት ማስተማር አይደለም።


አስተርዕዮ መንፈስ ቅዱስ፣ ወደ አብ ልጅ ወደ ክርስቶስ ያደርሳል። "አስተርዕዮ ማርያም" ግን ከታቦት ንግሥ በቀር ሌላ ምን ትርፍ አለው?! ወደ ክርስቶስ አለመድረስ አለመታደል ነው!


ጤናማና ትክክለኛ የቤተክርስቲያን መሪ ስትኾን እንዲህ ታስባለህ፤ ትጨነቃለህም።
በCordova ግዛት የTrinity Baptist Church ቄስ ወይም መጋቢ የኾነው  Matt Crawford እንዲህ ይላል፦

" ... ቤተክርስቲያን ለሰዎች የእምነት ቦታ ከአምላካቸው ጋር በጋራ በአምልኮ የሚያሳልፉባት ቦታ መኾንዋ ቀርቶ፣ በአዲሱ የአሜሪካ መንግሥት አስተዳደር ወረራ እየተደረገባትና የመኖሪያ ፈቃድ የሌላቸውና የአገሪቱን የኢሚግሬሽን መሥሪያ ቤት ውሳኔ እየተጠባበቁ ያሉትን ሰዎች ማፈሻ ቦታ ኾናለች። እኔም የቤተክርስቲያን መሪ እንደ መኾኔ፣ ልቤን ክፉኛ አስጨንቆታል። የወሰድኩትን ትንሽ የእረፍት ጊዜ በአግባቡ እንዳልጠቀም አእምሮዬን እረፍት ነስቶታል። ለእነዚህ በአገራቸው በሰላምና በመልካም ኹኔታ መኖር አቅቷቸው ወይም የተሻለ ኑሮ ለልጆቻቸው ፍለጋ ለተሰደዱትና በፍርሃት ላሉት አምላኬን እለምናለሁ። ብርቱ ጸሎት ያሻናል።
እኔም ስደተኛ ነኝ። ..."

“በስደተኛው ግፍ አታድርጉ፤ እናንተ በግብፅ ምድር ስደተኞች ስለ ነበራችሁ የስደተኛ ነፍስ እንዴት እንደ ሆነች አውቃችኋልና።”(ዘጸ. 23፥9)

“እኔ እግዚአብሔር አምላካችሁ ነኝና ለመጻተኛና ለአገር ልጅ አንድ ዓይነት ሕግ ይሁንላችሁ።”(ዘሌዋ. 24፥22)

ይህን የተገለጠ ቅዱስ ቃል፣ ኹል ጊዜ ዓለማውያንና አረማውያን ከሚሠሩት የግፍ ሥራ ጋራ "ሰባኪና አገልጋይ ነን" የሚሉ ሰዎች ሲተባበሩ ሳይ፤ ጨውነትና ብርሃንነትን ሲሸሽጉ ስመለከት እተክዛለኹ፤ እጨነቃለኹ።

ይህ ወንድማችን ግን እጅግ የተወደደ ነው። ከግፉአን ጎን በመቆም ብርሃንነቱን ገልጦአል። ጌታ አብዜቶ ይባርከው።

ጌታ ሆይ የክፋት ቀናትን አሳጥርልን፤ አሜን። (የቄሱን ሙሉ መልእክት - https://churchleaders.com/news/)

የቴሌግራም አድራሻ - https://t.me/ebenezertek


Video oldindan ko‘rish uchun mavjud emas
Telegram'da ko‘rish
ድኻ ጠሉ በጋሻው ደሳለኝ!

"የድኾችን ጩኸት ለመስማት ፈቃደኛ ያልሆነ ሰው እርሱም ተቸግሮ በሚጮኽበት ጊዜ የሚረዳው አያገኝም።" (ምሳ. 21፥13)

በተቸገርን ጊዜ እግዚአብሔር አምላክ ጸሎታችንን ይሰማን ዘንድ፣ የወገኖቻችንን ችግር በመስማት በፍቅር ልንደርስላቸው ይገባል። ጌታችን ኢየሱስ የታረዘውን ስናለብስ ርሱን እንዳለበስን እንደሚቆጥር በግልጥ ተናግሮአል፤ (ማቴ. 25፥40)። በአዲስ ኪዳን የጥበብ መጽሐፍም እንዲህ ይላል፣ “የእግዚአብሔር ፍርድ ምሕረት ለማያደርግ ሰው ምሕረት አያደርግም፤ ሆኖም ምሕረት ፍርድን ያሸንፋል።”(ያዕ. 2፥13)።

እግዚአብሔር ምሕረት የሚያደርገው፣ ለሚምሩና ለሚራሩ ነው። የሚምሩ ምስጉኖች ናቸው ፍጹም ይማራሉና እንዲል። ስለ ድኾች የጌታ ትምህርት አጭርና ግልጽ ነው። ለኹል ጊዜ ከእኛ ጋር አብረውን እንዳሉ፤ ደግሞም ይኖራሉ።“ድሆችስ ሁልጊዜ ከእናንተ ጋር ይኖራሉና”(ዮሐ. 12፥8) እንዲል። ድኾች ቤት ፈርሶባቸው ቢጮኹና ቢያለቅሱ ቅንጦት ወይም አዚም ተደርጎባቸው አይደለም። አልያ ድኾች መሻሻል የሚጠሉ፤ ድህነት ወይም ችጋር ወይም ሰቆቃ እንደ ዕጣ ፈንታ የተጣባቸው አይደሉም። ማንም ልማት የሚጠላ ጤነኛ ሰው የለም፤ ቁስ ግን የቱንም ያህል ቢጌጥና ቢያምር፣ ሰውን ካልጠቀመ፤ ለእግዚአብሔር ክብር ካልኾነ፤ ከንቱ የከንቱ ከንቱ ነው!

ስለ አንዳንድ "ወንጌላውያን" ነን ስለሚሉ አገልጋዮች አዝናለኹ። ከኦርቶዶክስ ያልተማሩ "አዚማሞች" ናቸው። ትላንት ኦርቶዶክስ መንግሥትን ተጠግታ የሠራችውን ስህተት እነርሱ ዛሬ በአደባባይ በብዙ ማስረጃ ፊት ይፈጽሙታል። ለምን መከራ ታጎመሩልናላችኹ? እንደ ከረመ ወይን ለምን መከራ ታሰነብቱልናችሁ? ለተጣለላችኹ ቅልጥም እዚያው ለፍልፉ እንጂ በወንጌል ታክካችኹ መጥታችኹ ወንጌሉን በማያምኑ ዘንድ አታሰድቡ፤ ለደካሞችም የማሰናከያ ዐለት አታኑሩ!

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.