የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከታህሳስ 1 ጀምሮ እንደሚሰጥ ተገለፀ!
በድሬደዋ አስተዳደር የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከታህሳስ 1 እስከ 3 መሰጠት እንደሚጀመር የድሬደዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሙሉካ መሀመድ ገልጸዋል።
በዚህም 7113 ተማሪዎች የ45 ቀን የክለሳ ትምህርት ተሰቷቸው በ 90 ትምህርት ቤቶች 289 የመፈተኛ ክፍሎች ውስጥ በአንድ ክፍል 40 ተማሪዎች እንደሚፈተኑ ኃላፊዋ ገልፀዋል፡፡
ፈተናው የ7ኛ ክፍል ሙሉ ይዘት እና የ8ኛ ክፍል የግማሽ አመቱን ይዘት እንደሚያጠቃል የተገለጸ ሲሆን ተማሪዎች በፈተናው ምንም አይነት መረበሽ እንደሌለባቸውም በመጠቆም ወላጆች ልጆቻቸውን ለፈተናው በበቂ ሁኔታ ዝግጁ እንዲሆኑ የስነ-ልቦና ምክር እንዲመክሩም ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡
(የድሬደዋ አስተዳደር ኮሚውኒኬሽን ቢሮ)
@ebs_official @ebs_official
በድሬደዋ አስተዳደር የ8ኛ ክፍል ክልላዊ ፈተና ከታህሳስ 1 እስከ 3 መሰጠት እንደሚጀመር የድሬደዋ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ወ/ሮ ሙሉካ መሀመድ ገልጸዋል።
በዚህም 7113 ተማሪዎች የ45 ቀን የክለሳ ትምህርት ተሰቷቸው በ 90 ትምህርት ቤቶች 289 የመፈተኛ ክፍሎች ውስጥ በአንድ ክፍል 40 ተማሪዎች እንደሚፈተኑ ኃላፊዋ ገልፀዋል፡፡
ፈተናው የ7ኛ ክፍል ሙሉ ይዘት እና የ8ኛ ክፍል የግማሽ አመቱን ይዘት እንደሚያጠቃል የተገለጸ ሲሆን ተማሪዎች በፈተናው ምንም አይነት መረበሽ እንደሌለባቸውም በመጠቆም ወላጆች ልጆቻቸውን ለፈተናው በበቂ ሁኔታ ዝግጁ እንዲሆኑ የስነ-ልቦና ምክር እንዲመክሩም ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡
(የድሬደዋ አስተዳደር ኮሚውኒኬሽን ቢሮ)
@ebs_official @ebs_official