ኦርቶዶክስ ተዋህዶ️


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


ይህ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ትምህርቶች መዝሙራት ቅዱሳት ሥዕላትን እንዲሁም ሌሎችን ምናጋራበት መንፈሳዊ ቻናል ነው።
👉"የአባቶቼን ርስት አልሰጥም"👈
ለማንኛውም አስተያየት @jermi123
ይጠቀሙ

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


✝እንኳን አደረሰነ!

☞ወርኀ የካቲት ቡሩክ፥ አመ ፳ወ፱

✝ጾም ዐቢይ ዘመድኅን ክርስቶስ (አምላክነ)
✝ወተዝካረ በዓሉ ለክርስቶስ እግዚእነ (ስቡሕ ወውዱስ)

✞ወበዓለ ቅዱሳን አበው፦

✿ፍቅርተ ክርስቶስ/እማ ምዑዝ (ጻድቅት፥ ወሰማዕት)
✿ደናግል ንጹሐት (ማኅበራኒሃ)
❀ዘርዓ ክርስቶስ ሰማዕት (ምታ)
❀ገብርኤል መነኮስ
❀ዘመለኮት ጳጳስ
✿ቢላካርዮስ አረጋዊ (ጳጳስ ወሰማዕት)

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡
https://t.me/enabib


እንኳን ለኢትዮጵያዊቷ ቅድስት ክብርት እናታችን ፍቅርተ ክርስቶስ ለቅዱስ ዘርዐ ክርስቶስ ለቅዱሱ ህጻን በዓል በሠላም አደረሳችሁ!!!


"ምንጮች እንዳይደርቁ ጉባኤ ቤቶችን እንገንባ" በሚል መሪ ቃል የምክክርና የውይይት መርሐ ግብር ተካሄደ !

የካቲት 28 ቀን 2017 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ]

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሰንበት ትምህርት ቤቶች ማደራጃና መምሪያ ማኅበረ ቅዱሳን የባሕር ዳር ማዕከል ከባሕር ዳርና ሰሜን ጎጃም አኅጉረ ስብከት ጋራ በመተባበር የአብነት ጉባኤ ቤቶች ልዩ የምክክርና የውይይት መርሐ ግብር ከየካቲት 26 እስከ 27 ቀን 2017 ዓ.ም ማካሔዱን ገልጿል፡፡

በጉባኤው የባሕር ዳርና የሰሜን ጎጃም አኅጉረ ስብከቶች ፣ የወረዳ ቤተ ክህነት ሥራ አስኪያጆች፣ የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች፣ የሰበካ ጉባኤ ተወካዮች፣ የአብነት ጉባኤ ቤት መምህራን ተወካዮችና ከ130 በላይ ተሳታፊዎች የተገኙ ሲሆን ፤ የባሕር ዳር ማዕከል ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አይሸሹም የኔው የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት ያስተላለፉ ሲሆን በጉባኤው መክፈቻ መርሐ ግብር ክቡር መልአከ ሰላም ኤፍሬም ሙሉዓለም የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ዋና ሥራ አስኪያጅ ተገኝተው መልእክት አስተላልፈዋል፡፡ በመልእክታቸውም ጉባኤ ቤቶች መሠረቶቻችን መሆናቸውን አንስተው “ሁላችንም በጉባኤ ቤቶቻችን ላይ በትኩረት ልንሠራ ይገባል” ብለዋል፡፡

በመርሐ ግብሩ የአብነት ት/ቤቶችን የሚመለከት ዳሰሳዊ ጽሑፍ በዲ/ን ግሩም መሠረትና የአብነት ት/ቤቶች ሚና ትናንት ፣ ዛሬና ነገ የሚል ጽሑፍ በመ/ር አስተርአየ ገላው ቀርበው ሰፊ ዉይይት የተደረገባቸው ሲሆን በውይይቱም የተለያዩ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ቀርበው የቀጣይ አቅጣጫዎች ተቀምጠዋል፡፡

በዝግጅቱ የግብጽ ኮፕቲክ ቤተ ክርስቲያን ተሞክሮ በመ/ር ኃይለማርያም ዘውዱና የአብነት ት/ቤቶችን አስተዳደር ለማዘመን የተዘጋጀው የመረጃ ቋት መተግበሪያ የባሕር ዳር ዩኒቨርሲቲ የሶፍትዌር ባለሙያ ፣ የገዳማትና መንፈሳዊ ት/ቤቶች አገልግሎት ዋና ክፍል አባል በሆኑት ወንድም ጌትነት መቅረቡ ተጠቁሟል።

በጉባኤው የመፍትሔ ሐሳቦችን የሚያመላክት አጭር መነሻ ሐሳብ በዲ/ን አዲሱ ሙሉጌታ በማንሳት በቡድን በውይይቱ የተደረገ ሲሆን የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት የትምህርት መምሪያ ኃላፊ ሊቀ ጉባዔ ሙሉጌታና የሰሜን ጎጃም ሀገረ ስብከት ትምህርት ክፍል ኃላፊ መ/ገነት መልአከ የማጠቃለያ ሃሳብ ሰጥተዋል፡፡

ከሰሜን ጎጃም ሀገረ ስብከት ተወክለው የተገኙት መልአከ ምሕረት ግሩም አለነ የሰሜን ጎጃም ሀገረ ስብከት ስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ አገልግሎት ክፍል ኃላፊ ጉባኤውን ያዘጋጀውን ማዕከሉን አመስግነው ሁሉም የቤተ ክርስቲያን አስተዳደራዊ መዋቅር ለጉባኤ ቤቶች ልዩ ትኩረት መስጠት እንደሚገባ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል፡፡

በመጨረሻም ጉባኤውን በተመለከተና በቀጣይ ከባለ ድርሻ አካላት ጋር መሥራት በሚቻልባቸዉ ጉዳዮች  ዙሪያ የማኅበሩን አቅጣጫዎች የማአከሉ ጽ/ቤት ኃላፊ በሆኑት አቶ አይሸሹም የኔው ቀርበው መርሐ ግብሩ ተጠናቋል፡፡

©ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማዕከል


በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤትና በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ባሉት አስተዳደራዊ ጕዳዮች ላይ የተቋቋመው አጣሪ ኮሚቴ መግለጫ ሰጠ !

የካቲት 27 ቀን 2017 ዓ.ም [ተ.ሚ.ማ/ አዲስ አበባ]

በቅዱስ ሲኖዶስ ጥቅምት 19 ቀን 2017 ዓ.ም  በዋለው ምልዓተ ጉባኤ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤትና በአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ባሉት አስተዳደራዊ ጉዳዮች ላይ የተቋቋመው አጣሪ ኮሚቴ ከተቋቋመበት ማግስት ጀምሮ የቅዱስ ሲኖዶስን መመሪያ መሠረት በማድረግ አያሌ ተግባራትን ሲያከናውን መቆየቱን በመግለጽ ለኢኦተቤ ቴቪ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ 

መግለጫው በሦስት ክፍል ተከፍሎ የቀረበ ሲሆን የዚህ የማጣራት ሥራው በጥቅምቱ ቅዱስ ሲኖዶስ በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽ/ቤት ጀምሮ የቤቶችና ሕንጻዎች አስተዳደር ልማት ድርጅትን አካትቶ ፣ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ጽ/ቤት እና በሥሩ ያሉ አድባራትና ገዳማት ላይ ያለውን የአሠራር ክፍተት የመጨረሻ እልባት እንዲሰጥ ያስችል ዘንድ የቀረቡ ጕዳዮች ያላቸውን አግባብነት መመልከት ሲሆን በዋነኝነት ግን የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን አስተዳደራዊና መዋቅራዊ ችግሮቿን መፍታት ስለሆነ ታላቅ ጥንቃቄ የሚያስፈልገው መሆኑ ታምኖበታል፡፡

በዚህም መሠረት አጣሪ ኮሚቴው፦

በክፍል አንድ

1. አጣሪ ኮሚቴው አዘጋጅቶ በአጸደቀው የሥራ መመሪያ መሠረት ጽ/ቤት አዋቅሮ እና የጽ/ቤት ሥራ አስፈጻሚዎችን መድቧል፡፡

2. መደበኛ የስብሰባ ጊዜያትን ወስኗል፣ የኮሚቴውን የሥራ ማጣቀሻ ዝርዝር እቅድ እና የሥራ መመሪያውን አዘጋጅቶ በቋሚ ሲኖዶስ በማጸደቅ ለማጣራት ሥራው አስፈላጊ የሆኑትን ቅድመ ዝግጅቶች በማሟላት ወደ ሥራ ገብቷል፡፡

3. በቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ውሳኔ መሠረት የማጣራት ሥራ የሚካሔድባቸው ተቋማትን በመለየትና ሊመለከታቸው በሚገባው ጕዳዮች ዙሪያ ጥልቅ ምልከታ በማድረግ የቅድመ ዝግጅት ሥራውን አጠናቋል።

4. የማጣራት ሥራው የታለመለትን ውጤት በማምጣት ረገድ ያለውን ችግር ነቅሶ በማውጣትና ለቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን ዘላቂ መፍትሔ ለማምጣት አስተዳደራዊ የሥራ ዘርፎችን አይቷል፡፡

5. በጥናት ተለይተው ለተቀመጡት አምስት የሥራ ዘርፎች በእያንዳንዳቸው የዘርፏን ሞያ መሠረት ባደረገ መልኩ ድጋፍ ሰጭ ባለሞያዎችን አቋቁሞ የጋራ ግንዛቤ በመፍጠር ሥራ አስጀምሯል፡፡

6. በማጣራት ሂደቱ የሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላትን የማሳተፍ ቅድመ ሁኔታዎችን በመለየት እና የሥራ ዝርዝር በማዘጋጀት በቋሚ ሲኖዶስ መመሪያ ሰጭነት የቅሬታ መረጃዎችን እና ማስረጃዎችን በተለያዩ የመረጃ መስጫ ዘዴዎች ለማቅረብ እንዲቻል በቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት መደበኛ ቢሮ በመክፈትና ቋሚ ሠራተኞችን በመመደብ ሥራውን እያከናወነ ይገኛል።

በክፍል ሁለት

1. በአጣሪ ኮሚቴውና የየዘርፉ ድጋፍ ሰጭ ባለሞያዎች ጋር የሥራ ዝርዝር እቅድ መሠረት ኮሚቴው በቀጣይ ከሚመለከታቸው የአስተዳዳራር አካላት ጋር የገጽ ለገጽ ማስረጃ የማረጋጋጥ እና ለማጣራት ሥራው አስፈላጊ በሆኑ ጉዳዮች ላይ ውደደት የማካሄድ ሥራ ያከናውናል።
2. ቅሬታዎችን የመስማትና የቅሬታ ሰነዶችን የመቀበል ይፋዊ ሥራውን የጀመረ በመሆኑ አስፈላጊ በሆኑ እና መፍትሔ በሚሹ ጕዳዮች ላይ ሁሉ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ልጆች አና ከማጣራት ሥራው ጋር በተያያዘ ለሚቀርቡ መረጃዎች እና ማስረጃዎች በሩ ክፍት መሆኑን ያስታውቃል፡፡

3. አጣሪ ኮሚቴውና ከየዘርፉ ድጋፍ ሰጭ ባለሞያዎች ጋር በሚኖረው የገጽ ለገጽ ውይይት፣ የሰነዶች ምርመራ እና ማስረጃዎች የማጣራት ሥራ ማብራሪያ እና ምላሽ በሚፈልግበት አግባብ በድጋሚ ጕዳዩ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር መረጃውን የማረጋገጥ ሥራ ያከናውናል፡፡

በክፍል ሦስት

1. በገጽ ለገጽ ውይይቶች፣ በመረጃ ማሰባሰብ እና ማጠናቀር ሂደቶች እንዲሁም አሁን እየተከናወኑ ባሉ አስተዳደር ተኮር ነባራዊ ኩነቶች ዙሪያ የማጠቃለያ ውይይት ኮሚቴው ከድጋፍ ሰጪ የዘርፍ ባለሙያዎች ጋር በመሆን ያከናውናል።

2. የመረጃ ትንተና እና የማጣራት ሥራው ማጠቃለያ ሰነድ ይደራጃል።

3. የማጣራት ሰነዱ በግኝቱ፣ በሂደቱ እና በዘላቂ መፍትሔው ላይ የሚያተኩር ይዘት ኖሮት መረጃ እና ማስረጃዎችን ከህትመት እንዲሁም ምስል ወድምጽ ጋር በአባሪነት በማካተት ይጠናቀቃል፡፡

4. በስተመጨረሻም በማጣራት ሥራው የተገኘውን ውጤት በቋሚ ሲኖዶስ በኩል አጀንዳ አስይዞ ለምልዓተ ጉባኤ ያቀርባል።

በማለት የተቋቋመው አጣሪ ኮሚቴ ያዘጋጀውን መግለጫ የሰጠ መሆኑን ያገኘነውን መረጃ ያስረዳል፡፡

©የኢኦተቤ ቴቪ


🕊እንኳን አደረሳችኹ ወርኃ የካቲትን በሰላም ያስፈጽመን የንስሐ ልብ ይሰጠን::

🕊"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::"    /ማቴ ፫:፫/

💥ስለ ንስሐ💥

✝ከቅዱስ ሙሴ ጸሊም የምንማራቸው 7 ነገሮች።

፩, 🌿ቅዱስ አብርሃምን መምሰል( ፈጣሪውን ተመራምሮ አገኘ)::

፪,  🌿ዓለምንና የዓለምን ነገሮች መተው።

፫, 🌿የንስሐ ሕይወት( ንስሐን በትጋት መፈጸም)።

፬, 🌿መታዘዝ (የሚታዘዘውን ሳያጓድል መስራትን)።

፭, 🌿ለሌሎች መኖርን።

፮, 🌿በሰው አለመፍረድን።

፯, 🌿ትሕትናን።
        
1,💥ጥሩ ክርስትና ፈጥኖ የሚገኝ አይደለም፡፡ ትእግስትን ይጠይቃል፡፡

2,💥ሰይጣን እኛን ኃጢአት በማሠራት አይረካም፡፡ የሚፈልገው ተስፋ ማስቆረጥ ነው፡፡

3, 💥በእምነት የሚደረግ የትኛውም ጸሎት መፍትሔ አለው፡፡

4,💥የበጎ ለውጥ እናት ዓላማና ቁርጥ ውሳኔ ናቸው

4 ነገሮችን በደንብ ልብ እንበል!
    1, ✨አላማ

    2 ,✨እምነት

    3,✨ጥረት

    4 ✨ጥንቃቄ

9ኙ የቅድስና መንገዶች

፩💥ሃይማኖት
፪💥ጾም
፫💥ጸሎት
፬💥ስግደት
፭💥ምጽዋት
፮💥ፍቅር
፯💥ትህትና
፰💥ትዕግስት
፱💥የዋህነት

✨እነዚኽን ያዟቸው ተጠቀሙባቸው

🌿እግዝእትየ ፍትሕኒ እማዕሠሩ ለሰይጣን፤
እሙ ለመድኅን ወለተ ብርሃን።

✝ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት
🌿ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን! (የቅዱሳንን ታሪክ እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)
🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር)

ለ ፳፻፲፯ የቤት ሥራ የሚሆኑ ፭ መልእክቶች

፩.ለጸሎት ተነሱ
፪.ክርስትናን መኖርን እንጀምር
፫.የእውነት ንስሐ ያስፈልገናል
፬.ካቆሸሸን ማኅበራዊ ሚዲያ ጥቂት እንራቅ
፭.ትልቁ መከራ እንዳያገኘን
https://t.me/enabib


+ከዚያም የተወሰኑ አገልጋዮችን አስቀምጣላቸው ወደ
ኢየሩሳሌም በመሄድ ለ7 ዓመታት በአየሩሳሌም ከኖረች
በኋላ የእመቤታችን በዓል ለማክበር ወደ ግብፅ በመሄድ
ላይ ሳለች በመንገድ አንድ ቤተ ክርስቲያን ውስጥ ገብታ
ስትፀልይ እመቤታችን በስዕሏ ላይ ተገልጣ: ቦታዋ
በኢትዮጵያ መሆኑን ነግራ: እጇን ዘርግታ "ወደ ኢትዮጵያ
ሂጂ" ብላ ነገረቻት::

+በኋላ በብርሃን አምድና በቅዱስ ሚካኤል እየተመራች
አሁን ወደ ምትታወቅበትና የእግዚአብሔር ድንቅ ሥራ ወደ
ተገለፀበት እመ ምዑዝ ኪዳነ ምህረት ቅድስት ፍቅርተ
ክርስቶስ አንድነት ገዳም ደርሳለች፡፡
+በቦታው ስትደርስ የቦታው ልምላሜ የሚያስደስት ነበርና
"ይህች ቦታ ምን ታምር!" ብላለች፡፡ ቦታውም እስከ አሁን
ድረስ ምንታምር በመባል ይጠራል፡፡

+ምንታምር ላይ ከአገልጋዮቿ ጋር በመሆን አርፋ ሳለ
ከኢየሩሳሌም መርቶ ያመጣት የብርሃን አምድ በዚያ ቦታ
ላይ በስፋት ረቦ (ከምድር እስከ ሰማ ተተክሎ) ብታየው:
መልአኩም "ቦታሽ ይሄ ነው" ብሎ ቢነግራት በዚያው
ተቀምጣለች፡፡

+የቦታው ባለ አባት "ይህን ቦታ ልቀቂ" ቢሎ ቢጠይቃት
"እግዚአብሔር የሰጠኝ ቦታዬ ነው" ብላዋለች፡፡ እርሱም
ለክስ ወደ ጎንደር በመሄድ አፄ ሱስንዮስ አርፈው አፄ
ፋሲል ነግሰው ነበርና እሳቸውን ፍርድ ቢጠይቃቸው በዝና
ያውቋት ነበርና "ቤተ ክርስቲያን ካልተሰራ ትልቀቅልህ:
ከተሠራ ግን ሌላ ቦታ ይሰጥሃል" የሚል ፍርድ አስፈርዶ
ነበር::

+ሲመለስ ቅዱስ ሚካኤል ቀድሞ "ቶሎ ቤተ ክርስቲያን
ስሪ እንዲህ የሚል ፍርድ ተፈርዷል ብሎ ነግሯት ‹‹ታህሳስ
14 ቀን ከነግህ ፀሎት በኋላ በሰንሰልና በስሚዛ
ግድግዳዋን: በአይጥ ሀረግ ማገር አድርጋ: የግድግዳ
ቤተ መቅደስ በዕለተ አርብ: በአንድ ቀን ሰርታ ታህሳስ 16
ቀን እሁድ ታቦተ ኪዳነ ምህረትን አስገብታ ቅዳሴ
አስቀድሳለች::››

+ቅዳሴውም ከተፈፀመ በኋላ ጌታችን ከቅዱስ መንበሩ
ላይ እንዳለ ሆኖ ከእናቱ ከእመቤታችን ጋራ ታያቸው፡፡
ከመንበሩ ወርዶም ይህን ቦታ በባረከው ጊዜ የስሚዛው
ቤተ መቅደስ በአራቱም አቅጣጫ ለፈጣሪው ሰገደ፡፡

+የመሬት መናወጥም ሆነ:: ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስም
"ልታጠፋን መጣህን? ቤተ ክርሰቲያኔንስ ልታፈርሳት
ነው?" ብላ ብትጠይቀው "ይህ የሰንሰል ቤተ መቅደስሽ
ዳግም እስከምመጣ ድረስ ሳይፈርስ: ሳይታደስ ፀንቶ
ይኖራል፣ በውስጡም እስከ ዓለም ፍፃሜ ድረስ
የክሀድያንና ፣ መናፍቃን እግር አይገባበትም፣ በውስጧ
ቁርባንን የተቀበሉ ሁለ ኃጢያታቸው ይሰረይላቸዋል፣
ዘወትር ምህረቴ በረከቴ ከእነርሱ ጋር ይኖራል" በማለት
ተናግሮ ተሰወራቸው፡፡

+ከዚያም በኋላ መነኮሳትና መነኮሳይያት የቅድስት ፍቅርተ
ክርስቶስን የትሩፋት ዜናዋን ሰምተው ከየአቅጣጫው
ተሰበሰቡ፡፡ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስም በአምላክ ሀይል
ተጋድሎአቸውን ይፈፅሙ ዘንድ ታስተምራቸው ፣
ትመክራቸው፣ በተግባርም እያሳየቻቸው ለብዙ ዘመናት
ከኖሩ በኋላ በገዳሙ ላይ የአጋንንት ፆር እንዳይነሳ
ወንዶቹን ለብቻ ሴቶቹን ለብቻ አደረገች፡፡

+ዘወትርም እንዳይተያዩ የእግዚአብሔር መልዐክ
በቅድስተ ፍቅርተ ክርሰቶስ ፀሎት ይጠብቃቸው ነበር፡፡
ከዚህ በኋላ እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ከዚህ
ኃላፊ ዓለም መለየቷ በቀረበ ጊዜ ሁለት መላዕክት ወደ
እርሷ መጥተው በብርሃን ሰረገላ ጭነው ወደ ደብረ ነባት
(ወደ ብሔረ- ህያዋን) ወስደው በዚያ ቅዱስ ቁርባንን
አቀብለው ወደ ቦታዎ መለሷት፡፡

+መልዐኩም "ከጻማ: ከድካም: ከመታረዝ: ከረሐብ
ከጥም: ከመትጋት: ከእንባ: ከዚህ ዓለም የምትለይበት
ጊዜ እነሆ ደረሰ" አላት፡፡ የካቲት 27 ቀንም ወደ ምስራቅ
እጇን ዘርግታ ቆማ ስትጸልይ በቤተ ክርስቲያን ውስጥ
ከደስታ ብርሀን ጋር ያማረ ሽታ መላ::

+ጌታችን ከአዕላፋት መላዕክትና ቅዱሳን ጋር ወደ እርሷ
መጣ፡፡ እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስም ሰገደች፡
ተንበረከከች: እጅግም አለቀሰች፡፡ ከወደቀችበት ቦታ
አንስቶ ‹‹ላጠፋሽ አልመጣሁም ወዳጄ ላከብርሽ ነው
እንጂ›› አላት፡፡

+"የዘለአለም መንግስት አዘጋጅቼልሻለሁና ደስ ይበልሽ"፡፡
ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስም ቃል ኪዳን እንዲገባላት
ተማጸነችው:: ጌታችንም ‹‹ሁሉም እንደ ቃልሽ ይሁንልሽ::
በስምሽ ስሜ ተጨምሯልና ለቤተ ክርስቲያንሽ መባ
የሰጠ፣ የተላከ ፣የተቀበረ፣ ቤተ መቅደስሽ መጥቶ
የተሳለመ ፣ እስከ 12 ትውልድ የምህረት ቃል ኪዳን
ሰጠሁሽ::

+በረከቴም በቤቱና በልጆቹ በገንዘቡም ላይ ይደር::
የገድልሽ መጽሐፍ ባለበት አጋንንት (ሰይጣናት)
አይቀርቡም:: በአዝመራ ስምሽን በጠሩት ጊዜ የለመለመ
ይሁን:: በጸሎትሽ የተማጸነ ሁሉ ባለጤና ይሁን::

+ስምሽን በእውነት የሚጠራ የከበረ ነው፡፡ ያለመጠራጠር
በቀናች ሐይማኖት የገድልሽን መጽሐፍ የጻፈ: ያጻፈ:
ያነበበ: የተረጎመ በሐይማኖት የሰማ: እስከ ቀዝቃዛ ውሃ
ድረስ የሰጠ ኃጢያቱ ይሰረይለታል::
ስለ ድካምሽ ስለ ትሩፋትሽ 7 አክሊሎችን እና ይህን ሁሉ
ቃል ኪዳን ሰጠሁሽ፡፡ ላልምረው ቦታሽን
አላስረግጠውም›› ብሏት ወደ ሰማይ አረገ፡፡

+በማግስቱ ትንሽ ህመም ታመመች ደናግል መነኮሳትን
ጠርታ የእረፍት ቀኗ መድረሱን ነገረቻቸው:: ከመካከላቸው
አንዷን ለገዳሙ አስተዳዳሪነት መርጣ በፍቅር ስም
ተሰናበተቻቸው፡፡ የዳዊት መዝሙርንም ስትጸልይ የካቲት
29 ቀን እሁድ አጥቢያ ጠዋት በጌታ በዓል አንቀላፋች
(ነፍሷ ከስጋዋ ተለየች)፡፡

+ጌታችንም ከእናቱ: ከቅዱሳኑ ጋር መጥቶ ነፍሷን
ተቀብሎ ወደ ዘለዓለም ገነት ወሰዳት፡፡ ቅዱሳንም
ከመላእክት ጋር እልል እያሉ እያመሰገኑ ወደ ዘለዓለም
ቦታ ገነት አስገቧት፡፡ ከቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ መቃብር
ላይ 40 ቀናት ብርሃን ሲበራበት ታይቷል፡፡

+በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት: በመቂት ወረዳ ጥባ
ማርያም ቀበሌ ውስጥ ምን ታምር በመትባል ቦታ ላይ
በ16ኛው መቶ ክ/ዘመን በኢትዮጵያዊቷ ሰማዕትና ጻድቅ
ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ የተመሰረተቸው እመ ምዑዝ
ኪዳነ ምህት ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ አንድት ገዳምም
በዓላቶቿ የሚከበሩት ታህሳስ 16 የቅዳሴ ቤቷ እንዲሁም
የካቲት 29 ቀን በዓለ እረፍቷ ይከበራል፡፡

††† ከቅድስት እናታችን በረከት አምላክ አይለየን::

††† የካቲት 29 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ኢትዮዽያዊት
2.ቅዱስ ዘርዐ ክርስቶስ (ጻድቅና ሰማዕት)
3.ቅዱሱ ሕፃን (የፍቅርተ ክርስቶስ ልጅ)
4.ቅዱስ ቢላካርዮስ ዘሃገረ አርሞኒ (አረጋዊ: ደራሲ: ጻድቅና ሰማዕት)

††† ወርኀዊ በዓላት
1.የፈጣሪያችንና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ልደት
2.ቅድስት አርሴማ ድንግል
3.ቅዱስ ዼጥሮስ ተፍጻሜተ ሰማዕት
4.ቅዱስ ማርቆስ ዘቶርማቅ

††† "መልካም ያደረጉ ብዙ ሴቶች አሉ:: አንቺ ግን ከሁሉ ትበልጫለሽ::
ውበት ሐሰት ነው:: ደም ግባትም ከንቱ ነው::
እግዚአብሔርን የምትፈራ ሴት ግን እርስዋ ትመሰገናለች:: ከእጇ ፍሬ ስጧት:: ሥራዎቿም በሸንጐ ያመስግኗት::" †††
(ምሳሌ. 31:29)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††


†✝† እንኳን ለኢትዮዽያዊቷ እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †✝†

†✝† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †✝†

†✝† እመ ምዑዝ (እም ምዑዝ) †✝†

††† ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ሐዋርያዊት: ጻድቅትና ሰማዕት ናት::
ይህስ እንደምን ነው ቢሉ:-
=>ወር በገባ በ29 በቤተክርስቲያናችን ታስበው
ከሚውሉት እግዚአብሔር አምላክ ቃል ኪዳን ከገባላቸው
(ከሰጣቸው) እናቶች ኢትዮጵያዊቷ ሰማዕትና ጻድቅት
ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ (እመ ምዑዝ) ትገኛለች::
ፍቅርተ ክርስቶስ (እመ ምዑዝ) ማን ናት? ምን ቃል ኪዳን
ተሰጣት? ያደረገችውን ተጋድሎ በጥቂቱ እንመልከት:-
✞✞ ጻድቅን በጻድቅ ስም የሚቀበል የጻድቁን ዋጋ
ይወስዳል፡፡ (ማቴ. 10፡40) ✞✞

=>በሰሜን ወሎ ሀገረ ስብከት በመቂት ወረዳ ጥባ
ማርያም ቀበሌ ውስጥ ምን ታምር በመትባል ቦታ ላይ
በ16ኛው መቶ ክፍለ ዘመን በኢትዮጵያዊቷ ሰማዕትና
ጻድቅ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ የተመሰረተቸው እመ
ምዑዝ ኪዳነ ምህት ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ አንድት
ገዳም ትገኛለች፡፡

+ይህች ገዳም ከአዲስ አበባ በደሴ ወደ ጎንደር
በሚወስደው መንገድ 665 ኪሎ ሜትር ከተጓዙ በኋላ
ገራገር (ፍላቂት) ከምትባለው ከተማ በመውረድ በእግር
2፡30 እንደተጓዙ ከ370 ዓመት ባለይ ያስቆጠረችውን
እመ ምዑዝ ኪዳነምህት ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ በአንድ
ቀን የሠራቻትና ለጌታ በአራቱም አቅጣጫ የሰገደችውን
ታላቅና ድንቅ ቤተመቅደስ ያገኛሉ፡፡

+የዚህች ታላቅ ገዳም መስራች ኢትጵያዊት ሰማዕትና
ጻድቅ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ በደቡብ ጎንደር ደራ ፎገራ
አንበሳሜ ወረዳ ልዩ ስሙ አቡነ ሐራ ገዳም አዋሳኝ ከተታ
ማርያም ተብሎ በሚጠራ ቦታ በሚያዚያ 4 ቀን ተፀንሳ
ታህሳስ 29 በጌታ ልደት ቀን ተወለደች፡፡

+አባቷ ላባ እናትዋ ወንጌላዊት የተባሉ እግዚዘብሔርን
የሚወዱ ትዕዛዙን የሚከብሩ ደጋግ ሰዎች ነበሩ፡፡
መሀን ሆነው ልጅ ባመውለዳቸው እያዘኑ ተግተው ወደ
እግዚአብሔር በመፀለያቸው ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስን
የመሰለች ልጅ: በፀሎትዋ ለሀገር ለወገን የምትበቃ
ሰጥቷቸዋል፡፡

+ከዚያም 80 ሲሆናት ለልጅነት ጥምቀት ወደ ቤተ
መቅደስ በወሰዷት ጊዜ ከጥምቀት በኋላ ስጋ አምላክ
ስትቀበል (ስትቆርብ) "ሕይወት የሆነውን ቅዱስ ስጋህን
ክቡር ደምህን የሰጠኸኝ አምላኬ ክብር ምስጋና ይግባህ"
ብላ አመስግናለች፡፡ ስመ ክርስትናዋ ማርያም ፀዳለ
ሲሆን የአለም ስሟ 'ሙዚት' ነው፡፡ ፍቅርተ ክርስቶስ
የምንኩስና (የቆብ) ስሟ ነው፡፡

+እናታችን ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ አባ ዳንኤል ከሚባል
አባት መፅሐፍን እየተማረች ካደገች በኋላ ለአቅመ ሄዋን
ስትደርስ እናትና አባቷ ሊድሯት በመፈለጋቸው ዘርዓ
ክርስቶስ ለሚባል ከደጋግ ሰዎች ወገን ለሆነ ሰው
አጋቧት፡፡

+ማታ እንደ ሙሽሮች ደምብ ወደ ጫጉላ ቤት ሲገቡ
ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ዘርዓ ክርስቶስን "ወንድሜ ሆይ!
እኔ የእናት አባቴን ፍቃድ ለመፈፀም ነው እንጂ ስጋዊ
ሙሽራ መሆን አልፈልግም ፡፡ ፍላጎቴ የእግዚአብሔር
ሙሽራ መሆን ነው" በማለት ብታማክረው ቅዱስ ዘርዓ
ክርስቶስም ፀጋ እግዚአብሔር የበዛለት ሰው ነበርና "እኔም
እናት አባቴን ላክበር ፈቃዳቸውን ለመፈፀም ነው እንጂ
የስጋ ፈቃድ የለኝም በማለት ተነጋገሩ::

+በኋላ በአንድ ቤት ውስጥ ለቤተሰቦቻቸው: ለአገሬው
እንደ ባልና ሚስት ግን በንፅህና ለ40 ዓመት ሁለቱም
በድንግልና ኖረዋል፡፡

+ከዚያም በኋላ በእግዚአብሔር ፈቃድ ቅዱስ ሚካኤል
መጥቶ ወንድ ልጅ እንደሚወልዱ ቢግራቸውም ሁለቱም
"ይህስ አይሆንም" ብለው ለ40 ቀን በጾም: ፀሎት:
በትጋት ጸልየዋል፡፡ መልአኩ ተገልጦ "ይህ የእግዚአብሔር
ፈቃድ ነው ሁለታችሁም ድንግልናችሁ አይፈርስም ብሎ
ነግሮአቸዋል፡፡

+ከዚያም ወንድ ልጅ ወልደዋል:: ህፃኑ በተወለደ በ7
ዓመቱ በቅዱስ ሚካኤል እቅፍ ገነትን ለ7 ቀናት ከጎበኛት
በኋላ ወደ ምድር ሲመልሰው "በእናት አባቴ አምላክ
ይዤሃለሁ ወደዚች ወደ ከፋች ዓለም አትመልሰኝ" ብሎ
ቢለምነው ቅዱስ ሚካኤልም ከአምላክ ጠይቆ በብሔረ
ህያዋን የህፃናት አለቃ ተብሎ እንዲቀመጥ አድርጎታል፡፡
ስሙም ዳግማዊ ቂርቆስ ተብሏል፡፡

+ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶና ቅዱስ ዘርዓ ክርስቶስም ልጅ
ከወለዱ በኋላ እንደ ቀደሞው በቅድስና: በንፀህና ፀንተው
ኑረዋል፡፡ በዘመናቸው በኢትዮጵያ ነግሶ የነበረው አፄ
ሱስንዮስ ሃይማኖቱን ለውጦ 'ሁለት ባህርይ የሚሉ
ካቶሊኮችን በመቀበሉ ክርስቲያኖችን እየገደለ ነው' የሚል
ወሬ ሰምተው ወደ ንጉሱ በመሄድ ሳይፈሩ ስለ ተዋህዶ
ሃማኖታቸው በንጉሱ ፊት መስክረዋል፡፡

+ንጉሱም በጣም የበዛ መከራን አድርሶባቸዋል፡፡ መከራ
በበዛ ቁጥር እነርሱም እየፀኑ ተከታዮቻቸውንና የንጉሱን
ሠራዎቶች ሳይቀር አሳመኑ:: 60,000 ክርስቲያኖችም
ሰማዕትነትን ተቀብለዋል፡፡

+ንጉሱም በጣም የበዛ መከራ አድርሶባቸዋል፡፡ መከራ
በበዛ ቁጥር እነርሱም እየጸኑ ተከታዮቻቸውንና የንጉሱን
ሰራዊቶች እያሳመኑ ቢያስቸግሩ በሰማዕትነት አንገታቸውን
አስቆርቷቸዋል፡፡ አንገታቸውም ሲቆረጥ ከሁለቱም ደም
ውሃ ወተት ፈሷዋል፡፡

+በዚያን ዘመን ከእነ ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ ጋር
ሰማዕትነት ከተቀበሉት ውስጥ የማህበረ ስላሴው ጻድቁ
አምደ ስላሴ: የጎረጉር ማርያም አባ መርአዊ: የመሲ
ኪዳነ ምህረት እመ ወተት እና ከ60 ሺ በላይ ክርስቲያኖች
ሰማዕትነት ተቀብለዋል፡፡

+ቅድስት ፍቅርተ ክርስቶስ አንገቷ ከተቆረጠና ሰማእትነት
ከተቀበለች በኋላ ወደ ምድር መልሶ አንገቷን ከቀሪው
የሰውነቷ ክፍል ጋር አዋህዶ ከአንቅልፍ አንደሚነቃ ሰው
ቀስቅሶ አስነስቷቷል፡፡
ከዚያም ከአቡነ ማርቆስ ስርዓተ ምንኩስናን በመቀበል
ዋልድባ ገዳም ለ4 ዓመት አገልግላለች፡፡

+ከዚህም ከ500 የሚበልጡ ተከታዮችዋን መነኮሳትን
አስከትላ በሰሜን ወሎ ቆቦ ወረዳ ወደምትገኘውና በፃድቁ
በአባ ጉባ ተመስርታ ጠፍታ ወደ ነበረችው ራማ ኪደና
ምህረት አንድነት ገዳም በመሄድ ገዳሟን አቅንታ: የወንድ
የሴት ብላ ስርዓት ሰርታ: ገዳሟን አስተካክላ: 500
የሚሆኑ አገልጋች መነኮሳትን አኑራ ወደ ኢየሩሳሌም ጉዞ
ጀምራለች፡፡

+በመንገዷም ላይ ሰውን የሚበሉ ወደ ሚኖሩበት አካባቢ
በመድረስ እነርሱም እርሷንና 60 የሚሆኑ አገልጋዮችዋን
ዓይኖቻቸውን በጉጠት በማውጣት ለ4 ወራት በጨለማ
ቤት ውስጥ ዘግተውባቸዋል፡፡ ከአራት ወር በኋላም በዓል
አድገው ለመብላት ከቤት ቢያወጧቸው መልካቸው እንደ
ፀሐይ የሚያበራ ቢሆንባቸው "አንቺ ሴት ምንድን ናችሁ?"
ብለው ጠይቀዋታል፡፡

+እርሷም ክርሰቲያን መሆናቸውንና እነሱ የስላሴ ሕንፃ
የሆነውን የሰውን ልጅ መብላት እንደሌለባቸው
ብትመክራቸው "ምን አንብላ?" ብለዋታል፡፡ እርሷም
ከራማ ኪዳነ ምህረት ስትነሳ የእህል ዘርን በአገልጋዮቿ
አሲዛ ነበርና ስንዴውን በአንድ ቀን ዘርታ: በቅሎ: ታጭዶ:
ደርቆ: ተፈጭቶ ለምግብነት በቅቷል፡፡

+እርሷ ቀምሳ ብታቀምሳቸው እንደማር እንደ ወተት
የሚጣፍጥ ሆኖላቸው በደስታ ተመግበውታል፡፡ ከዚያም
እንደዚህ እያደረጉ እየሰሩ እንዲበሉ አስተምራ: አስጠምቃ
ከ6 የሚበልጡ አብያተ ክርስቲያናትን አስተክላላቸዋለች፡፡


✝እንኳን አደረሰነ!

☞ወርኀ የካቲት ቡሩክ፥ አመ ፳ወ፰

✝ጾም ዐቢይ ዘመድኅን ክርስቶስ (አምላክነ)
✝ወተዝካረ በዓሉ ለአማኑኤል እግዚእነ (ስቡሕ ወውዱስ)

✞ወበዓለ ቅዱሳን አበው፦

✿ማር ቴዎድሮስ ሮማዊ (ሰማዕት)
❀፷ወ፫፻ ወ፬ቱ ማኅበራኒሁ (ሰማዕታት)
❀ዮሐንስ ምሥራቃዊ (ዘጉንድ ወዘጸገሮ)

❖ወስብሐት ለእግዚአብሔር፤
ኪያነኒ ይምሐረነ በጸሎቶሙ።
ወበረከቶሙ ይብጽሐነ፤ ለዓለመ ዓለም አሜን፡፡
https://t.me/enabib


የመነኮሳት አባት የሚባለው ማን ቅዱስ ነው?
So‘rovnoma
  •   መቃርስ
  •   ጳውሊ
  •   እንጦንስ
  •   አቡነ አረጋዊ
3 ta ovoz




ዝክረ ቅዱሳንን

እንማር


አምላከ ቴዎድሮስ ሮማዊ ይቅር ይበለን!!!


🕊እንኳን አደረሳችኹ ወርኃ የካቲትን በሰላም ያስፈጽመን የንስሐ ልብ ይሰጠን::

🕊"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::"    /ማቴ ፫:፫/

💥ስለ ንስሐ💥

✝ከቅዱስ ሙሴ ጸሊም የምንማራቸው 7 ነገሮች።

፩, 🌿ቅዱስ አብርሃምን መምሰል( ፈጣሪውን ተመራምሮ አገኘ)::

፪,  🌿ዓለምንና የዓለምን ነገሮች መተው።

፫, 🌿የንስሐ ሕይወት( ንስሐን በትጋት መፈጸም)።

፬, 🌿መታዘዝ (የሚታዘዘውን ሳያጓድል መስራትን)።

፭, 🌿ለሌሎች መኖርን።

፮, 🌿በሰው አለመፍረድን።

፯, 🌿ትሕትናን።
        
1,💥ጥሩ ክርስትና ፈጥኖ የሚገኝ አይደለም፡፡ ትእግስትን ይጠይቃል፡፡

2,💥ሰይጣን እኛን ኃጢአት በማሠራት አይረካም፡፡ የሚፈልገው ተስፋ ማስቆረጥ ነው፡፡

3, 💥በእምነት የሚደረግ የትኛውም ጸሎት መፍትሔ አለው፡፡

4,💥የበጎ ለውጥ እናት ዓላማና ቁርጥ ውሳኔ ናቸው

4 ነገሮችን በደንብ ልብ እንበል!
    1, ✨አላማ

    2 ,✨እምነት

    3,✨ጥረት

    4 ✨ጥንቃቄ

9ኙ የቅድስና መንገዶች

፩💥ሃይማኖት
፪💥ጾም
፫💥ጸሎት
፬💥ስግደት
፭💥ምጽዋት
፮💥ፍቅር
፯💥ትህትና
፰💥ትዕግስት
፱💥የዋህነት

✨እነዚኽን ያዟቸው ተጠቀሙባቸው

🌿እግዝእትየ ፍትሕኒ እማዕሠሩ ለሰይጣን፤
እሙ ለመድኅን ወለተ ብርሃን።

✝ዝክረ ቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት
🌿ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን! (የቅዱሳንን ታሪክ እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል)
🌿አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ (መጽሐፈ ምሥጢር)

ለ ፳፻፲፯ የቤት ሥራ የሚሆኑ ፭ መልእክቶች

፩.ለጸሎት ተነሱ
፪.ክርስትናን መኖርን እንጀምር
፫.የእውነት ንስሐ ያስፈልገናል
፬.ካቆሸሸን ማኅበራዊ ሚዲያ ጥቂት እንራቅ
፭.ትልቁ መከራ እንዳያገኘን
https://t.me/enabib


የካቲት28
✝ በዓለ ጽንሰቱ ለአቡነ ዮሐንስ ዘጉንድ ወዘደብረ ኤጎራ ✝

=>በረከቱ ትብጽሐነ፡፡"

ዝክረ ቅዱሳን ጉባኤ
" ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::  አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር/
https://t.me/enabib


††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን †††

††† እንኩዋን ለታላቁ ሰማዕት "ቅዱስ ቴዎድሮስ ሮማዊ" ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ †††

+*" ቅዱስ ቴዎድሮስ ዘሮም "*+

=>ሰማዕትነት በክርስትና ለሃይማኖት የሚከፈል የመጨረሻው ዋጋ (መስዋዕትነት) ነው:: ሰው ለፈጣሪው ሰውነቱን ሊያስገዛ: ሃብት ንብረቱን ሊሰጥ ይችላል:: ከስጦታ በላይ ታላቅ ስጦታ ግን ራስን አሳልፎ መስጠት ነው::

+ራስን መስጠት በትዳርም ሆነ በምናኔ ውስጥ ይቻላል:: የመጨረሻ ደረጃው ግን ሰማዕትነት ነው:: "አማን መነኑ ሰማዕት ጣዕማ ለዝ ዓለም: ወተዓገሡ ሞተ መሪረ በእንተ መንግስተ ሰማያት" እንዳለው ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ ሰማዕትነት ማለት መራራውን ሞት ስለ ፍቅረ እግዚአብሔር ሲሉ መታገስ ነው::

+እርሱ ቅሉ መድኃኒታችን ክርስቶስ የሰማይና የምድር ጌታ ሲሆን ኃፍረተ መስቀልን ታግሦ ሙቶልን የለ! በዓለም ያሉ ብዙ እምነቶች ስለ መግደል በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ያስተምራሉ:: ክርስትና ግን መሞትን እንጂ መግደልን የሚመለከት ሕግ የለውም::

+እርሱ ባለቤቱ "ጠላቶቻችሁን ውደዱ: የሚረግሟችሁን መርቁ: ስለሚያሳድዷችሁ ጸልዩ" ብሎናልና:: (ማቴ. 5:44) ነገር ግን ዕለት ዕለት ራሳችንን በሃይማኖትና በምግባር ካልኮተኮትነው ክርስትና በአንድ ጀምበር ፍጹም የሚኮንበት እምነት አይደለምና በፈተና መውደቅ ይመጣል::

+በተለይ የዘመኑ ክርስቲያን ወጣቶች ልናስተውል ይገባናል:: የቀደሙ ወጣት ሰማዕታት ዜና የሚነገረን እንድንጸና ነውና::

=>ቅዱስ ቴዎድሮስ በዘመነ ሰማዕታት (በ3ኛው መቶ ክ/ዘመን) በቀድሞው የሮም ግዛት ውስጥ ከተነሱ ታላላቅ ሰማዕታት አንዱ ነው:: በወቅቱ መሪ የነበረው ክሀዲው መክስምያኖስ "ክርስቶስን ክደህ ለጣኦት ስገድና በከተማዋ ላይ እሾምሃለሁ" ቢለው "ለእኔ ሃብቴም ሹመቴም የክብር ባለቤት ኢየሱስ ክርስቶስ ነው" በማለቱ ንጉሡ ተቆጥቶ በብረት ዘንግ አስደበደበው::

+በመንኮራኩር አበራየው:: ለአናብስት ጣለው:: አካላቱን ቆራረጠው:: በእሳትም አቃጠለው:: ቅዱስ ቴዎድሮስ ስቃዮችን ስለ ቀናች ሃይማኖት ሲል በትዕግስት ተቀበለ:: በፍፃሜውም አንገቱን በሰይፍ ተመትቶ 3 አክሊላት ወርደውለታል::

+ከፈጣሪው ዘንድም ነጭ መንፈሳዊ ፈረስና ቃል ኪዳን ተቀብሏል:: ስሙን የጠራ: መታሠቢያውን ያደረገ ዋጋው አይጠፋበትም:: (ማቴ. 10:41)

=>አምላከ ቅዱሳን ከቅዱሱ ሰማዕት በረከት ይክፈለን:: አይተወን:: አይጣለን:: ጾሞ ለማበርከትም ያብቃን::

=>የካቲት 28 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት=
1.ቅዱስ ቴዎድሮስ ሮማዊ (ሰማዕት)
2."6,304" ሰማዕታት (በቅ/ቴዎድሮስ አምላክ አምነው ሰማዕትነት የተቀበሉ)

=>ወርኀዊ በዓላት
1.አማኑኤል ቸር አምላካችን
2.ቅዱሳን አበው (አብርሃም: ይስሐቅና ያዕቆብ)
3.ቅዱስ እንድራኒቆስና ሚስቱ ቅድስት አትናስያ
4.ቅድስት ዓመተ ክርስቶስ

=>+"+ እግዚአብሔር ለኛ የሰማዕትነትን ሥራ ይሰጠን ዘንድ ቅዱሳን ስለሚሆኑ ሰማዕታት እንማልዳለን:: +"+
(ሥርዓተ ቅዳሴ ቁ. 73)

>


ቅኔ
➠ ➠ ➠
ኦ አምላክ ምሥጢረ-ቅኔ ኢትኅድገነ እሙነ ፣
ኵሉ ዓለም በምልዑ እስመ ይሜንን ምስኪነ።
🙏🙏🙏
( የድንግል ልጅ ፣ የድኻ አባት ፣ ቸሩ አምላክ መድኃኔዓለም ክርስቶስ ሆይ! "ወላጅ እንደ ሌላቸው #አልተዋችኹም የሚለው #ቃልኪዳንህ አይለየን። ዮሐ ፲፬፥፲፰ )


#ዳግማዊ ምኒልክ ጦርነቱ ነገር እርግጥ ሲሆን የእግዚአብሔር ርዳታ እንዳይለያቸው ሽተው ብዙ ተጉዘዋል፡፡ ወደእየ ገዳማቱ እና አድባራቱ ጧፍ፣ ዕጣን እና መገበሪያ አስይዘው ጸሎተ ዕጣን እንዲደረስ ላኩ፤ በጸሎት አስቡኝ አሉ፤ በኪደተ እግር ወደ አራዳው ጊዮርጊስ ጎራ ብለው ተሳሉ፡፡

“ጦርነቱን ካሸነፍኩ በልዩ ሁኔታ
ቤትህን አሳንጻለሁ” ብለው፡፡ ዕለቱን ካህናቱ ጸሎት፣ ንጉሡም የጦርነት ዝግጅቱን ጀመሩ፡፡
ምታ ነጋሪት ክተት ሠራዊት ተባለ፡፡
በዚህም ካህናት ተነሡ “ሃገር ሲኖር፣ ንጉሥ ሲኖር፣ ሕዝብ ሲኖር አይደል እንዴ ቤተ ክርስቲያን የምትኖረው” አሉ፡፡ ምህላው እና ሱባኤው በየአድባራቱ እና ገዳማቱ ተጀመረ፡፡

ከመሃከላቸው አባቶችን መረጡ፡፡ ከአዲስ አበባ ዐድዋ ድረስ ታቦተ ሕጉን አክብረው ይዘው ከሄዱት መካከል ለያውም በባዶ እግራቸው የሄዱ ናቸው ተብሎ ተጽፎላቸዋል የግቢ ገብርኤሉ ካህን መምሬ ካሣሁን፡፡ ታቦተ ጊዮርጊስን ያዙ፤ ሊቃውንት ከበሮ፣ ጸናጽል፤
ካህናት መስቀል፣ ዕጣን፣ ወንጌል ያዙ፡፡ ዘመቻ ተጀመረ ወደ አድዋ፡፡

ሙሉ ቀን ጉዞ ሆኖ ዕረፍት ሲሆን ድንኳን ይተከላል፡፡ ታቦቱ በድንኳን፣ ሕዝቡ በውጪ ይሆንና የሠርክ ጸሎት፣ ምህላ ይደረጋል፡፡ ታቦት ካለ ዝማሬ፣ ጸሎት አለ፡፡ ለያውም ወደ ጦርነት ወደ ሞት እየተሄደ፡፡ ሌሊት መነሣት፣ ጸሎት ማድረግ፣ ምኅላ ማድረስ የካህናቱ፣ የንጉሡ እና የዘማቹ መደበኛ ሥራ ሆነ፡፡

የማያልቅ የሚመስለው መንገድ አለቀ፡፡ የማይደረስ የሚመስለው ተደረሰበት፡፡ ትግራይ ገቡ፡፡ ቀድመው ተዘጋጅተው በምህላ እና በጸሎት የሰነበቱት የትግራይ ካህናት እና ሊቃውንት ሕዝቡን ጨምሮ ተቀበሏቸው፡፡ የጋራ ሱባኤ ታዘዘ፣ ምህላ ታወጀ፡፡ አጤው እና
እቴጌይቱ እንዳ አባ ገሪማ ሱባኤ ያዙ፡፡ መኳንቱ እና መሣፍንቱ ተራውን ወታደር ጨምሮ ሱባኤ ገባ፡፡

ሌት ጸሎት፤ ጧት ማታ ምኅላ፤ ቀን ቅዳሴ ፡፡ ጦርነት ካለ ሞት አለ፡፡ ሞት ካለ ደግሞ ፍትሐት አለ፡፡ ስለዚህ ወዶ ዘማቹ በጦርነት መሐል ቢሞት እንኳ ለሃገሩ፣ ለሃይማኖቱ፣ ለሚስቱ፣ ለልጁ እንደሆነ እና በሃይማኖቱ የሚደረጉ ሥርዓቶች እንደማይቀሩበት የኅሊና
ዕረፍት ይሰማውም ዘንድ የሰባት ቀን ምኅላ እና የቁም ፍትሐት ታወጀ፡፡

“እግዚአ ሕያዋን፡ ሕይወተ ሙታን፡ ተሥፋ ቅቡጻን፡ ረዳኤ ምንዱባን፡ ወመንጽኄ ኃጥአን…፡፡ የሕያዋን ጌታ፣ የሙታን ሕይወት፣ ተስፋ ለቆረጡት አለኝታ፣ የተቸገሩትን የሚረዳ፣ ኃጥአንን የሚያነጻ…"
የካቲት 22 ምሽት የመጨረሻው ምህላ የተደረሰበት፡፡ እንደ ወትሮው ምህላው ተደረሰ፡፡

ውስጣቸው ጠርጥሮ ነበርና በበነጋው የካቲት 23 ቅዳሴው ከወትሮው ቀደም ብሎ በሌሊት
እንዲገባ እና ከሌሊቱ 10 ሰአት እንዲያልቅ መከሩ፡፡ ከንጉሡ ጀምሮ በየ ራሱ፣ በየ ደጃዝማቹ፣ በየ ጎበዝ ዐለቃው ድንኳን እና ማደሪያ ምክር እና የጦር ወሬ፣ የጀግንነት ተረክ ሲነገር አመሸ፡፡ ጦርነቱ ሲጀመር የነበረውነረ ኹነት ብላቴን ጌታ
ኅሩይ በኢትዮጵያ ታሪክ መጽሐፋቸው “ሊቀ ጳጳሱ አቡነ ማቴዎስም ከየደብሩ አለቆች እና
ከድንባሮ ማርያም ካህናት ጋር ባንድ ስፍራ ቆመው ወደጦርነቱ የሚገባውን ወታደር እግዚአብሔር ይፍታህ እያሉ ይናዝዙ ነበር፡፡" ሲሉ ገልጸውታል።

ከድሉ በኋላ አፄ ምኒልክ አራዳ የሚገኘውን ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን በቃላቸው መሠረት
አንፀዋል። ጅማሮውን ያስጨረሱት ንግሥት ዘውዲቱ ናቸው።

ኢትዮጵያውያን አድዋን ባነሱ ቁጥር ስሙን ደጋግመው ያነሱታል፡፡ ስለ አድዋ ስዕል
ቢስሉም መሐል ላይ በነጭ ፈረስ ሆኖ ጦርነቱ መሐል አድርገው ይስሉታል፡፡ በዕለተ ቀኑ
ድል ጠላትን ድል ስላደረጉ፡፡

#የጥቁር_ህዝብ_ኩራት
#ዓድዋ_129
#የኢትዮጵያውያን_ድል

“የምኒልክ ተስፋው እግዚአብሔር ነው "

     #መልካም ቀን

  #ባለ ማዕተቦችን ወደዚህ
   ግሩፕ ይጋብዙ

ለመቀላቀል 👉  https://t.me/enabib


"መንግሥተ ሰማያት ቀርባለችና ንስሐ ግቡ::
(ማቴ ፫:፫


ሰላም ለክሙ እንጦንስ ወመቃርስ፤
አቢብ ሲኖዳ ገብረ መንፈስ ቅዱስ፤
ለባርኮትነ ንዑ ውስተ ጽርሐ ዛቲ መቅደስ፤
ተክለ ሃይማኖት አኖሬዎስ ኤዎስጣቴዎስ፤
ሳሙኤል ተክለ አልፋ በብኑዳ ኪሮስ፡፡

✝ 5 ነገሮችን
    1, 🛑አላማ

    2 ,🛑እምነት

   3,🛑ጥረት
    4 🛑ጥንቃቄ
     5🛑ጽናት
@9ኙ የቅድስና መንገዶች

፩👉ሃይማኖት
፪👉ጾም
፫👉ጸሎት
፬👉ስግደት
፭👉ምጽዋት
፮👉ፍቅር
፯👉ትህትና
፰👉ትዕግስት
፱👉የዋህነት

ንስሐ የተጣመመውን ያቀናል።በኃጥያት የቆሸሸውን ያነጻል፤ንስሐ ለሚገቡ ሁሉ የመላዕክት ንጹሕ ልብስ ይሰጣችኃል

ዝክረቅዱሳን ማኅበረ ቅዱስ ዳዊት

"ፍቅር ያጌብረኒ ከመ እንግር ዜናሆሙ ለቅዱሳን"::/የቅዱሳንን ዜና(ታሪክ) እንድመሰክር ፍቅር ያስገድደኛል::
       አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ /መጽሐፈ ምሥጢር
https://t.me/enabib


†††እንኳን ለታላቁ ሊቅና ጻድቅ ቅዱስ አንስጣስዮስ እና አቡነ ዓምደ ሥላሴ ዓመታዊ የዕረፍት በዓል በሰላም አደረሳችሁ፤ አደረሰን። †††

††† በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! †††

††† ቅዱስ አንስጣስዮስ ሊቅ †††

††† ቅዱስ አንስጣስዮስ በ4ኛው ክ/ዘመን የተነሳ ሶርያዊ የነገረ መለኮት ሊቅ: ገዳማዊ ጻድቅና የመንበረ አንጾኪያ ሊቀ ዻዻሳት ነበር:: ቅዱሱ ርጉም አርዮስን ካወገዙ 318ቱ ቅዱሳን ሊቃውንት አንዱ ነው:: በወቅቱ ታላላቅ ሊቃነ ዻዻሳት ሱባኤውንና ጉባኤውን የመሩ ሲሆን አንዱ ይህ ቅዱስ ነው::

ከ 5 ዓመታት በሁዋላም ብዙ ድርሳናትን ጽፎ: ሐዋርያዊ አገልግሎቱን ፈጽሞ በ330 ዓ/ም አርፏል:: ያረፈው ግን አርዮሳውያን ባቀረቡት ክስ በሃሰት ተመስክሮበት በግፍ ተሰዶ ነው:: ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ ስለ ውለታው የውዳሴ ድርሳን ጽፎለታል::

††† አቡነ ዓምደ ሥላሴ †††

††† እኒህ ታላቅ ጻድቅ ሐዋርያዊ አባት አቡነ ዓምደ ሥላሴ የትውልድ ሃገራቸው ጎጃም ሲሆን የተወለዱት በዚሁ ዕለት (የካቲት 27) ነው:: ጻድቁ በአጼ ሱስንዮስ (በ17ኛው መቶ ክ/ዘ) የነበሩ ድንቅ ሠሪ : ተአምረኛና ገዳማዊ አባት ናቸው::

የካቲት 16 ቀን መንኩሰው ወደ ተጋድሎ ገብተዋል:: በዋልድባ በነበራቸው ቆይታም እመቤቴ ኪዳነ ምሕረት የካቲት 16 ቀን እንድትከበር ማድረጋቸውም ይነገራል:: ጻድቁ በሌሎች ገዳማትም የነበሩ ሲሆን ዛሬም ድረስ ረድኤታቸው የሚደረግበት : ስማቸው የሚጠራበት ገዳም ግን ማኅበረ ሥላሴ ይባላል::

ገዳሙ የሚገኘው በሃገራችን ሰሜን ምዕራብ አቅጣጫ : በመተማ በርሃ ውስጥ ነው:: ይህንን ቅዱስ ገዳም የመሠረቱትም ራሳቸው አባ ዓምደ ሥላሴ ናቸው:: ገዳሙ ዛሬም ብዙ ምሑራንና መናንያን ያሉበት : በደህና ሁኔታም የሚገኝ ነው:: ግን በርሃውን የኔ ብጤ ደካማ ሰው የሚችለው አይደለም::

ስለ ጻድቁ ዓምደ ሥላሴ ከሚነገሩ ታሪኮች ቅድሚያውን የሚይዘው የተዋሕዶ ጠበቃነታቸው ነው:: በ1603 ዓ/ም ዼጥሮስ (ፔድሮ) ፓኤዝ የሚባል ካቶሊካዊ እሾህ ወደ ሃገራችን ገብቶ ነበርና ንጉሡን ሱስንዮስን አባብሎ ተዋሕዶን አስካዳቸው:: ነገሩ ውስጥ ለውስጥ ሲበስል ቆይቶ በ1609 ዓ/ም በመገለጡ እነ ራስ ዮልዮስ ለሃይማኖታቸው ጠዳ ላይ ተዋግተው ግንቦት 6 ቀን ተሰው::

ይህ ነገር ሲሰማ ወንድ ሴት : ትልቅ ትንሽ ሳይመረጥ በገጠሩም : በከተማውም : በገዳሙም ያሉት ሁሉ የተዋሕዶ ልጆች መንቀሳቀስ ጀመሩ:: 7 ዓመታት እንዲህ አልፈው በ1616 ዓ/ም ግጭቱ በይፋ ተጀመረ::

"ተዋሕዶን ካልካዳችሁ" በሚል በቀን እስከ 8,000 ሰው በሰይፍ ታረደ:: ይህን ያደረጉት ደግሞ አልፎንሱ ሜንዴዝ : ንጉሡ ሱስንዮስና ጀሌዎቻቸው ነበሩ::

በጊዜውም ከቤተ መንግሥት እነ ንግሥት ወልድ ሰዓላ (የሱስንዮስ ሚስት) : ከጻድቃን አበው ዘርዓ ቡሩክ ዘግሺ : ሐራ ድንግል ዘደራ : ምዕመነ ድንግል ዘጩጊ : ዓምደ ሥላሴ ዘማኅበረ ሥላሴ . . . ከቅዱሳት እነ ፍቅርተ ክርስቶስ : ወለተ ዼጥሮስ : ወለተ ዻውሎስ : እኅተ ዼጥሮስ . . . ለሃይማኖታቸው ተዋሕዶ ጥብቅና ቆመው ሕዝቡን አስተማሩ:: መከራም ተቀበሉ::

ብዙ ኢትዮዽያውያን የመከራ ጽዋን ተጐንጭተው ለክብር ከበቁ በሁዋላ የእግዚአብሔር ፍርድ ተገለጠ:: በጻድቃኑ እነ አባ ዓምደ ሥላሴ ሐዘን ንጉሡ ታመመ:: ምላሱ ተጐልጉሎ ወጣ::

በዚህ ጊዜ አቤቶ ፋሲለደስ ለአባ ዓምደ ሥላሴና ለሌሎቹ ቅዱሳን "አባቴን አድኑልኝ! ተዋሕዶም ትመለስ" አላቸው:: ጻድቁም ከባልንጀሮቻቸው ጋር ጸልየው ንጉሡን አዳኑት:: በፈንታውም ይህንን አሳወጁ::

††† ፋሲል ይንገሥ!
ሃይማኖት (ተዋሕዶ) ይመለስ!
የሮም ሃይማኖት ይፍለስ! †††

ከዚህ በሁዋላ በ1624 ዓ/ም ፋሲል ሲነግሥ አባ ዓምደ ሥላሴ ለገዳማቸው ብዙ ቦታ አስከልለው : በተጋድሎ ኑረው በዚህች ቀን ዐርፈዋል::

††† አምላከ ቅዱሳን በቀናችው እምነት ተዋሕዶ ሁላችንም እስከ ፍጻሜ ዘመናችን ያጽናን:: ከበረከተ ቅዱሳንም ይክፈለን::

††† የካቲት 27 ቀን የሚከበሩ ዓመታዊ የቅዱሳን በዓላት
1.አባ አንስጣስዮስ ርቱዓ ሃይማኖት (ዘአንጾኪያ)
2.አቡነ ዓምደ ሥላሴ

††† ወርኀዊ በዓላት
1.የጌታችንና አምላካችን መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ በዓለ ስቅለት
2.አቡነ መብዐ ፅዮን ጻድቅ
3.ቅዱስ መቃርስ (የመነኮሳት ሁሉ አለቃ)
4.ቅዱስ ፊቅጦር ሰማዕት
5.ቅዱስ ያዕቆብ ዘግሙድ
6.ቅዱስ ገላውዴዎስ ሰማዕት (ንጉሠ ኢትዮዽያ)
7.ቅዱስ ቢፋሞን ጻድቅና ሰማዕት

††† "የተጠራችሁለት ለዚህ ነው:: ክርስቶስ ደግሞ ፍለጋውን እንድትከተሉ ምሳሌ ትቶላችሁ ስለ እናንተ መከራን ተቀብሏልና:: እርሱም ኃጢአት አላደረገም:: ተንኮልም በአፉ አልተገኘበትም:: ሲሰድቡት መልሶ አልተሳደበም:: መከራንም ሲቀበል አልዛተም . . . እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ::" †††
(1ዼጥ. 2:21-25)

††† ወስብሐት ለእግዚአብሔር †††


#በከንቱ_እንዳንደክም_መጾም_እንደሚገባን_እንጹም

👉 በመጾም እየደከምን ሳለ የጾም አክሊልን ካላገኘን፥ እንዴትና በምን ዓይነት አኳኋን ይህን ልንፈጽመው እንደሚገባው ልንረዳ ያስፈልጋል፡፡ ፈሪሳዊዉም ጾሞ ነበርና፤ ከዚያ በኋላ ግን ወደ ቤቱ የኼደው ባዶ እጁንና የጾሙን ፍሬ ሳያገኝ ነውና (ሉቃ.18፡12)፡፡

👉 ቀራጩ ደግሞ በአንጻሩ አልጾመም ነበር፤ ነገር ግን ከጾመው ፈሪሳዊ ይልቅ በእግዚአብሔር ዘንድ ተቀባይነትን ያገኘው እርሱ ነው፡፡ ይህም የኾነበት ምክንያት [ቀራጩ ባይጾምም ተጠቀመ፤ በመፃዒ ሕይወቱም ጾም አላሻውም ለማለት ሳይኾን ከተአምኖ ኃጣውእ ጋር ሌሎች ግብራት ካልተከተሏት በቀር ጾም ረብ ጥቅም እንደሌላት እና ትሕትና የጾም አጣማጅ መኾኑን የምትሠምረው ከትሕትና ጋር መኾኑን እንድታውቅ ነው፡፡

👉 የነነዌ ሰዎች ጾመዋል፤ የእግዚአብሔር ምሕረትንም አግኝተዋል (ዮና.3፡10)፡፡ እስራኤላውያንም ጾመው ነበር፤ ነገር ግን እያጉረመረሙ ተመለሱ እንጂ በመጾማቸው አንዳች ጠቀሜታን አላገኙም (ኢሳ.58፡3-7፣ 1ኛ ቆሮ.9፡26)፡፡

ስለዚህ እንዴት መጾም እንዳለባቸው ለማያውቁ ሰዎች የጾም ጉዳቱ ትልቅ ነውና በጥርጣሬ እንዳንኼድ፣ እንዲሁ አየርን እንዳንደልቅ፣ እንዲሁ ከጨለማ ጋር እንዳንጋደል፥ ይህን የምናከናውንባቸውን ሕጎች ልንማር ያስፈልገናል፡፡

👉 ጾም መድኃኒት ናት! አወሳሰድዋን በትክክል ላላወቁ ግን ጥቅም የላትም፡፡ ይህችን መድኃኒት የሚወስድ ሰው በየስንት ሰዓቱና በምን ያህል መጠን እንደምትወሰድ፣ ለምን ዓይነት በሽታ እንደምትጠቅም፣ በየትኛው አከባቢና የአየር ኹናቴ እንደምትወሰድ፣ ከእርሷ ጋር የሚኼዱና የማይኼዱ ምግቦችን እንዲሁም ከእርሷ ጋር የማይስማሙ ሌሎች ነገሮችን ለይቶ ማወቅ አለበት፡፡

👉 እነዚህን ግምት ውስጥ አስገብቶ የማይወስዳት ሰው ግን ከጥቅሟ ይልቅ ጉዳቷ ታመዝንበታለች፡፡ አንድ በሐኪም የታዘዘልንን የደዌ ዘሥጋ መድኃኒት እንዲያሽለን ስንፈልግ በጥንቃቄ ልንወስደው ያስፈልጋል፤ የነፍሳችንን ደዌና በአእምሮአችን ውስጥ ያሉ ቁስሎችን ለመፈወስ ብለን በምንወስደው መድኃኒት ደግሞ ከዚህ የበለጠ መጠንቀቅ ይገባናል፡፡

© ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ፣ በእንተ ሐውልታት መጽሐፍ፣ ድርሳን 3፥8

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.