EOTC ቤተ መጻሕፍት


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


ይህ Channel የኢ/ኦ/ተ/ቤ/ያን የሆኑ ቅዱሳት መጻሕፍት፤ ስብከትች እንዲሁም የተለያዩ ለአብነት ትምህርት የሚሆኑ በድምፅ ፤ይሁን በጹሁፍ እንዲሁም በ Video ሚለቀቅበት Channl new
ተጨማሪ ወይም ሚፈልጉትን መፃህፍት
ብለው ይጠይቁን
ማስታወቂያም እንሰራለን በውስጥ መስመር ይጠይቁን
የሰማነዉን እንናገራለን!
ያየነዉን እንመሰክራለን!

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


ተ҈ ዋ҈ ህ҈ ዶ҈ dan repost
🔔✝ ከመምህራን የማንን ትምህርት ማግኘት ይፈልጋሉ?👇

┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር ምሕረተአብ አሰፋ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር ዘበነ ለማ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር ሄኖክ ኃይሌ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር ዮርዳኖስ አበበ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 አባ ገብረ ኪዳን
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር ያረጋል አበጋዝ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔መጋቢ ሐዲስ እሸቱ አለማየሁ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔 መምህር እዮብ ይመኑ
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔መምህር ገብረ እግዚአብሔር
┗━━━━━━━━━━━━━━┛
┏━━━━━━━━━━━━━━┓
🔔መምህር አባ ገብረ ኪዳን
┗━━━━━━━━━━━━━━┛

🔗የሁሉንም መምህራን ትምህርት ለማግኘት🔔
🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧🫧


የማርያም አዳራሽ - መርጡለ ማርያም !

ባሕር ዳር: ጥር 21/2017 ዓ.ም (አሚኮ) በጎጃም ከሚገኙት አያሌ ቅዱሳት ገደማት መካከል አንዷ የታላቋ እና የጥንታዊቷ ርዕሰ ርዑሳን መርጡለ-ማርያም ገዳም ናት።

ርዕሰ ርዑሳን መርጡለ ማርያም ገዳም የምትገኘው በጎጃም በእነብሴ ሳር ምድር ወረዳ ዋና ከተማ መርጡለ-ማርያም ነው።

መርጡለ-ማርያም ትርጉሙ የማርያም አዳራሽ ማለት ነው። ርዕሰ ርዑሳን መርጡለ ማርያም ገዳም አሁን የያዘችውን የስም መጠሪያ ከመያዟ በፊት በተለያዩ ዘመናት አራት ጊዜ የስም መለዋወጦች አጋጥሟታል።

መጀመሪያ ሀገረ ሰላም ቀጥሎ ሀገረ እግዚአብሔር ተብላለች። ከዚያም ጽርሐ አርያም ተብላ ተጠርታለች በመጨረሻም አሁን የምትጠራበትን መርጡለ ማርያም የሚለውን ስያሜ አግኝታለች።

ይች ታላቅ እና ጥንታዊት ገዳም የተመሠረተችው ከእስራኤሉ ንጉሥ ሰሎሞን እና ከኢትዮጵያዊት ንግሥት ሳባ (ማክዳ) የተወለደው ቀዳማዊ ምኒሊክ ይዟቸው በመጣ ፫፻፲፰ (318) የኦሪት ካህናት በ4500 ዓመተ ዓለም ነው።

ወደ ዚች ቦታ የመጡት የኦሪት ካህናት መሥዋዕተ ኦሪትን በመሰዋት የኦሪትን አምልዕኮት ሲፈጽሙ ኖረዋል። መርጡለ ማርያም በኢትዮጵያ መስዋዕተ ኦሪት ሲሰዋባቸው ከነበሩት አራቱ ጥንታዊ አብያተ ክርስቲያናት ማለትም አክሱም ጽዮን፣ ተድባበ ማርያም እና ጣና ቂርቆስ መካከል አንዷ ነበረች፡፡

ገድለ አብርሃ ወ አጽብሃ እና ገድለ አባ ሰላማ ከሳቴብርሃን እንደሚያስረዱት ሕሩያን ነገሥታት አብርሃ ወ አጽብሃ ከጳጳሱ አባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን ጋር በመኾን በ፫፻፴፫ (333) ዓ.ም ዓባይን ተሻግረው ጎጃም ምድር መርጡለ ማርያም ደረሱ።

በዚህ ቦታ ሕዝበ ክርስቲያኑን ወንጌል አስተምረው መክረው ከኦሪት ወደ ሐዲስ ከአምልኮተ ጣኦት ወደ አምልኮተ እግዚአብሔር መልሰው ካጠመቁ በኋላ ሕዝበ ክርስቲያኑ አምልኮቱን የሚፈጽምበት ቤተ ክርስቲያንን ለመሥራት አሰቡ።

ቦታው ላይ የሚያምር ቤተ ምኩራብ ስለ ነበር ይህንን ለታሪክ ትተን ሌላ ቦታ ላይ እንሥራ በማለት በስተምሥራቅ አሻጋሪ ካለው ተራራ አሁን ግንብ ወሬ እየተባለ ከሚጠራው ኮረብታ ላይ ቁፋሮ ጀመሩ።

ነገር ግን መሬቱ የእሳት ትንታግ እየተፋ አልቆፈር አለ። በመኾኑም በዚህ ቦታ ቤተ ክርስቲያን እንሠራ ዘንድ እግዚአብሔር አልፈቀደም። ፈቃደ እግዚአብሔርን እናውቅ ዘንድ ለ፫ (3) ተከታታይ ቀናት ሱባኤ እንግባ በማለት በ፭ (5) በአካባቢው ባሉ የተለያዩ ኮረብታዎች ሱባኤ ገቡ።

ሱባኤ የገቡባቸው ከረብታዎችም፡-
👉የኦሪቱ ሊቀ ካህን አብኒ ኮረብታ
የሐዲሱ ሹም ሐዲስጌ ኮረብታ
👉የጳጳሱ አቡነ ሰላማ ሰላምጌ ኮረብታ
👉በንጉሥ አብርሃ አብርሂ ኮረብታ
👉በንጉሥ አጽብሃ ዜነዎ ኮረብታ ላይ እንደነበሩ ይነገራል

ንጉሥ አጽብሃም ከሁሉም አስቀድሞ ወደ አባ ሰላማ ከሳቴ ብርሃን በመሄድ ያየውን ራዕይ ተናገረ። ሌሎችም መጥተው ያዩትን ሁሉ ተናገሩ አባ ሰላማም ይህንን ራዕይ ያዩ መኾናቸውን ነገሯቸው። ሁሉም በአንዲት ሌሊት አንድ ዓይነት ራዕይ አዩ።

ያዩት ራዕይም « ዐሥራ ሁለት በሮች ያላት አንድ አምደ ብርሃን የቤተ መቅደሱ መሠረት ከተጀመረበት ኮረብታ ተነስታ እያበራች የጥንቱ ቤተ ምኲራብ ከሚገኝበት ጽርሐ አርያም አምባላይ ስታርፍ » ነበር፡፡

ጧት ወደ ቦታው ሲሄዱ የጥንቱ አስደናቂው ቤተ ምኩራብ መሬት ውስጥ ተቀብሮ ለጥያለ አረንጓዴ ሜዳ ኾኖ አገኙት፡፡

ነገሥታቱ አብርሃ ወ አጽብሃ በቦታው ቤተ መቅደስን ይሠሩ ዘንድ ወደዱ። በወርቅ እና በእንቁ አምዶችን እና አረፍቶችን ልዩ አድርገው በማስጌጥ የማርያምን ቤተመቅደስ ሠሩ።

ሥርዓትንም በመደንገግ ካህናትን ዲያቆናትን እንዲሁም ሁሉንም ሊያሥተዳድር የሚችል ሊቀ ካህናት ርዕሰ ርዑሳን ብለው ሾሙ። መቅደሷንም መርጡለ ማርያም ብለው ሰየሟት።

ንጉሥ አብርሃ ወ አጽብሃም እግዚአብሔር በመራቸው መሠረት በጳጳሱ በአባ ሰላማ አስባርከው በጽርሐ አርያም አምባላይ አስደናቂውን ባለ ፲፪ (12) ቤተመቅደስ ባለ ፩ (1) ፎቅ ቤተ መቅደስ ሠርተው በወርቅ በእንቁ በከበሩ ማዕድናት አስጊጠው ጥር ፳፩ (21) ቀን የእመቤታችንን ጽላት በደማቅ ሥነ ሥርዓት አስገብተዋል።

ይህ ቤተ ክርስቲያን እጅግ የተለየ በልዩ ልዩ ቅርፅ ያጌጠ በወርቅ እና በእንቁ የተለበጠ አስደናቂ የጥበብ አሻራ ያረፈበት ነበር። ይህ ቤተ መቅደስ በዮዲት ጉዲት ዘመን በ፰፻፵፪ (842) ዓ.ም ተቃጥሏል።

በ፰፻፹፪ (882) ዓ.ም የነገሠው አንበሳ ውድም በዮዲት የተቃጠለውን ቤተ ክርስቲያን እንደገና አሠርቶታል። ይህንን ቤተ ክርስቲያን ዐፄ በእደ ማርያም በ፲፬፻፷ (1460) ዓ.ም አሳድሶታል። ባለቤቱ ንግሥት እሌኒ ደግሞ የአንባውን ዙሪያ አሠርታለች። አሁንም የገዳሟ ዙሪያ የእሌኒ ውድሞ ይባላል።

ገድለ አብርሃ ወ አጽብሃ፣ ገድለ አባ ሰላማ ከሳቴብርሃን እና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን የተሠራ ዘጋቢ ፕሮግራም እንደሚያስረዳው መርጡለ ማርያም በዋጋ የማይተመን ከፍተኛ የቅርስ ክምችት ያላት ገዳም ናት፡፡

እነዚህ ውድ ቅርሶች በመርጡለ ማርያም ሙዚየም ውስጥ የሚገኙ የአብርሃ ወአጽብሃ የወርቅ መስቀል፣ በ445 ዓ.ም የተጻፈ ግዕዙን በግዕዝ የሚተረጉም አርባዕቱ ወንጌል፣ የአጼ በእደ ማርያም ራስ ቁር እና የወርቅ ለምድ፣ የንግሥት እሌኒ የክብር ካባ እና የብር ዋንጫ፣ የብር እና የወርቅ መስቀሎች፣ የወርቅ አክሊሎች፣ የወርቅ ከበሮ፣ የአጼ ገላውዲዮስ ዳዊት እና ካባ፣ የብራና መጻሕፍት እና የመሳሰሉትን ለአብነት መጥቀስ ይቻላል፡፡

ጥር 21 የሚከበረው በዓለ አስተርእዮ ማርያም የመርጡለ ማርያም ልዩ የክብረ በዓል ቀን ነው፡፡ አስተርእዮ ማርያም በመርጡለ ማርያም በልዩ ልዩ ሃይማኖታዊ ክዋኔዎች የሚከበር ደማቅ በዓል ነው፡፡

@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot


የደቡቧ ኮከብ ብርብር ማርያም= የኦሪትና የሀዲስ ኪዳን ማህተም
~~~~~~~

የደቡቧ የአጥቢያ ኮከብ በመባል የምትታወቀው ብርብር ደብረ ማርያም ገዳም የምትገኘው በጋሞ ዞን በምዕራብ ዓባያ ወረዳ ቦላ ሔራ ቀበሌ ልዩ ስሙ ደጋ ብርብር እየተባለ በሚጠራው ከፍተኛ ቦታ ላይ ነው፡፡

ደብረ ማርያም ብርብር ገዳም ቀደም ሲል በኦሪት ቤተ መቅደስ የተተከለችው ከጌታችንና መድሃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅድመ ልደት 400 ዓመት አካባቢ ነበር።

በሀገራችን ኢትዮጵያ መሥዋዕተ ኦሪት ከሚሰዋባቸው ትምህርተ ብሉይ ከሚሰጥባቸው አክሱም ጽዮን፣ ተድባብ ማርያም፣ መርጡለ ማርያምና ጣና ቂርቆስ አብያተ መቃድስ ጋር በኦሪቱ ሥርዓትና በምኩራብ በአይሁድ ደንብ ትተዳደር ነበር።

በዘመነ ሐዲስ በአምስተኛው መቶ ክፍለ ዘመን አጋማሽ ላይ ደግሞ የቤተ መቅደስዋን የጥንት ታሪክና ዝና የሚያውቁት አጼ ገብረ መስቀል ብርብር በተባለችው ቤተ መቅደስ ሥርዓት ሐዲስ ዘመንን የሚመለከት ታቦት ገብቶ ሊወደስባትና ሊቀደስባት እንደሚገባ አስበው በታቦተ ማርያም ስም ቅዱስ ያሬድ እና ጻድቁ አቡነ አረጋዊን ታቦተ ማርያምን አስይዘው በአያሌ ሠራዊት ታጅበው ከአክሱም ጽዮን በብዙ ጉዞና ድካም ወደ ቦታው ደረሱ።

ግንቦት 21 ቀን ጻድቁ አቡነ አረጋዊ ቤተ መቅደሱን በሜሮን አክብረው ታቦተ ማርያምን አስገብተው ቅዳሴ ቤቷን አከበሩ።

በዚህ መሠረት አገልግሎቷን ከኦሪት እስከ ሐዲስ ኪዳን ስትቀጥል የደቡብ ኢትዮጵያ የሃይማኖት ማዕከል
በመባል የምትገለጸው ጥንታዊቷ ደብረ ማርያም ብርብር ገዳም በየዘመኑ የቤተክርስቲያናችን ላይ የሚነሱ አጽራረ አብያተ _ ክርስቲያናት ታሪኳን ለማጥፋት ቢጥሩም በተለያዩ ጊዜያት የተለያዩ ድንቅ ተዓምራትን በማድረግ ለዚህ ትውልድ ደርሳለች።

አናኒያንና አዛሪያን የሚባሉ ሊቃነ ካህናት ታቦተ ጽላቱን ከኢየሩሳሌም ቀይ ባህርን አሻግረው ከአክሱም ታቦተ ፅዮን ጋር እንዳመጧት ይነገራል፡፡
ብርብር ማርያም በምትባለው የታሪክ የእውነት የመመረጥ እና የበረከት ዶሴ ውስጥ በምኩራብ ስርዓት በዘመነ ኦሪት ከነበሩት ከሊቃ ካህኑ ሳዶቅ ልጅ ካህኑ አዛርያስ እስከ ጉባኤ ኒቂያ አዘጋጅ ከሆነው የንግስት እሌኒ ልጅ ንጉስ ቆስጢንጢኖስ ድረስ በድምቀት ጎልተው ይነበባሉ።

በኢትዮጽያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ታሪክ የመጀመርያው ሊቀጻጳስ ከሆኑት ከአቡነ ከሳቴ ብርሃን (ፍሬምናጦስ ) እስከ ከሳቱ ቅዱሳን አካል ከሆኑት አቡነ አረጋዊ ድረስ በእዚህች ገዳም በረከት አፈስው ሱባኤ ይዘው ፀሎትና ቡራኪያቸውን አስቀምጠው ለትውልድ አልፈዋል።

የዜማው ሊቅ ስውሩ አባታችን ቅዱስ ያሬድ በመላእክት ጣዑመ ዜማ በሰማያውያን ለዛ በእዚህች ገዳም የምስጋና መሰዋት ዘርግቶ አልፎባታል።
በእዚህች ገዳምን ፃዲቁ አባታችን አቡነተክለሐይማኖት መንበረ አድርገዋት የወንጌል ዘርን በደቡብ ኢትዮጽያ ውስጥ ዘርተዋል።

ከኢዛና ሳይዛና እስከ አፄ ልብነድንግል፤ከአፄ ገብረመስቀል እስከ አፄ ዘርያዕቆብ ፤ ከአፄ ምኒልክ እስከ ጃንሆዬ ድረስ እጅ መንሻ እና መባ ለደቡቧ ኮከብ ለሆነችው ለብርብር ማርያም ሰጥተዋታል በረከት አፍሰውባታል።
በሀገር ላይ መከራ እና ወረራ ተከስቶ ጠላቶች በተነሱበት ጊዜ ከታቦተ ጽዮን እስከ ግማደ መስቀል በእዚህች ገዳም ሰንብተው ህዝቡን ባርከው ምድሯን ቀድሰው አልፈዋል።

እንግዲህ የእዚህች ገዳም ስም የደቡቧ ኮከብ ርዕሰ አድባራት ወገዳማት ሰማያዊት ጽዮን ብርብር ማርያም ትባላለች።

በህገ ኦሪት ከክርስቶስ ልደት 800 ዓመት በፊት በደብተረ ደንኳን በሊቀ ካህኑ ሳዶቅ ልጅ ካህኑ አዛርያስ ህገ እግዚአብሔር ተዘርግቶባታል።
በ1440 ዓ.ም አፄ ዘርዓ-ያዕቆብ ከትግራይ፣በ530 ዓ.ም አፄ ልብነ-ድንግል እንዲሁም በ1961 ዓ.ም ግርማዊ ቀዳማዊ አፄ ኃይለሥላሴ ወደ ቤተ-ክርስቲያኗ በመምጣት መሳለማቸውና ድጋፍ እንዲሆን የሰጧቸው የተለያዩ ንዋዬ ቅድሳትን በገዳሟ ይገኛሉ።

የብርብር _ ማርያም ገዳም ከጋሞ ዞን ርዕሰ ከተማ አርባምንጭ 67 ኪ.ሜ ርቀት እንዲሁም ከምዕራብ አባያ ወረዳ ከተማ ብርብር 82 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ትገኛለች፡፡
ከተለያዩ የሀገሪቱ አከባቢዎች የሚጡ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታይ ምዕመናን አዘውትረው ፀሎት የሚያደርሱበት ስፍራ ነው፡፡

ጥንታዊና ታሪካዊ የሆኑ በርካታ ንዋየ ቅድሳትና መንፈሳዊ ቅርሶች ያቀፈች ገዳም ናት።
በዚህች ገዳም በርካታ ሀገርንና ህዝብን ሊጠቅሙ የሚችሉ የባህልና የቅርስ ማስረጃዎች ይገኛሉ።
ይህንንም ከግምት በማስገባት የኢፌድሪ ቅርስ ጥናትና ጥበቃ ባለስልጣን በሀገር ቅርስነት መዝግቦ በተለያዩ ጊዜያቶች እየተንከባከባትም ይገኛል።

የገዳሟ የቅርስ ይዘትን ስንመለከት ፦ በርካታ የብራና መፃህፍት፣ ከነገሥታት የተበረከቱ ጥንታዊ መፅሐፍት ፣ የቅዳሴ መስቀሎችና ሌሎች ቅርሶች ይገኛሉ።
የዚህችን ገዳም ታሪካዊነት ከሚያሳዩ የቁም ማስረጃዎች ዋና ዋናዎቹ ገዳሟ በአካባቢው የጋሞ ቤት አሰራር መሠረት የተሰራ ሲሆን የህንጻው ባህላዊ የቤት አሰራርም ጥበብ አሁን ላይ ይዘቱን እንደጠበቀ ይገኛል፡፡

የብርብር ማርያም ገዳም በአሁኑ ወቅት በጥሩ ሁኔታ ላይ ብትሆንም ቅርሶቹ የሚገኙበት ሁኔታ ካላት ውድ ዘመን ተሻጋሪ ሀብት አንጻር ለአደጋ የተጋለጠ በመሆኑ ከትውልድ ወደ ትውልድ እንዲተላለፍ ዘመናዊ ቤተ-መዘክር ሊገነባለት ይገባል።
አክሱም ጽዮንን ተሳልመው ይሆናል፤ጣና ቂርቆስን ረግጠው ሊሆን ይችላል፤ከተድባባ እና መርጦለማርያምንም በረከት ቢያፍሱም መልካም ነው።

ነገር ግን ብርብር ማርያም የምትባል አንድ ደቡቧዊር የህገ ኦሪትና ህገ ወንጌል ግምጃ ቤት በጋሞዎች መንደር አለች።

እሷ ትቀራችዋለች። ይሳለሟት፤ይርገጧት። በረከትና ቃልኪዷኗ ነፍስን አንጽቶ ስጋን የሚያከብር ነው።
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery


የሰማዕታት ውበት
             
Size:-59.9MB
Length:- 1:04:40

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot


የቸርነት በር
             
Size:-93.4MB
Length:-1:40:54

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot
@mezigebehayimanot














እንኳን አደረሳቹሁ
#ጥር21_አስተርእዮ_ማርያም_ ( #በዓለ_ዕረፍታ_ለማርያም_(ለሶልያና )
#እመቤታችን_በ64_ዓመቷ_ጥር_21_በ49ዓም_ያረፈችበት_ዕለት_መታሰቢያ_ክብረ_በዓል_ነው፡፡
#ተናገራ_ዕዝራ_ተናገራ_ዳዊት_ዘመራ፤
#ዕዝራ_በመሰንቆ_ዳዊት_በበገና_እያጫወቷት፤
#ሳታውቀው_አለፈች_ያንን_መራራ_ሞት፡፡
፠ ጌታችን ለእናታችን ለቅድስት ማርያም ብዙ ቃልኪዳንን ከገባላት በኋላ፤ ቅድስት ነፍሷን ከክብርት ሥጋዋ ለይቶ በቃለ አቅርንት፥ በዝማሬ መላእክት አሳረጋት፡፡ ደቀመዛሙርቱንም ከያሉበት ደመና ጠቅሶ እመቤታችሁን ቅበሩ አላቸው፡፡ በአጎበር አድርገው እናትና  አባቷ  ወደተቀበሩበት  ወደ ጌቴ  ሴማኒ  ሲወስዷት  አይሁድ  አይተው፤  ልጇ ተነሳ፥ አረገ  እያሉ ሲያውኩን ኖሩ አሁን ደግሞ እሷ ተነሳች፥ አረገች እያለ ሉያውኩን አይደለምን? ንዑ ናዓውያ ሥጋሃ ለማርያም /ኑ ሥጋዋን እናቃጥልባቸው/ ብለው ተነሱ፤ ለዚሁም ከመካከላቸውም ታውፊኒያ የተባለውን የጎበዝ አለቃ መረጡ፤ እርሱም የአልጋዋን ሸንኮር ሊያቃጥል ሲይዝ የታዘዘ መልአክ መጥቶ ሁለት እጁን በሰይፍ ቀጣው፡፡ በድያለሁ ማሪኝ ብሎ ቢማፀናት እራሷን ዘምበል አድርጋ ቅዱስ ጴጥሮስን እንደነበረው  አድርግለት ብላ አዘዘችው፤ እርሱም እጁን አድኖለታል፡፡ ከዚህ  በኋላ ጌታችን ከመካከላቸው ነጥቆ ከገነት ከዕፀ ሕይወት ስር አኑሯታል፡፡ ….. ሐዋርያት የቀበሯት ግን ከ6 ወር በኋላ በነሐሴ 14 ነው  ‹‹ሞት በጥር ነሐሴ መቃብር እንዲሉ፡፡››ረፍታ ለሶልያና(ለማርያም)
ወረደ ወልድ ዲበ እምዲበ ልዕልና ወረደ፡፡
#ሶልያና_የእመቤታችን_የማርያም_ሌላ_ስሟ_ነው፡፡
*የእመቤታችንን ዕረፍት ሊቁ ቅዱስ  ያሬድም  ‹‹ሞትሰ  ለመዊት ይደሉ፥  ሞታ  ለማርያም የአጽብ ለኵሉ፡፡ /ሞት ለሚሞት ሰው ሁለ የተገባ ነው፥ የማርያም ሞት ግን ሁለን ያስደንቃል፡፡›› በማለት አደንቆ ጽፏል፡፡
*እንደየደብራችሁ ይትበሃል ትጠቀሙበት ዘንድ የላይ ቤት (የግምጃ ቤት ማርያም) አብነትና የታች ቤት(የበዓታ) አብነትን ሁለቱንም አዘጋጅተንላችኋል፡፡ መልካም ክብረ በዓል፡፡
**ክብረ በዓሉ በሃገራችንና በዓለማችን ክፍሎች ባሉ የእመቤታችን አብያተ ክርስቲያናት የሚከብሩ ቢሆንም ግን፤ በልዩ ሁኔታ እንደ ጎንደር አዘዞ ሎዛ ማርያም ባሉት አብያተ ክርስቲያናት ግን እንደ ጥምቀት በዓል፤ ከዋይዜማው ጀምሮ ወደ ጥምቀተ ተወርዶ በማደር ክብረ በዓሉ በልዩ ሁኔታ መከበሩን ልብ ይሏል::
@EotcLibilery
@EotcLibilery
@EotcLibilery
















እግዚአብሔርም ብርሃን ይሁን አለ
             
Size:-128.8MB
Length:-2:20:43

    በርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳን ግርማ
@Nigatu5
@Nigatu5
@Nigatu5

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.