Ethiopian university Students


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: Ta’lim


ኢትዮጵያ ዉስጥ ስለሚገኙ ሁሉም ዩኒቨርሲቲወች እና ኮሌጆች ትክክለኛ መረጃወችን የምታገኙበት ቻናል ነው!!! You tube channel 👇
https://youtube.com/@temari_podcast?si=hKrtNc5CAe7NwS2I

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Statistika
Postlar filtri


ሀገር አቀፍ የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራም የመውጫ ፈተና ዛሬ ይጠናቀቃል።

ፈተናው 5ኛ ቀኑ ላይ የሚገኝ ሲሆን፤ በዛሬው የጠዋት 2:30 መርሐግብር የነርሲንግ ፈተና እየተሰጠ ነው።

በጁምዓ ምክንያት ጠዋት 5፡30 የሚጀመረው የመውጫ ፈተና ወደ 7፡30 እንዲሁም ከሰዓት 8፡30 የሚጀመረው ፈተና ወደ 10፡30 ተቀይሯል።

የመውጫ ፈተና መጠናቀቅን ተከትሎ በሚኖሩ ቀጣይ ቀናት ውጤት እንደሚገለፅ ይጠበቃል።

በሌላ በኩል በመምህርነት ሙያ ከዲፕሎማ ወደ መጀመሪያ ዲግሪ የትምህርት ደረጃ ማሻሻያ ስልጠና በክረምት መርሐግብር ሲከታታሉ የቆዩ #መምህራን የመውጫ ምዘና ነገ ቅዳሜ የካቲት 1/2017 ዓ.ም እንደሚሰጥ መገለፁ ይታወቃል።

ምስል፦ ደምቢ ዶሎ ዩኒቨርሲቲ

@EthiopianUniversitystudents1


#Update

ነገ አርብ ጥር 30/2017 ዓ.ም በሚሰጡ የመውጫ ፈተና ላይ የሰዓት ለውጥ መደረጉን የተወሰኑ ዩኒቨርሲቲዎች እየገለፁ ነው፡፡

በዚህም ጠዋት 5፡30 ይጀምር የነበረው ፈተና ወደ ከሰዓት 7፡30 እንዲሁም ከሰዓት 8፡30 ይጀምር የነበረው ፈተና ወደ 10፡30 የተሸጋሸገ መሆኑ ተመላክቷል፡፡

ምስል፦ ሐረማያ ዩኒቨርሲቲ፣ ደብረ ብርሃን ዩኒቨርሲቲ፣ ዋቸሞ ዩኒቨርሲቲ እና ድሬዳዋ ዩኒቨርሲቲ

@EthiopianUniversitystudents1


የ2017 ኢንትራንስ ፈተና ዝግጅት ምን ይመስላል❓

https://youtu.be/7hSs-PTJyvs


Freshman Tricks dan repost
የ ጤና እና የ ኢንጂነሪንግ ዲፓርትመንቶች ንፅፅር / Health Bs Engineering Departments comparison 👇👇👇

https://youtu.be/JQRlyHMGJpM


#ExitExamSchedule #AAU

ሀገር አቀፍ የመውጫ ፈተና ከሰኞ ጥር 26/2017 ዓ.ም ጀምሮ እንደሚሰጥ ይታወቃል፡፡

በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የመውጫ ፈተና ለመፈተን የተመዘገባችሁ የፈተናው የመጀመሪያ ሁለት ቀናት መርሐግብር (ጥር 26 እና 27/2017 ዓ.ም) ከላይ ተያይዟል።

@EthiopianUniversitystudents1


#ExitExam

176 ሺሕ ተማሪዎች የመውጫ ፈተናን ለመውሰድ መመዝገባቸው ተገለጸ

👉ፈተናው ከጥር 26 እስከ 30 ድረስ ይሰጣል

ጥር 23/2017 (አሐዱ ሬዲዮ) በ2017 ዓ.ም አጋማሽ ላይ የሚሰጠውን የቅድመ ምረቃ ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተና ለመውሰድ 176 ሺሕ ተማሪዎች መመዝገባቸውን ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።

ፈተናውን በድጋሚ የሚወስዱትን ጨምሮ በጠቅላላው 176 ሺሕ ተማሪዎች የመውጫ ፈተናውን ይወስዳሉ ተብሎ እንደሚጠበቅ በትምህርት ሚኒስቴር የአካዳሚክ ጉዳዬች መሪ ስራ አስፈፃሚ ዶ/ር ኤባ ሚጀና #ለአሐዱ ገልጸዋል።

በዚህም መሰረት በኢትዮጵያ የሚገኙ በሁሉም የኒቨርሲቲዎች ፈተናው የሚሰጥ ሲሆን፤ ተጠሪነቱ ለትምህርት ሚኒስቴር ያልሆነው የመከላከያ ዩኒቨርሲቲ ጭምር በዚህ ፕሮግራም ተካታች መሆኑ ተጠቁሟል፡፡

የግል ኮሌጆችን በሚመለከት አሐዱ ላቀረበላቸው ጥያቄ ትምህርት ሚኒስቴር የግል ኮሌጆች ላይ ገብቶ ለመፈተን የሚያስችል መዋቅር እንደሌለው በማንሳት፤ ነገር ግን ተማሪዎች በአቅራቢያቸው በሚገኝ የመንግስት ተቋም በኩል መፈተን እንደሚችሉ ገልፀዋል።

የፈተና ቀኑ በተለያዩ ምክንያቶች ዘግይተው ትምህርት የጀመሩትን ዩኒቨርሲቲዎች ታሳቢ ያደረገና በቂ ዝግጅት ማድረጋቸው ከተረጋገጠ በኋላ መወሰኑን ተናግረዋል።

ፈተናውን ለመስጠት ታቅዶ የነበረው ጥር 14 እና 15 የነበረ ቢሆንም፤ ሁሉም ዩኒቨርስቲዎች እኩል ትምህርት ባለመጀመራቸው ወደ ጥር 26 ቀን 2017 ዓ.ም. እንዲሸጋገር መደረጉን ገልጸዋል፡፡

በዚህ የፈተና ፕሮግራም ተንቀሻቃሽ ስልክና የወረቀት ፅሁፍ ይዞ መገኘት ፈፅሞ #የተከለከለ መሆኑን የገለጹት የአካዳሚክ ጉዳዮች መሪ ሥራ አስፈፃሚው፤ "ተፈታኞች መታወቂያ መያዝና ከፈተና ፕሮግራሙ 30 ደቂቃ ቀድሞ ቦታው ላይ መድረስ ይጠበቅባቸዋል" ብለዋል፡፡ የወጣው ፈተናም ከተማሩት በመሆኑ ሳይጨነቁ በተረጋጋ መንፈስ መስራት እንደሚገባቸው አሳስበዋል።

የዘንድሮው የዩኒቨርስቲዎች የመውጫ ፈተና ከዚህ በፊት ይሰጥ እንደነበረው ሙሉ ለሙሉ በኦንላይን የሚካሄድ ሲሆን፤ ከጥር 26 እስከ 30 ከሰኞ እስከ አርብ ባሉት አምስት ተከታታይ ቀናት እንደሚሰጥ አስታውቀዋል።

የተማሪዎች ፈተና እንደተጠናቀቀ ቅዳሜ ማለትም የካቲት 1 ቀን የመምህራንን ስልጠና ሲወስዱ የነበሩ መምህራን ፈተና ይወስዳሉ ተብሎ ይጠበቃል።

[ዘገባው የአሃዱ ሬድዮ ጣቢያ ነው]

@EthiopianUniversitystudents1




ማካካሻ_ትምህርት_REMEDIAL_ማስፈፀሚያ_ሰነድ.pdf
4.9Mb
📘የሪሜዲያል ማስፈፀሚያ ሰነድ ለ2016 ዓ.ም
📝ለዘንድሮም አንድ አይነት ሲሆን የተቀየረው የምዘና ሂደቱ ብቻ ነው።

@EthiopianUniversitystudents1


ዝምተኛው ገዳይ ካርበን ሞኖክሳይድ(CO) (የከሰል ጭስ)

✍ አብዛኞቻችን  በቤታችን ውስጥ ከሰል የማጨስ ልምድ አለን፡፡ ታዲያ ይህ በቤታችንን የምንጠቀምበት ጭስ በአግባቡና በጥንቃቄ ካልያዝነው ለዕድሜ ልክ ህመም ለሆኑት የአንጎል ውድመትና የልብ በሽታን ሲያጋልጥ ባስ ሲልም ሕይወታችንን ሊያሳጣን የሚችል አደገኛ ጋዥ ነው::

✍ እንደ አሜሪካ የበሽታዎች መቆጣጠሪያና መከላከያ ማእከል መረጃ መሠረት የከሰል ጭስ ወይም ካርበን ሞኖክሳይድ በአይን የማይታይና ሽታ አልባ መርዛማ ጋዝ ነው፡፡

👉ካርበን ሞኖክሳይድ የሚፈጠረው ጋዝ፣ዘይት፣ ከሰል ወይም እንጨት ሙሉ በሙሉ ተቃጥለው ባለማለቃቸው የሚፈጠር ነው፡፡

✍የእንጨት ከሰል (charcoal) የመኪና ጭስና ሲጋራ ይህንኑ ካርበን ሞኖክሳይድ በማመንጨት ይጠቀሳሉ፡፡ ከሰልን ጨምሮ የካርበን ምንጭ የሆኑ እንደ ጋዝ ስቶቭ፣ውሃ ማሞቂያ፣ የቤት ማሞቂያ፣የምግብ ማብሰያ ምድጃዎች በሙሉ በአግባቡ ካልተገጠሙ፣በአግባቡ ካልተጠገኑና ነፋስ የማያገኛቸው ጥብቅብቅ ያለቦታ ከተቀመጡ ችግሩን ሊያከትሉ ይችላሉ፡፡

✍የከሰል ጭስ ወይም ካርበን ሞኖክሳይድ ወደ ውስጣችን በምንስበብት ወቅት በቀጥተ በደማችን ውስጥ በመግባት የቀይ የደም ሕዋስ አካል የሆነውና ኦክስጅን ተሸክሞ ለለተያዩ የሰውነታችን ክፍል ከሚያደርሰው ሂሞግሎቢን ጋር በመቀላቀል ካርበኦክሲሄሞግሎቢን ይሆናል፡፡

👉ይህ ከሆነ በኃላ ደማችን ኦክሰጅን መሸከሙን ያቆማል፡፡ በዚህ የተነሳ ሕዋሳቶቻችንና የሕዋሳቶቸችን አነስተኛ ክፍሎች ይጎዳሉ፤ይሞታሉ፡፡ህይወታችንንም እናጣለን::

✅በመሆኑም  በከሰል ጢስ  ምክንያት በርካቶች በዝምታ እየሞቱ  በመሆኑ ጥንቃቄ እናድርግ የሚለው ምክራችን ነው::

@EthiopianUniversitystudents1


በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት 10 ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ ለማድረግ እየተሰራ ነው፡- ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ


በሚቀጥሉት ሁለት ዓመታት 10 ዩኒቨርሲቲዎችን ራስ ገዝ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ ገልጸዋል።

የዩኒቨርስቲዎች የቀጣይ የሪፎርም መዳረሻ ራስ ገዝ መሆን ነው ያሉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ፤በትምህርት ጥራት እና ተደራሽነት ላይ ያለውን ችግር ለመፍታት የተለያዩ የማሻሻያ ስራዎቸ መሰራታቸውን ተናግረዋል።

የትምህርት እና የምርምር ስራዎችን የበለጠ ለማጠናከር ራስ ገዝነት የተሻለ እድል ይፈጥራል ነው ያሉት።

ሚኒስትሩ የጎንደር ዩኒቨርስቲ የተመሰረተበትን 70ኛ ዓመት እና የጎንድር ዩኒቨርሲቲ አጠቃላይ ስፔሻላይዝድ ሆስፒታል 100ኛ ዓመት ክብረ በዓል ላይ ተገኝተዋል።

ጥራትን መሰረት አድርጎ የትምህርት ተቋማት ሃገር ተረካቢዎችና መሪዎችን በመቅረጽ ዩኒቨርሲቲዎች ከመቼውም ጊዜ በላይ ሊሰሩ ይገባል ብለዋል።

እስካሁን የተሰሩ ስራዎች እንዳሉ ሆነው በቀጣይ ሊሰሩ የሚገቡት ላይ ማተኮር ይገባል ብለዋል ሚኒስትሩ።

ዩኒቨርሲቲው በተለያዩ ዝግጅቶች የምስረታ በዓሉን እያከበረ ይገኛል።

የጎንድር ዩኒቨርሲቲ ኢትዮጵያ የራሷ የጤና ባለሙያዎች ያስፈለጓታል ተብሎ በ1942 በተነሳ ሃሳብ መነሻነት በተደረገ ጥረት 1947 ዓ.ም የጤና ባለሙያ ማሰልጠኛ ሆኖ መመስቱ የዩኒቨርስቲው ታሪክ ያሳያል።

@EthiopianUniversitystudents1


#BongaUniversity

በ2017 ዓ.ም ለአቅም ማሻሻያ ትምህርት (Remedial Program) ቦንጋ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች ሪፖርት ማድረጊያ ቀናት የካትቲ 1 እና 2/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል።

ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

➭ የ8ኛ ክፍል ካርድ ዋናውና ኮፒው፣
➭ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
➭ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቅያ ሰርትፍኬት ዋናውና ኮፒው፣
➭ ስድስት ፓስፖርት መጠን ፎቶግራፍ፣
➭ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ ትራስ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ።

@remedial_tricks


እጃችሁ ላይ ያላችሁን ማንኛውንም ነገር ካላችሁበት ቦታ ሆናችሁ መሸጥም ሆነ መግዛት የምትችሉበትን የቴሌግራም ቻናል እናስተዋውቃችሁ 👇👇👇

@Habesha_Gebeya1
@Habesha_Gebeya1


#Update

በ2017 ዓ.ም አጋማሽ የሚሰጠውን የቅድመ-ምረቃ ፕሮግራሞች የመውጫ ፈተና (Exit Exam) ዳግም ለመውሰድ ፍላጎት ያላቸው አመልካቾች ምዝገባ ከጥር 8-14/2017 ዓ.ም እንደሚከናወን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል፡፡

ለመመዝገብ 👉 https://exam.ethernet.edu.et

ፈተና የሚሰጥበትን ጊዜ በቀጣይ እንደሚያሳውቅ ሚኒስቴሩ ገልጿል፡፡

ከምዝገባ ጋር ተያይዞ ለሚኖራችሁ ጥያቄ ዘውትር በሥራ ሰዓት በተከታዮቹ አማራጮች ማብራሪያ መጠየቅ የምትችሉ መሆኑን ተገልጿል፡፡

Email: ngat@ethernet.edu.et
☎️ 0911824528 / 0913678404 / 0913949676 / 0910076453 / 0923106826 / 0913866717 / 0911335683

Note:
➫ የመፈተኛ User Name እና Password በመመዝገቢያ ፖርታል በኩል የሚላክ ይሆናል።
➫ የመመዝገቢያ ክፍያ ብር 500 በቴሌብር በኩል ብቻ መፈፀም ይኖርባችኋል፡፡
➫ ምዝገባ ማድረግ የሚቻለው በተጠቀሱት የምዝገባ ቀናት ብቻ ነው፡፡

@EthiopianUniversitystudents1


#AksumUniversity

በ2017 ዓ.ም ለአቅም ማሻሻያ ትምህርት (Remedial Program) አክሱም ዩኒቨርሲቲ አዲስ የተመደባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ቀናት ጥር 15 እና 16/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

የምዝገባ ቦታ፦
በዩኒቨርሲቲው ዋና ግቢ፣ አክሱም ከተማ

ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

➫ የ8ኛ ክፍል ፈተና የወሰዳችሁበት ማስረጃ ዋናውና ኮፒው፣
➫ የ12ኛ ክፍል ፈተና የወሰዳችሁበት ማስረጃ ዋናውና ኮፒው፣
➫ የ2ኛ ደረጃ የትምህርት ማስረጃዎች ዋናውና ኮፒው፣
➫ 3×4 የሆነ ስድስት ጉርድ ፎቶግራፍ፣
➫ የመኝታ አልባሳት እና የስፖርት ትጥቅ፣
➫ ማንነታቸሁ የሚገልፅ የታደሰ መታወቂያ፡፡

📘Join Us 👇👇

@EthiopianUniversitystudents1


በወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ አዲስ ለተመደባቹህ የሪሜዲያል (REMEDIAL) ተማሪዎች በሙሉ

ወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ለሪሜዲያል (REMEDIAL) የተመደባችሁ ተማሪዎች የመግቢያ ጊዜ ጥር 26-27/2017 ዓ.ም መሆኑን አውቃችሁ በተጠቀሱት ቀናት በአካል በመገኘት እንድትመዘገቡ እያሳሰብን ትምህርት የሚጀመረው ጥር 28/2017 ዓ.ም መሆኑን አውቃችሁ ዝግጅት እንድታደርጉ እናሳውቃለን፡፡

ማሳሰቢያ፡
ተማሪዎች ወደ ዩኒቨርሲቲው ስትመጡ የሚከተሉትን ይዛችሁ መምጣት ይጠበቅባችኃል፡፡
1ኛ. መሰናዶ ያጠናቀቃችሁበትን ሰርተፍኬት፣ ከ9ኛ እስከ 12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት፣ የ8ኛ ክፍል ካርድ ዋናውን ከማይመለስ አንድ ኮፒ ጋር እና አራት 3x4 ጉርድ ፎቶ ግራፍ፡፡
2ኛ. አንሶላ፣ ብርድ ልብስ እና የትራስ ጨርቅ ይዛችሁ መምጣት እንዳለባችሁ እናሳስባለን፡፡
3ኛ. ይህንን የመግቢያ ጊዜ አሳልፎም ሆነ ቀድሞ የሚመጣ ተማሪን ዩኒቨርሲቲው የማያስተናግድ መሆኑን እንገልፃለን፡፡

የወልቂጤ ዩኒቨርሲቲ ሬጅስትራር ዳይሬክቶሬት

𝚓𝚘𝚒𝚗 𝚞𝚜
@EthiopianUniversitystudents1


Freshman Mathematics unit 2 proof by using mathematical induction 👇👇

https://youtu.be/vDXXZ4-qggM


ለዘንድሮው ማትሪክ ከ9 እና 10 የግድ መነበብ ያለባቸው ወሳኝ ምዕራፎች /grade 9 and 10 entrance exam contents 👇👇

https://youtu.be/z9jdwQNaNJw


ማስታወቂያ
የድህረምረቃ ፕሮግራሞች (NGAT) የመግቢያ ፈተና ለመውሰድ የተመዘጋባችሁ በሙሉ ይህንን ሊንክ ( https://ngat.ethernet.edu.et) በመጫን መረጃ ማግኘት ትችላላችሁ።

@EthiopianUniversitystudents1


#Debark_University

በ2017ዓ.ም ለአቅም ማሻሻያ ትምህርት (Remedial Program) ደባርቅ ዩኒቨርሲቲ የተመደባችሁ ተማሪዎች የምዝገባ ጊዜ ጥር 29 እና 30/2017 ዓ.ም መሆኑን ዩኒቨርሲቲው አሳውቋል፡፡

📢 በቅጣት ምዝገባ የካቲት 1/2017 ዓ.ም ብቻ፡፡

👉 ለምዝገባ ስትሔዱ ልትይዟቸው የሚገቡ፦

➫ የ8ኛ ክፍል ፈተና ውጤት ዋናውና ኮፒው፣
➫ ከ9-12ኛ ክፍል ትራንስክሪፕት ዋናውና ኮፒው፣
➫ የ12ኛ ክፍል ማጠናቀቂያ ስርተፊኬት ዋናውና ኮፒው፣
➫ አራት 3×4 ጉርድ ፎቶግራፍ፣
➫ አንሶላ፣ ብርድ ልብስ፣ ትራስ ልብስ እና የስፖርት ትጥቅ።

👉 ትምህርት የካቲት 3/2017 ዓ.ም ይጀምራል ተብሏል፡፡

@EthiopianUniversitystudents1


ከዲግሪ በላይ TVET የተማረ 4 እጥፍ ደመወዝ ያገኛል ። ፕ/ር ብርሀኑ ነጋ የትምህርት ሚኒስትር

https://youtu.be/QTJNzfTFqzE

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.