👩◈ ሚስቴና አባቷ ◈👴🏻
ክፍል - ሰባት [፯]
✍ (በጥላሁን ተስፋዬ)
.
.
.
ዘወር ብዬ ወደአመላከተችይ አቅጣጫ ትመለከት እመንገዱ ዳር ላይ ታለ አንድ ስጋ ቤት ነጭ እተቀባ ግርግዳ ላይ የተሳለ ትልቅ ጥቁር በሬ ነው !
እንደው አንዳርጌ ሙት ነው እምልህ ብልጭጭ አለብይ!"•••••
ቲለኝ አልቻልሁም ወሬውን እስኪያከትም አፍኜ የያዝሁትን ሳቅ እንደ ሀምሌ መብረቅ አንባረቅሁት ።
ካካካካካካ ያንተስ ለጉድ ነው ጃል
እና ምን ይሻልሀል ? ብለው•••
ታድያ እሄ ባልና ሚሽት ታንድ ወንዝ ይቀዳሉ ያለ ሰው ጥሁፍን እንዲህ ብሎ ያስተካክልልይ
ባልና ሚሽት ታንድ ወንዝ ይቀዳሉ ተዳምጠው እና ተሳቷ ሚሽቱ በስተቀር ብሎ ያስተካክልልይ።
ይህን ማድረግ የማይችል ተሆነ ግን ተሚስቴ ያፋታ እና ታለወንዟ የሄደይውን የኔዋን ያምጣልይ።
ይህም ታልሆነለት ያለክዳና ታልገጠምክ እያለይ ቲላት እስፓናቶ ቲላት አንጎል ፋቶ እያረገይ
አወላልቃ ታጨርሰይ የኔ ታትሆን የሷ ላረችይ ሚሽቴ የራሷን ግጣም አፈላልጎ ይስጣት።ይህም ተተሳነው ደግሞ•••
በእሳት ምላሷ ተጨጓራዬ ዥምራ በሷ ንዴት ስጠጣ ወደ ጉበቴ ፣ በሷ ብሶት ታጨስ ወደሳምባዬ እየመጣይ ተንቀሳቃሽ ሬሳ ካረገችይ ተይች ሴት እምገላገልበትን መንገድ ጠቁሞይ ፣ ተተቀዳሁበት የተቀዳይውን እማገኝበትን መላ ጀባ ይበለይ ።ያለበለዚያ አልፋታውም
ለሁሉም የማይሰራ ለሁሉም ቲተረት ደስ አይልማ ደስ አይልም!!! ቲለይ ሳቅ በላይ በላዩ እያፈነይ•••
"መፍትሄ ታልሰጠህስ ምን ትሆን ?" አልሁት።
"እሱማ ምን እሆናለሁ ወንድም አለም ነገሩን አጫወትሁህ እንጂ ከነፍጥርጥሯ እኮ ታንጀቴ አፈቅራታለሁ !"
"ካፈቀርካትማ ቻለው እንግዲህ እኔም ትለማፈቅራት እይ እንዳባቷ ጠባይ እማ ቢሆኔ እስታሁን ጥያት በጠፋሁ ነበር!" ብለው••
"ሀሳባችን ፍላጎታችን አልገጥም ቲል የጠላሁትን ትትወድ ፣ የወደድሁትን ትትጠላ ታንድ ወንዝ ተቀድተን ተሆነ በመሀላችን ፍቅር ታይጠፋ ለምን መንገድና ፍላጎታ ተኔ ታቃረነ ብዬ እይ ማፍቀርስ አፈቅራታለሁ።
ብታስከፋይኝም እሷስ በምን ምህንያት ይሆን እንዲህ ተኔ በተቃራኒው ለመሆን የበቃይው ብዬ አስባለሁ እይ አልነካትም።
ባይሆን አንዳንዴ ነገር ቲበዛ እና ትታስከፋይ ወጣ እልና ታፋፉ ላይ ቆሜ ብሶቴን በፉከራም በቀረርቶም ለዱሩም ለጫካውም እነግረዋለሁይ " አለይ።
"ምን እያልህ ነው እምትነግረው ጃል? ብለው እዛው ዠመረዋ •••
ኧ••••ረ ጎራው
ኧ•••••ረ ወንዱ
አረጎራው አረወንዱ
አረጎራው አረወንዱ•••
ተ••••ተሰውት በላይ እግምባር ሲወርዱ
ተ•••••ቆሰሉት በላይ ጠላት ሲያሳድዱ
እ•••••ልፍ ጀግና ወንዶይ በሴቶይ ነደዱ
ኧረ ጎራው
ኧረ ጎራው
ኧረ ወንዱ
ዳሩልይ ብላቸው የግራ ጎኔን
ዳሩልይ ብላቸው ውሃ አጣጪዬን
እ•••••ሳቷን አምጥተው ጠበሱዪ እኔን
እረ ጎራው
ኧረ ወንዱ
ኧረ ጎራው
ስንቱን ዥግና ነዪ ባይ እንዳላሯራጥነው
ስንቱን ወንድ ነዪ ባይ ገርፈን እንዳልጣልነው
ለ••••ፍቅር እጅ ሰጥተን ስንቱን አሳለፍነው
እረ ጎራው
ኧረ ወንዱ
ኧረ ጎራው
ዘራፍ አካኪ ዘራፍ
ዘራፍ አካኪ ዘራፍ
ጀግና ቲመስለን ጡንቻ ያስነካ
ጀግና ቲመስለን •••
ስንት እንደጣለ ሬሳ ያስለካ
የራሷን ሳሰጥ የሰው ታትነካ
በፍቅር ገዳይ ሴት አለይ ለካ
ዘራፍ አካኪ ዘራፍ
ዘራፍ አካኪ ዘራፍ
የዥግናው ልዥ ነይ የበላያ ዘር
ጓንዴ ቢተኮስ የማልበገር
መድፍ ቢንጣጣ የማልደነብር
ጠልፋ ጣለችይ በሀያል ፍቅር
ላገሬ ባልዘምት ባልወጣ ከዱር
ለሚስቴ ዘብ ነይ የቤት ወታደር
ዘራፍ አካኪ ዘራፍ
ዘራፍ አካኪ ዘራፍ
እጠጅ ቤቱ ውስጥ ያለው በሙሉ በመሀል በመሀል በወኔ እያጨበጨበ ቲያጅበው ቆየ ። ጨርሶ አጠገቤ ተቀመጠ።
እሄውልህ ወዳጄ አንተ ከፋም ለማም በፍቅርህም በጠብህም መሀል የሚገባብህ ሰው የለም እኔኮ የተጀገርሁት የራሳቸውን ሚሽት ፈተው የገዛ ሚስቴን ዘብ ሆኜ ታልጠበኳት በሚሉት አባቷ ነው።
"ያንተው ነገር ለሰሚውም ግራ ነው ኩለው ድረው ተሰጡ ቡሀላ ያንተ እንዢ የሳቸው እንዳልሆነይ አያውቁ ኖራል እንደው እሄን የሚነግራቸውስ ወዳጅ የላቸውም ? ሴት ልዥ እናት እና አባቷን ትተዋለይ ተባሏ ጋም ትተባበራለይ !"ቲባል አልሰሙም" አልይ።
ምን መስሚያ አላቸው እንደው ምን እንደማረግ ግራ ግብት ብሎያል ባክህ!" ብለው•••
" እኔን ቻለው እንዳልኸይ ቻለው ተማለት ውጪ ክፉ አልመክርህ እንግዲ መሄዴ ነው ውዳጄ ቻለው ብሎዪ ተጠጅ ቤቱ ወጣ።
ደሞ መለስ አለና ወደ ዥሮዬ ጠጋ ብሎ ችግር በጉልበት አልያም ጥፋተኛውን በመውቀስ ብቻ አይፈታም ብልሀት ያስፈልጋልይ እኔ ከሰሞኑ ተሞላ ጎደል በኔና በሷ መሀል ያለውን ሽግር እየፈታሁ ነው።
በምን እንደሆነ ታውቃለህ ለምን እንዲህ ትሆኛለሽ ለምን እሄን አደረግሽ ብዬ እምቧ ከረዩ በማለት እንዳይመስልህ ለሚሽቴ የምጠላውን እንደምወድ የምወደውን እንደምጠላ እያረግሁ ገለባብጬ በመንገር ነው ተያ ቡሀላ ተኔ በተቃራኒው የሄደይ መስሏት መስመራችንን ገጥማው ቁጭ አለይ!!
ኪኪኪኪኪኪኪ አሁንም ልድገምልህ በመሀላችሁ ያለውን ችግር ለመፍታት ብልሀተኛ መሆን አልያ መቻል ብቻ ነው ያለህ አማራጭ ቻለው ኪኪኪኪኪኪኪ"
መክሮይ ታይሆን ተሳልቆብይ የወጣ መስሎይ በገንሁ!።
ተጠጅ ቤት ወጥቼ ወደ ቤቴ የሚያደርሰይን መንገድ እንደዥመርሁት ነበር እንደእብድ ብቻዬን ማውራት የዠመርሁት።
ያው ለግዜውም ቢሆን ስካሩ እስቲበርድ እብድ እና ሰካራም አንድ ትለሆኑ ነው መሰል እንደእብድም እንደሰካራምን እያርገይ •••
"በየቤቱ ስንት ጉድ አለ እናንተው በኑሮ ጉያ ውስጥ እንቅፋት ቲመታይ ተሰው ዘር ሁሉ እኔን ብቻ መርጦ የሚመታይ እየመሰለይ ሳማርረው የቆየሁትን አምላኬን ይቅር በላይ አልሁት ።
ሁሉም በሂወቱ ውስጥ በፍቅር መሀል ፣ በስራ መሀል ፣ በጤና መሀል፣ በሰላም መሀል እያደናቀፈ የሚፈታተነው የየራሱ የሆነ እንቅፋት አለው ።
አንዳንዱ በእንቅፋቱ ተመቶ ይወድቅና ተሩጫው ይገታል ፣ አንዳንዱ በእንቅፋቱ ተንገዳግዶ ቆም ይልና መንገዱን ይቀጥላል፣ አንዳንዱ ተራሱ ተእንቅፋቱ ጋር ተላምዶ ሽግሩ ምን እንደሆን እንኳን በወጉ ታይለየው በፈጣሪው አልያም በሌላው ሰው ላይ ቲማረር ይኖራል።
አንዳንዱ እራሱን እንቅፋቱን ፈንቅሎ ይጥለውና ሌሎይንም እንዳይመታ መንገዱን ያቀናል ።
አሁን በኔ ሂወት እንቅፋት የሆኑብዪን የሚሽቴን አባት እንዴት ተኑሮዬ መሀል ፈንቅዬ እንደማወጣቸው ብቻ ነው ማሰብ ያለብይ።
እይ በሳቸው ምህንያት ተዋቡ ፍቅሬን እና ሴት ልዤን ጥዬ ዌትም አልሄድም ፣ ትዳሬን አልበትንም እያልሁ በሀሳብ እንደናወዝሁ ግቢ ደረስሁ።
በበነገው ታልጋዬ ላይ ታልነሳ ጥዋት ቁርስ ይዛልይ እንደመጣይ ወገቧን ይዛ ቁልቁል እያየችይ•••
"ለምን ሄድክ ትናንት ?" ትትለይ •••
"ተይይ እስቲ ተዋቡ በቃ ብስጭትጭት ቲያረገዪ ሄድሁ!
እየሆነ ያለው ነገር ቢያበሳጨይ በኔ ይፈረዳል?"
እንደውም ተሳቸው ጋር ክፉና ደጉን ተምነጋገር ወሩ እስቲሞላላቸው ድረስ ልብሴን ሸክፌ ዘመድ ጥየቃ ልሄድ ወስኛለሁ!" አልኋት።
"እኔን ጥለህ አንዱ ? አታደርገውማ ይልቅ
ቆይ አንድ መላ መጥቶልኛል እነግርሀለሁ መጣሁ አለይችዪና ቁርሱን አስቀምጣልይ ወጣይ።
ትንሽ ቆይታ መጣይና
•••••••ይቀጥላል
ክፍል - ስምንት ... ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like❤️ ማድረግ አይርሱ።
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
@fkrn_be_kalat
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
ክፍል - ሰባት [፯]
✍ (በጥላሁን ተስፋዬ)
.
.
.
ዘወር ብዬ ወደአመላከተችይ አቅጣጫ ትመለከት እመንገዱ ዳር ላይ ታለ አንድ ስጋ ቤት ነጭ እተቀባ ግርግዳ ላይ የተሳለ ትልቅ ጥቁር በሬ ነው !
እንደው አንዳርጌ ሙት ነው እምልህ ብልጭጭ አለብይ!"•••••
ቲለኝ አልቻልሁም ወሬውን እስኪያከትም አፍኜ የያዝሁትን ሳቅ እንደ ሀምሌ መብረቅ አንባረቅሁት ።
ካካካካካካ ያንተስ ለጉድ ነው ጃል
እና ምን ይሻልሀል ? ብለው•••
ታድያ እሄ ባልና ሚሽት ታንድ ወንዝ ይቀዳሉ ያለ ሰው ጥሁፍን እንዲህ ብሎ ያስተካክልልይ
ባልና ሚሽት ታንድ ወንዝ ይቀዳሉ ተዳምጠው እና ተሳቷ ሚሽቱ በስተቀር ብሎ ያስተካክልልይ።
ይህን ማድረግ የማይችል ተሆነ ግን ተሚስቴ ያፋታ እና ታለወንዟ የሄደይውን የኔዋን ያምጣልይ።
ይህም ታልሆነለት ያለክዳና ታልገጠምክ እያለይ ቲላት እስፓናቶ ቲላት አንጎል ፋቶ እያረገይ
አወላልቃ ታጨርሰይ የኔ ታትሆን የሷ ላረችይ ሚሽቴ የራሷን ግጣም አፈላልጎ ይስጣት።ይህም ተተሳነው ደግሞ•••
በእሳት ምላሷ ተጨጓራዬ ዥምራ በሷ ንዴት ስጠጣ ወደ ጉበቴ ፣ በሷ ብሶት ታጨስ ወደሳምባዬ እየመጣይ ተንቀሳቃሽ ሬሳ ካረገችይ ተይች ሴት እምገላገልበትን መንገድ ጠቁሞይ ፣ ተተቀዳሁበት የተቀዳይውን እማገኝበትን መላ ጀባ ይበለይ ።ያለበለዚያ አልፋታውም
ለሁሉም የማይሰራ ለሁሉም ቲተረት ደስ አይልማ ደስ አይልም!!! ቲለይ ሳቅ በላይ በላዩ እያፈነይ•••
"መፍትሄ ታልሰጠህስ ምን ትሆን ?" አልሁት።
"እሱማ ምን እሆናለሁ ወንድም አለም ነገሩን አጫወትሁህ እንጂ ከነፍጥርጥሯ እኮ ታንጀቴ አፈቅራታለሁ !"
"ካፈቀርካትማ ቻለው እንግዲህ እኔም ትለማፈቅራት እይ እንዳባቷ ጠባይ እማ ቢሆኔ እስታሁን ጥያት በጠፋሁ ነበር!" ብለው••
"ሀሳባችን ፍላጎታችን አልገጥም ቲል የጠላሁትን ትትወድ ፣ የወደድሁትን ትትጠላ ታንድ ወንዝ ተቀድተን ተሆነ በመሀላችን ፍቅር ታይጠፋ ለምን መንገድና ፍላጎታ ተኔ ታቃረነ ብዬ እይ ማፍቀርስ አፈቅራታለሁ።
ብታስከፋይኝም እሷስ በምን ምህንያት ይሆን እንዲህ ተኔ በተቃራኒው ለመሆን የበቃይው ብዬ አስባለሁ እይ አልነካትም።
ባይሆን አንዳንዴ ነገር ቲበዛ እና ትታስከፋይ ወጣ እልና ታፋፉ ላይ ቆሜ ብሶቴን በፉከራም በቀረርቶም ለዱሩም ለጫካውም እነግረዋለሁይ " አለይ።
"ምን እያልህ ነው እምትነግረው ጃል? ብለው እዛው ዠመረዋ •••
ኧ••••ረ ጎራው
ኧ•••••ረ ወንዱ
አረጎራው አረወንዱ
አረጎራው አረወንዱ•••
ተ••••ተሰውት በላይ እግምባር ሲወርዱ
ተ•••••ቆሰሉት በላይ ጠላት ሲያሳድዱ
እ•••••ልፍ ጀግና ወንዶይ በሴቶይ ነደዱ
ኧረ ጎራው
ኧረ ጎራው
ኧረ ወንዱ
ዳሩልይ ብላቸው የግራ ጎኔን
ዳሩልይ ብላቸው ውሃ አጣጪዬን
እ•••••ሳቷን አምጥተው ጠበሱዪ እኔን
እረ ጎራው
ኧረ ወንዱ
ኧረ ጎራው
ስንቱን ዥግና ነዪ ባይ እንዳላሯራጥነው
ስንቱን ወንድ ነዪ ባይ ገርፈን እንዳልጣልነው
ለ••••ፍቅር እጅ ሰጥተን ስንቱን አሳለፍነው
እረ ጎራው
ኧረ ወንዱ
ኧረ ጎራው
ዘራፍ አካኪ ዘራፍ
ዘራፍ አካኪ ዘራፍ
ጀግና ቲመስለን ጡንቻ ያስነካ
ጀግና ቲመስለን •••
ስንት እንደጣለ ሬሳ ያስለካ
የራሷን ሳሰጥ የሰው ታትነካ
በፍቅር ገዳይ ሴት አለይ ለካ
ዘራፍ አካኪ ዘራፍ
ዘራፍ አካኪ ዘራፍ
የዥግናው ልዥ ነይ የበላያ ዘር
ጓንዴ ቢተኮስ የማልበገር
መድፍ ቢንጣጣ የማልደነብር
ጠልፋ ጣለችይ በሀያል ፍቅር
ላገሬ ባልዘምት ባልወጣ ከዱር
ለሚስቴ ዘብ ነይ የቤት ወታደር
ዘራፍ አካኪ ዘራፍ
ዘራፍ አካኪ ዘራፍ
እጠጅ ቤቱ ውስጥ ያለው በሙሉ በመሀል በመሀል በወኔ እያጨበጨበ ቲያጅበው ቆየ ። ጨርሶ አጠገቤ ተቀመጠ።
እሄውልህ ወዳጄ አንተ ከፋም ለማም በፍቅርህም በጠብህም መሀል የሚገባብህ ሰው የለም እኔኮ የተጀገርሁት የራሳቸውን ሚሽት ፈተው የገዛ ሚስቴን ዘብ ሆኜ ታልጠበኳት በሚሉት አባቷ ነው።
"ያንተው ነገር ለሰሚውም ግራ ነው ኩለው ድረው ተሰጡ ቡሀላ ያንተ እንዢ የሳቸው እንዳልሆነይ አያውቁ ኖራል እንደው እሄን የሚነግራቸውስ ወዳጅ የላቸውም ? ሴት ልዥ እናት እና አባቷን ትተዋለይ ተባሏ ጋም ትተባበራለይ !"ቲባል አልሰሙም" አልይ።
ምን መስሚያ አላቸው እንደው ምን እንደማረግ ግራ ግብት ብሎያል ባክህ!" ብለው•••
" እኔን ቻለው እንዳልኸይ ቻለው ተማለት ውጪ ክፉ አልመክርህ እንግዲ መሄዴ ነው ውዳጄ ቻለው ብሎዪ ተጠጅ ቤቱ ወጣ።
ደሞ መለስ አለና ወደ ዥሮዬ ጠጋ ብሎ ችግር በጉልበት አልያም ጥፋተኛውን በመውቀስ ብቻ አይፈታም ብልሀት ያስፈልጋልይ እኔ ከሰሞኑ ተሞላ ጎደል በኔና በሷ መሀል ያለውን ሽግር እየፈታሁ ነው።
በምን እንደሆነ ታውቃለህ ለምን እንዲህ ትሆኛለሽ ለምን እሄን አደረግሽ ብዬ እምቧ ከረዩ በማለት እንዳይመስልህ ለሚሽቴ የምጠላውን እንደምወድ የምወደውን እንደምጠላ እያረግሁ ገለባብጬ በመንገር ነው ተያ ቡሀላ ተኔ በተቃራኒው የሄደይ መስሏት መስመራችንን ገጥማው ቁጭ አለይ!!
ኪኪኪኪኪኪኪ አሁንም ልድገምልህ በመሀላችሁ ያለውን ችግር ለመፍታት ብልሀተኛ መሆን አልያ መቻል ብቻ ነው ያለህ አማራጭ ቻለው ኪኪኪኪኪኪኪ"
መክሮይ ታይሆን ተሳልቆብይ የወጣ መስሎይ በገንሁ!።
ተጠጅ ቤት ወጥቼ ወደ ቤቴ የሚያደርሰይን መንገድ እንደዥመርሁት ነበር እንደእብድ ብቻዬን ማውራት የዠመርሁት።
ያው ለግዜውም ቢሆን ስካሩ እስቲበርድ እብድ እና ሰካራም አንድ ትለሆኑ ነው መሰል እንደእብድም እንደሰካራምን እያርገይ •••
"በየቤቱ ስንት ጉድ አለ እናንተው በኑሮ ጉያ ውስጥ እንቅፋት ቲመታይ ተሰው ዘር ሁሉ እኔን ብቻ መርጦ የሚመታይ እየመሰለይ ሳማርረው የቆየሁትን አምላኬን ይቅር በላይ አልሁት ።
ሁሉም በሂወቱ ውስጥ በፍቅር መሀል ፣ በስራ መሀል ፣ በጤና መሀል፣ በሰላም መሀል እያደናቀፈ የሚፈታተነው የየራሱ የሆነ እንቅፋት አለው ።
አንዳንዱ በእንቅፋቱ ተመቶ ይወድቅና ተሩጫው ይገታል ፣ አንዳንዱ በእንቅፋቱ ተንገዳግዶ ቆም ይልና መንገዱን ይቀጥላል፣ አንዳንዱ ተራሱ ተእንቅፋቱ ጋር ተላምዶ ሽግሩ ምን እንደሆን እንኳን በወጉ ታይለየው በፈጣሪው አልያም በሌላው ሰው ላይ ቲማረር ይኖራል።
አንዳንዱ እራሱን እንቅፋቱን ፈንቅሎ ይጥለውና ሌሎይንም እንዳይመታ መንገዱን ያቀናል ።
አሁን በኔ ሂወት እንቅፋት የሆኑብዪን የሚሽቴን አባት እንዴት ተኑሮዬ መሀል ፈንቅዬ እንደማወጣቸው ብቻ ነው ማሰብ ያለብይ።
እይ በሳቸው ምህንያት ተዋቡ ፍቅሬን እና ሴት ልዤን ጥዬ ዌትም አልሄድም ፣ ትዳሬን አልበትንም እያልሁ በሀሳብ እንደናወዝሁ ግቢ ደረስሁ።
በበነገው ታልጋዬ ላይ ታልነሳ ጥዋት ቁርስ ይዛልይ እንደመጣይ ወገቧን ይዛ ቁልቁል እያየችይ•••
"ለምን ሄድክ ትናንት ?" ትትለይ •••
"ተይይ እስቲ ተዋቡ በቃ ብስጭትጭት ቲያረገዪ ሄድሁ!
እየሆነ ያለው ነገር ቢያበሳጨይ በኔ ይፈረዳል?"
እንደውም ተሳቸው ጋር ክፉና ደጉን ተምነጋገር ወሩ እስቲሞላላቸው ድረስ ልብሴን ሸክፌ ዘመድ ጥየቃ ልሄድ ወስኛለሁ!" አልኋት።
"እኔን ጥለህ አንዱ ? አታደርገውማ ይልቅ
ቆይ አንድ መላ መጥቶልኛል እነግርሀለሁ መጣሁ አለይችዪና ቁርሱን አስቀምጣልይ ወጣይ።
ትንሽ ቆይታ መጣይና
•••••••ይቀጥላል
ክፍል - ስምንት ... ቶሎ እንዲቀጥል አንብበው ሲጨርሱ Like❤️ ማድረግ አይርሱ።
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈
@fkrn_be_kalat
┈┈┈┈••●◉❖◉●••┈┈┈