ወርቃማ ንግግሮች


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


ሰው የለበስክ ሰው እንጂ ልብስ የለበስክ ሰው አትሁን.. ሰውነት የአለም ምርጡ ጌጥህ እሱ ነውና።
አስተያየት እንቀበላለን.. @Golden_SpeechBot
🍂

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


ካነበብኩት dan repost
🍃 ዱ ኒ ያ 🍂


👑          ⭐️             ⚡️
ٰ    • ○ ° 🌹🌹🌹• ○ °• ○ °• ○ °
 • ○    🌹🌹🌹🌹    • ○ °  👈አበባውን
• ○ °🌹🌹🌹🌹🌹           በመንካት• ○ °
  • 🌹🌹🌹🌹🌹🌹    ብቻ ምርጥ
○ 🌹🌹🌹🌹🌹🌹    የሱና 𝙘𝙝𝙖𝙣𝙣𝙚𝙡  ° :.
   🌹🌹🌹🌹🌹🌹         ያገኛሉ📡
 • 🌹🌹🌹🌹🌹      ° :.   * • ○       
• ○  🌿🌹🌹🌿      
  • ○ °   🌿🌿            👈
     •        🌿   • ○ °        🌿🌿
 • ○ °        🌿     • ○ ° 🌿🌿🌿
   • ○ °         🌿       🌿🌿🌿🌿
    • ○ °          🌿  🌿🌿🌿🌿🌿
        • ○ °       🌿   🌿🌿🌿🌿
      • ○ °         🌿  🌿🌿🌿
          • ○ °     🌿  🌿° :. * • ○
         °• ○ °      🌿° :.   * • ○
                    🌿° . °☆  . * ● ¸
.    ★  🌿° :.   * • ○ °
        ° .     🌿. * ● ¸
                  🌿       በቀላሉ ይቀላቀላሉ ።
☆  . * ● ¸ .
★ ° . *   ° . °☆  . * ● ¸
.    ★  ° :.   * • ○

🅰️🅰️🅰️⭐️✅🔗🔡🔡🔡
ለተጨማሪ ሀሳብ አስተያየት  ጥቆማ
@twhidfirst1 ⭐️🔗🔡🔡🔡




➡️ኢህሳን jobs Advertising

⚙ይህ ቻናል በሀገር ውስጥ ያሉ ስራ አጥ
            ወንድም እህቶች
በአላህ ፍቃድ  የስራ ማግኛ ሰበብይሆን ዘንድ
ታስቦ የተከፈተና የስራ ማስታወቂያ የምንለቅበት
አዲስ ⚪️⚪️⚪️⚪️⚪️⚪️⚪️ ነው  ✅

በቻናሉ ያለምንም ክፍያ የስራ ማስታወቂያ
የሚለቀቅበት ቻናል ሲሆን

እናንተም ወደቻናሉ በመቀላቀል የቻናሉ
አባል ሁኑ እናንተም ይህንንም ቻናል
ሼር በማድረግ የቻናሉን እድገት አስቀጥሉ

አላማችን ወንድምና እህቶቻችን ስራ አጥ
እንዳይሆኑ ሰበብ ማድረስ ነው
🔗ተቀላቀሉ ✅

https://t.me/ihsan_jobs
https://t.me/ihsan_jobs


በሰው ተፈጥራዊ ቅርፅ ላይ አንድ ነገር ቢጨመርበት እንኳን አያምርም። እንዲሁ አንድ ነገር ቢቀነስ ያስጠላል።

የዓለም ሰዓሊዎችና ዲዛይነሮች ተሰባስበው በሰው ቅርፅ ላይ አንድ የሚያስውብ ነገር እንፍጠር ቢሉ አይችሉም። ወይም ይህ አያስፈልግም ብለው ቢቀንሱ ያስጠላልም፥ እንዲሁም ይበላሻልም።

ሌላው ቀርቶ ከሰው ተፈጥሮ ጋር የማይመሳሰል አዲስ ነገር እንኳን መሳል አይችሉም። ምሳሌ ስላልታወቁ ፍጥረታት (Aliens) የተሰሩ የአሜሪካ ፊልሞችን ካያችሁ ሁሉም ኤሊዬንሶች ከሰው ጋር የሚመሳሰሉና የሆነ ተፈጥሮ የጎደላቸው አስቀያሚ ፍጥረታት ናቸው። የዚህ ምክንያቱ በፊልሞቹ ላይ በርካታ “ጠበብት” ዲዛይነሮች ቢሰባሰቡም ከሰው የተለዬ አዲስ ፍጥረት መቅረፅ ስላልቻሉ ነው።

ይህ የሰው ልጅ በሌላ ሰው ወይም ፍጥረት ሊፈጠር ቀርቶ ሊሳል እንኳን እንደማይችል የሚያሳይም ነው።

አላህ የሰው ልጅ ተፈጥሯዊ ቅርፅ እንከን የሌለው የተሟላና የተዋበ እንደሆነ ሲነግረን እንዲህ አለ፦

❝ቀረፃችሁም! ቅርፃችሁንም አሳመረ።❞
(አት-ተጋቡን 3)


~

ለአመታት ግንባታው ተቋርጦ የነበረው የደሴው አንጋፋው የአረብገንዳ መስጂድ የሚናራ ግንባታ ስራ ተጀምሯል። የመስጂድ አስተዳደሩና የከተማው መጅሊስ ባደረገው ትግል የማስፋፊያ ቦታ በቅርቡ መሰጠቱ የሚታወስ ነው። በርቱ…


~ ዛሬ በመዲናችን አዲስ አበባ


የጎሮው መስጅድ ኢማም መታሰራቸውን ሰምተናል። ምክንያቱም ደግሞ ለምን ዳእው ለምን አደረጋችሁ በማለት ጥዋት ላይ መታሰራቸውን ከቦታው የነበሩ አማኞች ተናግረዋል።

ዳእዋውን ያደረገውም ወንድም ወንድም ሬድዋን እኔ ነኝ ያደረኩት እሰሩኝ እኔንም በማለት እሱም አብሮ መታሰሩ ተሰምቶል። የታሰሩት ውጡ ቢባሉም ያ ሰረን አካል ለምን አሰረን በማለት ህዝቡም በቁጣ አንድ ላይ ይምጣና ያናግረን የከሰሰንም ካለ ይምጣ በማለት በፖሊስ ጣቢያ እንደታሰሩ ተሰምቶል


የነፃነቱ ጉድጓድ ባለ ድል!

ሴፕቴምበር 6/2021 ማለዳ ላይ እስራኤላዊያኑን ያስደነገጠ አንድ ክስተት ተከስቶ ነበር።ወራሪው "የብረት ቁልፍ" ብሎ ከሚጠራው እጅግ ጥብቅ ቁጥጥር ከሚደረግበት የጊልቦአ እስር ቤት ስድስት ታሳሪዎች ማምለጣቸው ተሰማ።በየት በኩል አመለጡ ተብሎ ሲፈለግ ወደ እስር ቤቱ የሚወስድ ረጅም ጉድጓድን ያገኛሉ።ታዲያ ታሳሪዎቹ ረጅም ቀናትን ከፈጀ ቁፋሮ በኃላ ከእስርቤቱ ማምለጥ ችለዋል።ይህ በወቅቱ የእስራኤል የደህንነት መረብን መበጠስ የቻለ ታላቅ ጀብዱ ሆኖ ተወርቶ ነበር።ታዲያ ይህን ታላቅ ሚሽን የመራውን የሹሀዳኡል-ቁድስ ብርጌድ አመራር የነበረው ዘከሪያ አዝ-ዙቤይዲና ሌሎችም ታሳሪዎች ከቀናት አሰሳ በኃላ በጠቋሚዎች ተባባሪነት ዳግም ይያዛሉ።
ዘከሪያ አዝ-ዙበይዲ ዳግም ሊፈረድበት በዳኛው ፊት ቆሞ የተናገረው ይህ ነበር:-
"አንዲት ክፍተት ካገኘሁ እጄን አጣጥፌ የምቀመጥበት ምክኒያት የለም።አሁንም ከእስር ወጥቼ ነፃነቴን ለማረጋገጥ እሞክራለሁ።"

ታዲያ ይህ ጀግና ከ3 ዓመታት የእስር ቆይታ በኃላ በፍልስጤማዊያኑ የትግል ቡድኖች ተፅዕኖ አንገቱን ቀና አድርጎ በበሩ በኩል ለመውጣት ችሏል።


የ #ዲላ ዩኒቨርስቲ ሙስሊም ተማሪዎች ኒቃብ ለብሰው እንዳይገቡ በመከልከላቸው #በመስጂድ ውስጥ ለመቆየት መገደዳቸውን ተናገሩ!!!

#አርባ_አራት የሚሆኑ የዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ሴት ተማሪዎች ኒቃብ ለብሰው ወደ ግቢው እንዳይገቡ እንደተከለከሉና አንዳንዶቹም ከአምስት ቀናት በላይ በመስጂዱ ውስጥ ለመቆየት መገደዳቸውን ለአዲስ ስታንዳርድ ገለጹ።

ከአዲስ ስታንዳርድ ጋር ቆይታ ያደረጉ ተማሪዎች፤ ቀደም ባሉት ዓመታት ኒቃብ መልበስ ይፈቀድ የነበረ ቢሆንም ዩኒቨርሲቲው በቅርቡ “የደህንነት ስጋትን” በመጥቀስ ያለቅድመ ማስጠንቀቂያ ኒቃብ መልበስን እንደከለከለ ተናግረዋል።

በዲላ ዩኒቨርስቲ የሙስሊም ተማሪዎች ማህበር ሊቀመንበር የሆነው ኑረዲን አብደላ በበኩሉ ጉዳዩን ከዩኒቨርስቲው የስራ ሃላፊዎች ጋር በጽሑፍም ሆነ በአካል ለመፍታት የተደረጉ ተደጋጋሚ ጥረቶች መፍትሄ አለማምጣታቸውን ለአዲስ ስታንዳርድ ተናግሯል።

አክሎም “በርካታ ሙስሊም ተማሪዎች ላለፉት አምስት ቀናት በመስጂድ ውስጥ ቆይተዋል። በዚህ ጊዜ ለፈተና መቅረብም ሆነ የሚጠበቅባቸውን አሳይመንት ለማጠናቀቅ አልቻሉም” ብሏል።


أشهد أنْ لا إله إلا الله وحده لا شريك له، وأشهد أن محمدًا عبده ورسوله


የዲላ ዩኒቨርሲቲ የኒቃብ ክልከላን በተመለከተ

    የደቡብ ኢትዮጵያ  እስልምና ጉዳዮች ከፍተኛ ምክር ቤት ለኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ም/ቤት በፃፈው ደብዳቤ የዲላ ዩኒቨርሲቲ የኒቃብ ክልከላ ማድረጉንና ሴት ተማሪዎች ከትምህርት እና ከፈተና ፕሮግራም መስተጓጎላቸዉን በተመለከተ መፍትሄ እንዲሰጥበት ጠይቋል፡፡

የዩኒቨርሲቲዉ አመራሮች ከዲላ ዩኒቨርሲቲ ሙስሊም ተማሪዎች ተወካዮች ጋር ባደረጉት ዉይይት ከደህንነት ስጋትና ሀይማኖትን ከማንጸባረቅ ጋር ተያይዞ ኒቃብ መከልከላቸዉን በቃል የገለጹላቸዉ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት ኒቃብ የሚለብሱ ሴት ሙስሊም ተማሪዎች ከትምህርት እና ከፈተና ፕሮግራም ተስተጓጉለዉ እንደሚገኙ ጠቅሷል።

ጉዳዩን በተመለከተ የኢትዮጲያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ከሚመለከታቸዉ የመንግስት ተቋማት ጋር በመነጋገር መፍትሄ እንዲያበጅለት ስንል በአላህ ስም እንጠይቃለን በማለት ደብዳቤውን አጠናቋል።




የዘንድሮ የሀጅ እና ዑምራ የጉዞ ዋጋ 625 ሺህ ብር ሆኗል

📌 ምዝገባው ጥር 15 ይጀምራል።

የ1446ኛው የሀጅ እና ዑምራ ጉዞ ምዝገባ ከጥር 15 ቀን 2017 ጀምሮ እስከ የካቲት 21 ብቻ እንደሚከናወን የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ገልጿል።

ምዝገባው ጥር 15/2017 በሁሉም የክልል እና የከተማ አስተዳደር የምዝገባ ጣቢያዎች ይጀመራል።

የሳውዲ ሀጅ ሚኒስቴር ባስቀመጠው አሰራር መሰረት ያለው የምዝገባ ጊዜ አጭር በመሆኑ ሁጃጆች (ተጓዦች) በወቅቱ ቅድመ ዝግጅታቸውን እንዲያጠናቅቁ ጥሪ ቀርቧል።

የዘንድሮ የሀጅ እና ዑምራ የጉዞ ዋጋ 625 ሺህ ብር መሆኑ ተገልጿል።

ምክር ቤቱ " የጉዞው ዋጋ የማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ጋር ተያይዞ የታየው የዶላር ጭማሪና በአየር መንገዶች ላይ ያለው የትኬት ዋጋ መናር ዋጋው ከፍ እንዲል አድርጎታል " ብሏል። 

" የሀጅ ዋሃ ከዶላር አንፃር የ4,921 ዶላር ቅናሽ እንዲደረግበት ቢደረግም በብር ግን ጭማሪ አሳይቷል " ሲል ገልጿል።

ጠቅላይ ምክር-ቤቱ የአገልግሎት ዋጋን በመቀነስ በዕቅድ የተያዙ ፕሮጀክቶችን በማጠፍና በሳውዲ የሚቀርበውን አገልግሎት ተመጣጣኝ እንዲሆን በማድረግ 108 ሺህ ብር ቅናሽ እንዲኖረው ማድረጉን አሳውቋል።

የዶላር ዋጋ ከፍ በማለቱ ግን ብሩ መጨመሩ ተገልጿል።

ባለፈው ዓመት ለአንድ ሀጅ ዋጋ አጠቃላይ ብር 329,000 እንደነበር ይታወሳል።


ዋጋው የሚቀመስ አልሆን ጎበዝ😡


መቀሌ


በዚህ ሰአት የሰሜን ኮከብ የምትባላዊ ከተማ መቀሌ በአክሱም እየተደረገ ባለው ግፍ አፈና ጭቆን አገፍግፎናል።

በሂጃባችን አንደራደርም ብለው ተሰባስበው ጎዳና ላይ ወጥተዋል።


~~

ዲላ ዩኒቨርስቲ «ኒቃብ ለደህንነት ስጋት ነው!» ብሎ ሙስሊም እህቶቻችንን እንዳይማሩ ከልክሏል።
እውነት ለመናገር፤ ኒቃብን እንደ ስጋት ከሚመለከቱ ጽንፈኞች በላይ የሃገር ስጋት የለም።


~

ከአንድ ወጣት ጋር በፍቅር ትወድቃለች። በአንድ ጎጆ ውስጥ ለመኖር ወስነው ከቤተሰብ ጠፍታ ከጎንደር ከእሱ ጋር ወደ አዲስ አበባ ይመጣሉ። እስከዚህች ሰዓት ድረስ ሙስሊም መሆኑን አታውቅም ነበር። ቤተሰቦቹ እንደሚያካብዱና እንደማይቀበሏት ለዛም አክስቱ ጋር እንድታርፍ ሲነግራት ነበር ሙስሊም መሆኑን ያወቀችው!
ኋላ ላይ በየእምነታቸው ሊኖሩ ተስማምተው ጎጆ ተቀለሰ። ከሁለት አመታት በኋላ ግን በአንዲት እህት ( ጎረቤቷ) ሰበብ ከእስልምና ጋር ተዋወቀች! ለእስልምና ተረታችም! በተረታችበት ማግስት ግን ሕይወት መልኳ ሌላ ሆነ!

ክህደት! ህመም! ማጣት ! መገፋት........... የሕይወት መንገዷ ሆነ😥

ለእስልምና የተከፈለ መስዋትነት !......
በፅናት የመቆም ተምሳሌትነት... ብቻ ... ጌታዬ ስንት አይነት ባርያ እንዳለሁ ያየሁባት መንገደኛዬ ነች!


የትግራይ ክልል እስልምና ጉዳይ ጠቅላይ ምክር ቤት በአክሱም ት/ቤቶች የሒጃብ ክልከላ በመቃወም ነገ በሚደረገው ሰልፍ ሁሉም እንዲገኝ ጥሪ አቅርቧል።

ሸኽ አደም አደም ዓብዱልቃድር ዛሬ በሰጡት መግለጫ መጅልሱ ሒጃብ ከተከለከለበት ከጥቅምት ጀምሮ ጉዳዩ በውይይት እንዲፋታ ለወራት ያላሰለሰ ጥረት ሲያደርግ ቆይቷል። ከታች የመጅልሱ መዋቅር ከወረዳው ጀምሮ ጉዳዩ በቀጥታ ወደ ሚመለከታቸው መ/ቤቶችና የስራ ኃላፊዎች በአካል በመቅረብና ለቁጥር የሚታክቱ ደብዳቤዎች በመፃፍ ሁሉም ብዙ ጥረት ማድረጋቸው አስተውቀዋል። ነገር ግን ድካሙ ውጤት ማምጣት አልቻለም። ስለዚህም ለነገ ሰላማዊ ሰልፍ ጠርተናል። በሰልፉም ስለፍትህ የሚያሳስበው የእህቶቹና ልጆቹ መበደል የሚያስጨንቀው ሁሉም በሰልፉ ተገኝቶ ድምጹን እንዲያሰማ ጥሪ አቅርበዋል።

ሒጃቧ ትለብሳለች
ትምህርቷም ትማራለች‼️


╰ ዱንያ ላይ ያልጎደለው ማንም የለም፣
━━━━━━━━━━━━━━━
⎓ሰው ሆኖ ሀሳብ ያልተጫነው አልተፈጠረም፣
⎓ሕይወት ትንሽ ይሁን ትልቅ ከሁሉም ፍጡር የሆነ ነገር ቀንሳለች፣
⎓ሰው ሆኖ የሞላለት አንድም ሰው የለም።

⊖መጥፎ ሰው ማለት ሀሳብ በገባው ሰው ላይ ሌላ ሀሳብ የሚጨምር ነው።
ጭንቀት በወረሰው ላይ ተጨማሪ ጭንቀት የሚለቅ ነው።
⊖ለሰው ችግር መፍትሄ መሆን ባትችሉ እንኳ ችግሩን ከአንድ ወደ ሁለት አታሳድጉ።╯




ባልና ሚስት ይጣሉና ሽማግሌ ይሰበሰባል። ከዚያም ሁለቱም ችግራችሁን ተናገሩ ሲባሉ ...
ባል፦ "እኔ ከስራ ደክሞኝ ስመለስ ማረፍ እፈልጋለሁ። ነገር ግን ልጆችን እያንጫጫች አያሳርፉኝም" አለ
ሽማግሌዎቹም "ሌላስ?" ይሉታል
"እኔ ከስራ ስመለስ ልጅ ያዝ ትለኝና ወጥ ትሰራለች። የልጅ ወተት ታፈላለች። ምናለ ሳልመጣ ጨርሳ ብጠብቀኝ ተቀምጣ እየዋለች" ይላል በንዴት።

ሚስትም በሰዎቹ ፊት "ከዚህ በኃላ በፍፁም አንረብሸውም" ብላ ይቅርታ ስለጠየቀች ሽማግሌዎቹ ትተዋቸው ይሄዳሉ።

በነጋታውም ሚስት ልጆቿን ይዛ እናቷ ቤት ሄደች። ከስራ ሲመጣ ቤቱ ተቆልፏል። ልክ ከፍቶ ሲገባ ቤቱ እጅግ ይቀዘቅዛል። ከሰል ለማቀጣጠል ቢሞክር እምቢ አለው። ልብሱን ደራርቦ ሚስት ሰርታ የነበረውን
ጠራርጎ በላ። ዝምታው ሲጨንቀው ቴሌቪዥን ከፍቶ ለማየት ሞከረ ግን የለመደው የልጆቹ ድምፅ ናፈቀው እና እየከፋው ተኛ።

ጠዋት ሲነሳ ያ የሚጣፍጠው ቁርስና የሚወደው የሚስቱ ፈገግታ የለም። ከፋው። ፊቱን ታጥቦ ወደ ስራው ሄደ። ቁርሱንም ውጪ በላ ግን አላረካውም። ቀኑ እንደከበደው ዋለ። ስልኩን ቢያይም አትደውልለትም። ውሎ ሲመለስ ራቱን ውጭ በልቶ ከጓደኞቹ ጋር ቢያመሽም በመጨረሻ ያ ባዶ ቤት ጠበቀው። ለቅሶ ቤት ይመስል መግባት አስጠላው። ዞር ብሎ ሲያስብ ለካ ያለ ሚስቱ ጎዶሎ ነው።
ለካ ልጆቹ ረባሾቹ ሳይሆኑ አጫዋቾቹና የመንፈስ እርካታው ናቸው።

ከዚያ በኃላ "በእጅ የያዙት ወርቅ ሆናችሁብኝ ጥቅማችሁን ስላልተረዳሁ በጣም በድያችኃለሁ። እባክሽ ይቅር በይኝ ውዷ ሚስቴ!" ብሎ በሽማግሌ ታረቃትና በሰላም ኖሩ።
***
መልዕክቱ፦ ሚስቶች ሸክሞች ሳይሆኑ የቤቱ ተሸካሚዎች፣ ሰራተኞች እና አስተዳዳሪዎች ናቸው። ልጆች የቤቱ ሁከት ፈጣሪዎች ሳይሆኑ ደስታና ሙቀት ፈጣሪዎች ናቸው።
ስለዚህ ደስታ የሚሰጠንን ነገር ከማጣታችን በፊት ቀድመን ለይተን አውቀነው ተገቢውን ቦታ እንስጠው ለማለት ነው።

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.