ሀበሻ 🇪🇹


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


🇪🇹 ኢትዮጽያዊነታችንን የምናሳይበት 🤝 አንድነታችንን የምናጠነክርበት 🥰 ፍቅርን የምንማርበት ቻናል ነው ።
☞☞ @Ferhanhabesha

Связанные каналы  |  Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


''ሰው ሲታመም የምንጠይቀው ከቋጠሮ ሰሐን ጋር ነው"
አለማየሁ ገላጋይ

ሰው ሲታሰር ' እግዚአብሔር ያውጣህ ' የምንለው ከፍትፍት አገልግል ጋር ነው ....አራስ የምትጠይቀው ከፔርሙዝ አጥሚት ጋር ነው ... የክርስትና አባታችን ለፋሲካ አክፋዩን የሚጠብቀው ድፎ ዳቦ ና አረቄ ነው ...እዝንተኛ የምናስተዛዝነው ሰባት እንጀራ ከአንድ ሰሐን ወጥ ጋር ነው ...ሟች የምንሸኘው ከገንቦ ጠላና ከለምለም እንጀራ ጋር ነው ...የቅዱሳንና የመልአክታት ተራዳኢነት የሚጎበኘን በስማቸው ከዘከርን ነው።

...ሰዕለታችን በሬ ወይም በግ ነው ...ሰርጋችን ፣ ልደታችን፣ እርቃችን፣ ሹመታችን፣ አምልኳችን፣ የሚበላ ነገርን ሙጥኝ ያሉ ናቸው ... ...ሌላው ቀርቶ አንድ ሰው ተምሮ ሲመረቅ ይዘን የምንሄደለት ስጦታ ብዕር ወይንም መጽሐፍ አይደለም ፤ ኬክ ፣ ብርቱካን ፣ ሙዝ ...ነው ።

በሽተኛ ስትጠይቅ ከብርቱካንና ከሙዝ ይልቅ መጽሐፍ መውሰድ እንደማላገጥ ይቆጠራል ። ጊዜውን ይገፋበት ዘንድ መጽሐፍ ማበርከት በሽተኛው እንዳይድን ከመመኘት እኩል ነው ። ለኛ ለኢትዮጵያውያን መጻሕፍት ከባዶ ገበታችን በስተዚያ የተቀመጡ ትርፍ ነገሮች ናቸው ። መጻሕፍት የሚያስፈልጉት ገበታችን ሞልቶ ከገነፈለ በኃላ ነው ብለን በይነናል። ገበታችንም አይሞላ ፤ መጻሕፍቱም አይነሱም ። ያልተረዳነው ቢኖር ለገበታ መትረፍረፍ ዙሪያ ጥምጥም ጉዞ መጻሕፍት አቋራጭ መንገድ መሆናቸውን ነው ።እንዴት ታዲያ ማንበብ መብላትን ይቅደም ? መቼ ይሆን ከምንኮራባቸው ባህሎቻችን በላይ ማንበብ ባህላችን ሆኖ የምንታወቅበት ናየምንኮራበት?......'''''

አለማየሁ ገላጋይ


#ትግራይ

" ' ያንቺ እቃ ብቻዬን ጠላ እየሸጥኩ ያሳደኳቸውን 2 ወንድ ልጆቼን ይመልስልኛል ወይ ? ' ነው ያለችኝ ! " - ፕሬዚዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ

ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ በታሪካዊቷ ዓድዋ ከተማ በነበረው የዓድዋ ድል በዓል  ላይ እምባ እየተናነቃቸው 😭 ንግግር አድርገው ነበር።

እሳቸው በእንባ ንግግር ሲያደርጉ የበዓሉ ታዳሚ ህዝብ ከፍተኛ የሀዘን ስሜቱ ከፊቱ ይነበብ እንደነበር በስፍራው የነበረው የቲክቫህ ቤተሰብ አባል ገልጿል።

ፕሬዝዳንት ሳህለወርቅ ዘውዴ ምን አሉ ?

" ዛሬ ወደ ትግራይ ስመለስ በህሊናዬ የሚመጡብኝ ብዙ ትዝታዎች አሉብኝ።

ይቅርታ አድርጉልኝና አጋጣሚውን ተጠቅሜ ማንሳት እፈልጋለሁ።

በትምህርት ቤት ውስጥ ተጠልለው ከነበሩ ወገኖች መካከል አንዷ ፈንጠር ብላ የተቀመጠች አንዲት ሴት ለማነጋገር ሞክሬ ነበር።

በተፈናቃዮች ካምፕ ጉብኝት ልብን የሚሰብር  ነው። ከቤት ንብረታቸው ወጥተው ፣ ክብራቸውን አጥተው ቁጭ ብለው ጉብኝት .. እኛ ደግሞ እንመጣለን ልናያቸው።

ታዲያ ያችን ሴት ጠጋ ብዬ ሳነጋግራት፤ በጥሩ አልመለሰችልኝም። ጥቂት ያመጣሁትን እቃ እንድታከፋፍልልኝ ነበር ልጠይቃት የነበረው ' ያንቺን እቃ አልፈልግም ' አለችኝ።

በሆስፒታል እና በመጠለያ ጣቢያቸው ሄጄ ያየዋቸዋን ሴቶች በእጅጉ አስባቸዋለሁ። እቺን ሴትዮ ለምንድነው የምትመልሽልኝ ስላት ' ያንቺ እቃ ብቻዬን ጠላ እየሸጥኩ ያሳደኳቸውን ሁለት ወንድ ልጆቼን ይመልስልኛል ወይ ? ' ነው ያለችኝ መልስ የለኝም ፤ አይመልስም ብቻ ነው ያልኳት።

ጦርነቱ ተዛምቶ በአፋር ክልል ሰመራ ሆስፒታል ህክምና ላይ የነበሩ የተማረኩ የህወሓት ታጋይ ሴቶችን አግኝቻቸዋለሁ ሳናግራቸው ያሉኝ ከልቤ አይጠፋም ፤ ቦታቸው እዛ አልነበራም ትምህርት ቤት ነው።

ያሉኝ ' እኛ መመለስ የምንፈልገው ወደ ትምህርት ቤት ነው ' ይሄንን ወግቼ ያንን አሸንፌ የሚል ዓላማ አልነበራቸውም። በክፍላቸው ግርግዳ ላይ የፃፉት የለጠፉት የአፋር ህዝብ እንዴት ደግ እንደሆነ ነው። ኢትዮጵያዊ ለኢትዮጵያዊ እንዴት እንደሚረዳዳ ነው።

ሌሎችም አሉ ብዙ እርጉዝ ሆነው ሶስት ልጅ ወልደው ሲንከራተቱ የነበሩ ... ለማንኛውም ብዙ መንከራተት ነበር።

ዛሬ እዚህ ቆሜ የትግራይ እናቶች ያሳለፉትን #ሰቆቃ በእውነቱ እረዳለሁ ለማለት ነው ይሄን ሁሉ የምናገረው። እግዚአብሔር ብርታቱን ይስጥዎ !!

ዞሮ ዞሮ የማንኛውም ግጭት መጨረሻው ጠረጴዛ ዙሪያ ተቀምጦ የሰላም ስምምነት መፈረሙ አይቀርምና ይህ ሳይሆን ተጨራርሰን ተጨካክነን ፣ ዘርና ሃይማኖት መለያያ አድርገን ሃይማኖቶችን ከፋፍለን ሳይሆን በቅድሚያ መከላከል እንዳለብን መገንዘብ አለብን።

የዓድዋ ባለቤቶች እንዳልሆንን ገፅታችንን አጉድፈን አበላሽተናል። "

#TikvahFamilyAdawa

@tikvahethiopia


አድዋ የአለምን አካሄድ የለወጠ ታላቅ ክስተት ነው።

የአድዋ ድል ባይኖር አለም መልኳ ተለውጦ ሌላ ይሆን ነበር።
የሐርቫርድ ዩኒቨርስቲው Raymond jonas "The battle of Adwa" በሚል መፅሐፉ እስከ አሁን ከተለመደው የተለየ ሃሳብ ስለ አድዋ ድል አስፍሯል።

እንደ ፀሐፊው ሃሳብ ፥ ኢትዮጵያ በአድዋ ጦርነት በጣሊያን ወራሪ ብትሸነፍ ኖሮ አለም መልኳ ይለወጥ ነበር። አፍሪካ እንደ አውስትራሊያ ፥ ኒውዝላንድ እና ሰሜን አሜሪካ የነጮች መኖሪያ ወደ መሆን ትሸጋገር ነበር። አፍሪካዊ ሙሉ ለሙሉ በነጮች መዳፍ ውስጥ ገብቶ በጦርነት ፥ በበሽታ እና በባ*ርነት ቁጥሩ ተመናምኖ በገዛ ምድሩ አና*ሳ እንዳይሆን መሰረት የጣለው የአድዋ ድል ነው።

የአውሮፓ የጋለ መስፋፋት ህልም ላይ ውሃን የቸለሰ ድል ነው ፥ አድዋ። ጥቁሮች የነጭን የባርነት ቀንበር እንዲፋለሙ የልብ ልብ ሰጥቷል፥ ነጮች ደግሞ ቆም ብለው እንዲያስቡ የማስጠንቀቂያ ደውልን ደውሏል።

የ "The Battle of Adwa" ፀሐፊ 'በአድዋ የተነሳ አፍሪካ የነጮች መኖሪያ ከመሆን ከመተርፏ በተጨማሪ አውሮፓውያን ወደ ኢሲያ እንደልብ እንዲይስፋፉ እግድን ፈጥሮባቸዋል' ይላል።

የዚህ ትርጉሙ ምንድነው? አድዋ ያለ ጥርጥር የአለምን መልክ እንደወሰነ አስረጅ አይደለም?

ተስፋኣብ ተሾመ


የንባብ ባህላችን እየተዳከመ ነው ሲባል ይገርመኛል፤ ሲጀመር የንባብ ባህል ኑሮን ያውቃል ወይ? እዛና እዚህ በግለሰቦች ላይ የተንጠለጠለ የግል ፍላጎት ባህል ይባላል? እንዳውም "አንባቢ የመምሰል" እና "በንባብ የመጎራት" ባህላችን አስቀያሚ ባህል ፈጥሯል! "ምሁር ቅብ" የመሆን ባህል!? የፈረደበትን ጎግል ዞር ብታደርግበት ሌጣውን የሚቀር "ምሁር" ነው በየሚዲያው አገር ይያዝ የሚለው!


"ሴቶች በምንም አይማልሉም አትድከሙ!"
(አሌክስ አብርሃም)

በነገራችን ላይ እንደምታስቡት ሴት"መጀንጀን" ላይ አሪፍ አይደለሁም! ስለመጨረሻ ጅንጀናየ ላውጋችሁ! የሆነ ጊዜ አምስት መንገዶች አስር ማሳለጫዎች ምናምን የሚል የሬዲዮ ፕሮግራም ላይ ሴት ልጅ በራሱ የሚተማመን ወንዳወንድ ወንድ ትወዳለች የሚል ነገር ሰማሁ! እና አንዲት በዛ ሰሞን የወደድኳትን ልጅ ማማለል ፈለኩ! ተቀጣጥረን ተገናኘን ምሳ አብረን በላን (በድሮሮሮሮሮሮሮ ጊዜ የዛሬ ስድስት ዓመት ሰዎች ምሳ ይገባበዙ ነበር) እና ከመሬት ተነስቸ ጀብዱ ነገር ማውራት ጀመርኩ!

"ይገርምሻል የሆነ ጊዜ አንድ ዳይኖሰር የሚያክል በሬ ከቄራ አመለጠ ፤ እና ከቄራ ቡልጋሪያ ድረስ ሰባት ወንዶች ሶስት ሴቶች ሁለት መኪና በቀንዱ እየወጋ አተረማመሰው! ፖሊስ ሁሉ ማስቆም አልቻለም! እና እኔ ስደርስ ወደሆኑ አሮጊት ቀንዱን አሹሎ እየሮጠ ነበር ... በባልቴቷና በበሬው መካከል ሶስት የበሬ እርምጃ ሲቀር ተፈትልኬ ሮጥኩና መሀላቸው ገብቸ ስቆም ጫማየ እንደመኪና ጎማ ፉጭጭጭጭጭጭ አለ! በሬው ደንግጦ ቆመና ተፋጠን እንደቆምን በቀስታ ቀረብኩት .... በእግሩ አስፋልቱን እየቆፈረ ሊወጋኝ ሲሞክር ሸወድኩትና አንገቱ ላይ የታሰረውን ገመድ ቀጨም አድርጌ ለባለቤቱ አስረከብኩ! ይገርምሻል በተፈጥሮየ አልፈራም!

ልጅቱ ስትሰማኝ ቆየችና የበሬውን ነገር እንዳልሰማ ሰው " ዳይኖሰር ስትል አስታወስከኝ! ለምን ዛሬ ኤድናሞል ሙቪ አናይም? አሪፍ የዳይኖሰር ሙቪ አላቸው" ብላ በሚያማምሩ አይኖቿ አየችኝ! ጀብዱየን ውሃ ቸለሰችበት! ቅር እንዳለኝ ወደኤድናሞል የሚወስደን ታክሲ ስንጠብቅ አስገራሚ ነገር ተፈጠረ .... በሬ! የፈረጠጠ በሬ መንገዱን እያመሰው ከፊት ለፊታችን መጣ ... በእርግጥ ነፍሴን ለማትረፍ ባደረኩት ሩጫ ከበሬው የበለጠ ብዙ ሰው እየገፋሁ ሳልጥል አልቀረሁም! ልጅቱ ጋር በተፈጠረው ግር ግር እንደተጠፋፋን ከዛ በኋላ አልተገናኘንም! በእርግጥ ትዝ ያለችኝም የሆነ ካፌ ገብቸ ሁለት ሊትሩን ውሃ ከጠጣሁ በኋላ ነው!


ቀጥ ብለህ ቁም!
(አሌክስ አብርሃም)

ጎተራ ኮንዶሚኒየም ስኖር ወጣት ባልና ሚስት ጎረቤቶች ነበሩኝ! በጣም የሚፋቀሩ ! እና ሌሊት ሌሊት አንዳንድ ተቀባይነት የሌላቸው ድምፆች ያለዕቅድ ግድግዳውን አልፈው ይረብሹኝ ነበር! ሌላ ሌላው ነገር ሳይሆን በተለይ ሚስቱ የባሏን ስም በቁልምጫ ስትጠራው "ምናለ ይሄን ለቁልምጫ የማይመች ስም ቢያስቀይረው" እያልኩ በሌሊቱ አስባለሁ! ወይም የብዕር ስም እንደሚባለው የእንትን ...ስም ቢጠቀሙ! ከነገሩ ይልቅ የስሙ ቁልምጫ ነበር በሀፍረት ጆሮየን የሚያግለው! (ለአንባቢወቸ የስነ ልቦናና የስነ ተዋልዶ ስሜት ስል ስሙን እዘለዋለሁ)

አንድ ቀን ድንገት ቤቱን ለቀው ሄዱ! ለአንድ ሳምንት ከደበረኝ በኋላ😀 ሌሎች ባልና ሚስቶች ተከራዮች ገቡ! በተለይ ሚስትየዋ የፆሎት ሰው ነች! ባሏ ስራ ሲሄድ ቤቷን ዘግታ ይሄን አጋንንት ስትለበልበው ነው የምትውለው...ከጎተራ ልቀቅ ...ከሳሪስ ልቀቅ ...ከቦሌ ልቀቅ...ከቡልቡላ ....ስገስፅ ነው የምትውለው! ለወሬ ነጋሪ አንድ አጋንንት አዲሳባ አታስቀርም! ድምጿ ራሱ ጎርናና እና አስፈሪ ከመሆኑ ብዛት እኔ ራሱ ልለቅ ይቃጣኝ ነበር! ፀባችን ከስጋና ደም አይደለም ስትል ሻንጣየን አስቀምጨ ተረጋጋሁ!

እና አንድ ሌሊት ያ ድምፅ አነቃኝ ! መጀመሪያ ሹክሹክታ ነበር በኋላ ግን ድምጿ ጨመረ " በአንተ ላይ በተሰጠኝ ስልጣን አዝሃለሁ... ቀጥ ብለህ ቁም ! የተፈጠርክበትን አላማ ትፈፅም ዘንድ ቀጥ ብለህ ቁም ! ስራህን እስክታከናውን ፀንተህ ቁም! የሚያልፈሰፍስህ መንፈስ አሁን ተመታ! ..."

"አሜን" ይላል ባሏ በሚያሳዝን ድምፅ! ምንድነው ይሄ ቁም የሚባል ነገር ? ብየ እኔም በቀስታ ፀለይኩ "ጌታ ሆይ ምንም ድምፅ የማያሳልፍ ግድግዳ ባለው ቤት ባርከኝ! ልጅህን ክፉ የሚያሳስበውን መንፈስ ከጎተራ ...ወሎ ሰፈር ...ከቦሌ... ከቡልቡላ ...ንቀለው! ከሶስት ወር በኋላ ፆሎቴ ሰመረ እኔን ከጎተራ ነቀለኝ!


ወግ ብቻ dan repost
[እኔ አለሁ እንዳለሁ
እንዴት ነሽ እመ?]

ከጦርነት ቀጠና ወጥቼ አዲስ አበባ እንደገባሁ የመጀመሪያው ስራየ ስራቦታ ጎራ ማለትና ቤት መፈለግ ነበር። እውነት ለመናገር ከሆነ አዲስ በብዙ ግልምጫዎችና በሰቃዥ የኑሮ ውድነት የታጀበች እጅግ ባይተዋር ከተማ ሆና ነው የጠበቀችኝ።

አዲስ አበባ ቁመት ሙሉ እንባ ስጋ ሙሉ ኧረወይለሊቴ ሆናለች ወገን።

“ጃክሮስ ቆንጆ ቤት አግኝቼልሀለሁ” ደላላው ነበር

ሄድኩ

ቤቷ ሁለት በሶስት ናት። ጭራሽ መሀከሉ ላይ እንደሰፊው ህዝብ መድረሻ ያጣ የሚመስል ኮለን ተገትሯል።

“ኧኸ እንዴት ነው ወደድሻት? 3500 ናት”

ምን ነካህ ደላላ!? ይሄኮ እንኳን አልጋ ሊያዘረጋ ጠረንጴዛና ወንበር ሊይዝ ፍራሽ እንኳን ካላጠፍኩት አያስነጥፈኝም።

😳

የውሻውን ቤት ነው እንዴ ልታከራዮኝ ያሰባችሁት🤔

“ውሻውማ የተሻለ አግኝቶ ስለወጣ ነው እምናከራይህ” አከራዩዋ

እንባየ ደርሶ ግጥም አለ🥴

ደግሞ ሌላ ቤት መስቀል ፍላወር

“ድርድር የለውም። 6 ክፈል” ሸምገል ያሉ ናቸው አከራዮ

ቆንጀት ያለ ቤት ነው እሺ እከፍላለሁ

“ታመሻለህ?”

አዎ አንዳንዴ ሚቲንግ ሲኖረኝ እስከ 4 ምናምን ላመሽ እችላለሁ

“አይሆንም አይሆንም እስከ 2 ልፍቀድልህ”

እንዴ ልጅዎ አደረጉኝ እንዴ!

“ምን አልክ? ይሄንም እኔ ሆኜ ነው”

እንዴ ትራንስፖርቱ ራሱ ያስመሻል እኮ። ቁልፍ ካለ ይስጡኝ ላስቀርጸው።

“ቁልፍ? ለምንድን ነው ቁልፍ እምሰጥህ? አምሽተህ እየገባህ ልታዘርፈኝ!”

እ😳

“ተወው ለሌላ አከራየዋለሁ። በዚያ በኩል ውጣ”

እንባየ ደርሶ ግጥም አለ🥴

ከሰአቱን ድክም ሲለኝ ልረፍ ምሳም ልብላ ብየ የሆነ ሆቴል ገባሁ

ቅቅል ተፈርሾ አምጪልኝ።

By the way ቅቅል ኢዝ ማይ ተወዳጅ ምግብ

በድንች፣ በካሮት እና በሆኑ ቅጠላቅጠሎች የታጀቡ 3 ግድንግድየ ቅልጥሞች መረቅ ደፍቀው መጡ

ተጠራጠራጠርኩ

ሂሳብ ስንት ነው እናት?

“550”

እ😳

እንስቷ እንባዋ ደርሶ ግጥም አለ🥴

ከጎጃም በእግርና በባጃጅ ያስወጣኸኝ አንድየ አንተ ታውቃለህ ብየ በላሁት

ሂሳብ ከፍየ ስወጣ ከጀርባየ የሆነ ድምፅ ሰምቼ ዞር ስል አስተጋጇ እጇን እያውለበለበች

“ዌል ካም ቱ አዲስ የዝቅተኛው ማህበረሰብ አባል” ስትለኝ ደረስኩ

እስኪ ሆዴ ቻለው ቻለው ቻለው እያልኩ ወደስራ ቦታየ ወክ አደርግ ጀመር

አለም ሲኒማን እልፍ ስትሉ ባስ መጠበቂያው አለአይደል፣ አንድ በግምት 60 ዎቹ አካባቢ የሆነ ሰውየ እግሩን አጥፎ ወንበሩ ላይ ተቀምጦ አይኑን ጨፍኖ
“ኦም…ኦ….ም…. ኦ….ም” ይላል

ሆዴ ቦጭ ቦጭ አለ
ዝርዝር የአምስት ብር ሳንቲሞች መፀወትኩት

ሰውየው ግን አንድ አይኑን ገልጦ
“ወንድም ዮጋ እየሰራሁ እንጂ እየለመንኩ አይደለም። አዲስ አበባ መቆየት ከቻልክ ይጠቅምሀል ገንዘብህን ያዝ” አለኝ

አደነጋገጤ😳

ህዝቤ እንዳለ ለቆ ነው🤔

ቢሮ ልደርስ አካባቢ የሆነ ሙዚቃ ሰመቼ ዞር ስል የሬሳ ሳጥን የሚሸጥበት ሱቅ ላይ ሁለት ወጣቶች እየቃሙ በትንሽየ ስፒከር

“ጉርምርሜ ና ጉርምርሜ ያሆ መሌ ያሆ መሌ ና ጉርምርምርሜ” የሚል ሙዚቃ ያዳምጣሉ

ጆሮየ ፕራንክ ነው በለኝ😳

እውነት ለመናገር የሬሳ ሳጥን መሸጫ ውስጥ ሙዚቃ ስሰማ ይህ የመጀመሪያየ ነው

“የኔ ልጅ ተውው አሽሙር ነው። መንገድህን ቀጥል” አሉኝ በአጠገቤ ሲያልፉ የነበሩ እናት

ወይ አዲስ አበባ እንዲህ ሁሉን ነገር ድብልቅልቅ አደርጋ ትጠብቀኝ። ታክሲዎች ትንሽ መንገድ አምቦራችተውህ 10 ብር አምጣ ይሉሀል። ከመሸብህ ይሄ ብር ሁለት እጥፍ ሁሉ ሊሆን ይችላል። ራይድ ልያዝ ካልክ happy textile road bruh በሶስት ቀን ሆድህ ፈርደሀል ማለት ነው!

ደግሞ ሰው ምንድን ነው እንዲህ የተፈራራው🤔ለንደን ያለህ ይመስል ማንም ሰላም ሊልህ አይፈልግም። ሰላምታ ብታቀርብም አበጀህ የሚልህ የለም።

ወንድም ሰአት ስንት ነ..?

“እግዜር ይስጥልኝ እኔ ራሱ የታክሲ ብቻ ነው የቀረኝ። እህል ከቀመስኩ ዛሬ ሁለት ወሬን ደፈንኩ”

እ😳

“ተወኝ በቃ እኔ የትኛውንም ፖለቲካ ፓርቲ አልደግፍም። የሁሉም ባንክ አካውንት አለኝ”

ዋ ኧረ ምንጉድ ነው ብየ ወደ ጎዳናየ ተመለስኩ

ወገን እንግዲህ አዲስ ጥይት አልተተኮሰባትም እንጂ ጦርነት ላይ ናት የሚባለው ነገር እውነት ነው መሰል…

ቢጨንቀኝ
እመ ጋ ደወልኩና
“እመ ለካንስ ይሆን መስሎኝ እንዲያው ሳላውቀው ከሞት ሸሽቼ ወደ ሞት ነው የመጣሁት” አልኳት

እመ ግን ሳግ በሚተናነቀው ድምፅ
ምን አለችኝ?

“ልጅ ታምሩ ምን የሚያጓጓ ህይወት ኖሮህ ነው ሞት የሚያስፈራህ!”

እንባየ ደርሶ ግጥም አለ🥴

@wegoch
@wegoch
@paappii

By Tamiru Temesgen


Jafer Books 📚 dan repost
የአድዋው ጀግና ራስ መኰንን የታፈነው ዜና መዋዕል በአማርኛ ተተርጉሞ ለንባብ በቃ!

በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ ጉልህ ስፍራ ከሚይዙት ታላላቅ የጦር ሰዎች ውስጥ ቀዳሚው ራስ መኰንን ናቸው፡፡ እኒህ ታላቅ የጦር መሪ የቀዳማዊ ኃይለሥላሴ አባት፤ የምኒልክ ዙፋን ታማኝ፤ የሣህለ ሥላሴ የሥጋም የመንፈስም ውርስ ያላቸው ታላቅ የጦር ሰው ናቸው ፡፡
 
ይህ ዜና መዋዕል መነሻውን ከዘመነ አክሱም በማድረግ የንግሥና ሐረጎችን እያጣቀሰ፣ ዋናውን የታሪክ መቼቱን ዐፄ ምኒልክ አንኮበር ላይ ከተወለዱበት ከ1836 ዓ.ም. ያደርጋል፡፡ ከዚህ ዘመን ጀምሮ ፍሰቱ እስከ 1910 ዓ.ም. ዋዜማ ይቀጥላል፡፡

በእነዚህ ዘመናት በኢትዮጵያ ቤተ መንግሥት የተከናወኑ ታላላቅ ተግባራት በዚህ ዜና መዋዕል ተመዝግበዋል፡፡ የመጽሐፉ ርእስና ዋና ተተራኪ ራስ መኰንን ይሁኑ እንጅ በሐረር የተሾሙ ደጃዝማቾች የአስተዳደር ሁኔታ፣ ሐረርና ጅጅጋ ሲያዙ የተካሄዱ ጦርነቶች፣ በምሥራቅ ኢትዮጵያ የተተከሉ ቀዳምያን አድባራት ዝርዝርና የአተካከል ታሪክ፣ በማዕከላዊ መንግሥት የነበሩ የሥልጣን ሽኩቻዎች፣ የአድዋ ጦርነትና ሌሎችም አካባቢያውያን ዘመቻዎች ተካተዋል፡፡

ስለሆነም ይህ ዜና መዋዕል በዘመኑ ስለነበረችው ታሪካዊቷ ኢትዮጵያ አስተዳደር አንደኛ ሁነኛ ምንጭ ሆኖ ሊጠቀስ የሚችል ድንቅ ትርጉም ነው፡፡

ዜና መዋዕሉን አንብቦ ምስክርነቱን የሰጠው ደብተራና የሕግ ባለሙያው በአማን ነጸረ የዜና መዋዕሉ ጸሐፊ ግራጌታ ኃይለጊዮርጊስ የአጻጻፍ ክህሎታቸውን እንዲህ ሲል አወድሶታል፡- ‹‹… ጸሐፊው ፍሬ ነገር አያዛቡም፡፡ ታሪክ አያንዛዙም፡፡ የድርጊት ጊዜን፣ ቦታንና ሁኔታን አይስቱም፡፡ ከቀደምት ጸሐፍት በተለየ ዓመተ ምሕረትን በጥንቃቄ ይመዘግባሉ፡፡ ከውጋዴን እስከ አድዋ ዐቢይ ድርጊት የተፈጸመባቸው የቦታ ስሞችን ፊደል ሳያዛንፉ ጠንቅቀው ይጽፋሉ…››


Jafer Books 📚 dan repost
"ዛሬ ቅዳሜ አይደለም" በተሰኘው መጽሐፍ ዙሪያ የተሰጠ ዳሰሳ።

በዮሴፍ ተመስገን (የቋንቋ እና ሥነ ፅሁፍ መምህር)

ክፍል አንድ

በአዳም ረታ የምናውቀው የህጽናዊነት አጻጻፍ በ “ዛሬ ቅዳሜ አይደለም” መጽሐፍ ውስጥ ረብቦበታል የሚል ሀሳብ ውስጤ ተፈጥሮ ነበር፡፡ (ለመጀመሪያ ጊዜ ሳነበው፡፡)

ነገር ግን ከደራሲው ማረጋገጫ ካላገኘሁ በስተቀር ይህንን ሀሳብ እንድቀይር የሚገፋፋ ስሜት ከውስጤ ተፈጥሯል፡፡ (ለሁለተኛ ጊዜ ሳነበው፡፡) መጽሐፉን ሁለት ጊዜ አንብቤው የተፈጠረብኝ ስሜት ሁለት አይነት ነውና የማስቀምጠው አልሆነም፡፡ እሰልሠው ግድ ነው፡፡
የመጽሐፉ ደራሲ ናትናኤል ቀረዓለም “ዛሬ ቅዳሜ አይደለም” የመጀመሪያ የታተመ መጽሐፉ እንጂ የመጀመሪያ መጽሐፉ ላለመሆኑ እርግጠኛ ነኝ፡፡ ቁጭ ብለን እናጠናቸው ዘንድ ሊያስገድዱን የሚቃጣቸው ቴክኒኮችን በመጽሐፉ ውስጥ አካቷል፡፡ (ዶክተር እንዳለጌታ ከበደ ለዚህም ይመስለኛል መጽሐፉን “ቋንቋው ፣ ቴክኒኩ እና የሀሳቡ ፍሰት አጃኢብ ነው፡፡) ሲል የገለጸው፡፡

መጽሐፍ አንብቤ የመጽሐፍ ዘውግ ፣ ቴክኒክ እና የአጻጻፍ ስልት መለየት እስኪሳነኝ ድረስ ስደነቅ ይህ የመጀመሪያዬ ነው ብል ብዙም ያጋነንኩ አይመስለኝም፡፡ “ምን አይነት መጽሐፍ ነው?” ብዬ ከማንበቤ በፊት ለጠየቅኩት ጥያቄ ያገኘሁት መልስ “በአጫጭር ታሪኮች እንዲሁም በዘፈቀደ ሀሳቦች የተዋቀረ” የሚል መልስ ነበር ያገኘሁት፡፡ ያገኘሁት መልስ እውነት ያልነበረ ስለመሆኑ እመሰክራለሁ፡፡ 

የመጽሐፉ የመጀመሪያ ገጽ ላይ…
“…እውነት የሚባል ነገር የለም! ሊል ፈልጎ…”
“…እውነት የሚባል ነገር የለም! ማለቱ እውነት አይሆንምና ተወው…” (ገጽ 1) የሚል ሀሳብ ስታገኙ አንዴ አንብበን ወደ ቀጣዩ ገጽ እንሻገር ዘንድ መጽሐፉ እንዴት ይፈቅድልናል?

ሮማን ተወልደ መጽሐፉን ስትገልጸው “አጫጭርም ወጥም ፣ ወጥም አጫጭርም ፣ ፍልስፍናዊ ልብ ወለድ” ብላዋለች፡፡ እውነት አላት፡፡ ያለማቋረጥ የሚዥጎደጎዱ ጥያቄዎቹ እና የተሰመረበት ምላሽ ሳይሰጥ አንባቢውን አስተክዞ ፣ ማለቂያ ወደሌለው የሀሳብ ዓለም አሻግሮ መጽሐፉ ወደ ቀጣዩ ገጽ ይሻገራል፡፡

“…ልጄ ማታ በጊዜ ነው የምትመጣው?” እናቱ ጠየቁት፡፡
“እርግጠኛ አይደለሁም እማዬ!” መለሰ፡፡
እየወጣ ማብሰልሰል ጀመረ፡፡
“እርግጠኛ አይደለሁም!” ስል ምን ማለቴ ነው?
በምንም አይነት ነገር ላይ በእርግጠኝነት እርግጠኛ መሆን ይቻል ይሆን?
በጊዜ ስለመምጣቴ እርግጠኛ አይደለሁም፡፡ ጭራሽ ስለመመለሴስ እርግጠኛ መሆን እችላለሁ?
አይመስለኝም፡፡
ሰው እኮ እርግጠኛ ስለመሆኑ ራሱ በእርግጠኝነት መናገር አይችልም፡፡
እኔም… ሰው እርግጠኛ ስለመሆኑ በእርግጠኝነት መናገር አይችልም ብዬ በእርግጠኝነት መናገር አልችልም፡፡”
ማብሰልሰሉን ቀጠለ፡፡… (ገጽ 44)

ማብሰልሰሉን የሚቀጥለው ገጸ ባህሪው ብቻ ሳይሆን ተደራሲው መሆኑንም ማስተዋል ልብ ይሏል፡፡

ይህ በየመሀሉ ከእናቱ እና እህቱ ጋር የሚጨዋወት ገጸ ባህሪይ ካፌው ውስጥ የሚመሰጠው እንዲሁም ከመምህራኑ ጋር የሚከራከረው መምህር ይሆንን ብዬ እጠረጥራለሁ፡፡ (ገጸ ባህርያቱ ስም አልተሰጣቸውምና እርግጠኛ ለመሆን ቢከብደኝም እርግጠኛ የሆንኩ ይመስለኛል፡፡ ያው መጽሐፉ “ሰው ስለ አንድ ነገር በእርግጠኝነት እርግጠኛ መሆን አይችልም…” ብሎ እንዳይሞግተኝ እየሰጋሁ፡፡ 
መጽሐፉ በዚህ ገጸ ባህርይ ላይ ያጠነጥናል የሚል ድምዳሜ መስጠት ግን ስህተት መፍጠርም ይሆናል፡፡ በአጫጭር እና ራሳቸውን የቻሉ በሚመስሉን (ራሳቸውን የቻሉ ሊሆኑም ከሌሎች ጋር ሊደጋገፉ ቢችሉም) ታሪኮች ውስጥ አላገኘነውም ይሆን የሚል ጥያቄን ማስከተሉ አልቀረም፡፡

…በብቸኝነት አላደገም፡፡
በብቸኝነት አድጓልም፡፡
ከሰው አልተለየምና በብቸኝነት አላደገም፡፡
ሰው መሀል ሆኖ ተነጥሏልና ብቸኝነት አጥቅቶታል፡፡
ፀሐይ በብቸኝነት የምታንጸባርቀውን ጨረር ተመልክቶ ብቸኝነቱ ኃይል ስለመሆኑ አያስብም፡፡
ውብ ቅላጼ ያለው ሕብረ ዝማሬ አድምጦ ብቸኝነቱ ድክመት ስለመሆኑ አያስብም፡፡
እሱ እሱ ነው፡፡
ብቸኛ የሆነ፡፡
ብቸኛም ያልሆነ፡፡  (ገጽ 10)

የገጸ ባህርያቱ ስም አልባ መሆን ገጸ ባህርያቱን እንዳንወዳቸው ወይም እንዳንጠላቸው አላገደንምና (እሷ ፣ እሱ እንዲሁም እነሱ) ያጎደሉብን የለም፡፡ እንዲያው አንዳንዴ ጥቂት እንድንመራመር እና የመጽሐፉን ገጽ እንድንገለብጥ ማመንታት ውስጥ ቢከቱንም፡፡

ይቀጥላል


ኢትዮጵያ ቡክ ፎረም - Ethiopia Book Forum dan repost
ማስታወሻ - ዘነበ ወላ

በስብሐት ገብረእግዚአብሔር (1928 እስከ 2004ዓ.ም) የሕይወት ታሪክና ኪነጥበባዊ ክህሎት ዙሪያ በዘነበ ወላ በተጻፈው "ማስታወሻ" መጽሐፍ ላይ የኢትዮጵያ ቡክ ፎረም አሰናኞችና ተሳታፊዎች ውይይት ያደርጋሉ።

የውይይቱ ሊንክ:

https://www.clubhouse.com/invite/DwdI13znJQ0b03yXn5ad0Aq8Wp5dcBo9N0:jx_iw6QCLbPwS2D4t4CwauP7Is16VSledfGjvY_K2G8


ከደራሲያን እልፍኝ dan repost
‘ጊዜ ድሮ ቀረ’
(ጋዜጠኛና የኪነጥበብ ባለሙያ ተፈሪ ዓለሙ)


ድሮ ጊዜ ነበር!!!
ጠላትን ለማጥመድ ወዳጅ ለመሰብሰብ፣
ፍቅር ለመጠንሰስ ሴራ ለመሸረብ።
የፍንጥር ለማለት ለመጣል ደንቃራ፣
ለወሬ ክርክር ለምክር ለሴራ።
ለስድብ ሰላምታም፣
ለውዳሴ ሃሜታም።
አድፍጦ ለማድባት ለመደበቅ ሸሽቶ፣
ግብዣ ለመታደም ለመጋበዝ ጠርቶ።
ለጠብ ቀን ለመቁረጥ ለፍልሚያ ቀጠሮ፣
ሰዓት …
ዕለት …
ዓመት …
ጊዜ ነበር ድሮ!
ዘንድሮ ጊዜ የለም!!!
ከሚፈቅዱት ወዳጅ ከሚወድዱት ጋርም፣
ቆይታ ለመያዝ ወግ ለመደርደርም።
አላደርስ እያለ ለእግዚአብሔር ሰላምታ፣
ዛሬ ምን ጊዜ አለ ለፍቅር ጨዋታ፧
ለምን ሰው ዘንድሮም ጠብ ጠብ ያሰኘዋል፧
ምን ያኳርፈዋል፧
ያቀያይመዋል፧
እንኳን ተቀያይሞ በጥል ተራርቆ፣
ጠኗል መተያየት ከአንጀት ተነፋፍቆ።
መቼ ጊዜ አለና፧፧፧
የሃሳብ መለያየት በአንድ አለመግጠሙ፣
ያለ ነው ይኖራል አለመጣጣሙ።
በጋራ ሚከፈል ብዙ እቁብ እያለን፣
ሃሳባችን ቢለይ እኛን ምን ለያየን፧


ጎበዝ!
መኖር እንደዚህ ነው!!!
ከልዩነት በላይ ከቅራኔ ልቆ፣
አልፎ ሂያጅ ትኩሳት ግጭቶችን ንቆ።
አርቆ አስተውሎ የጋራን አላማ፣
በፈገግታ አንግቶ የኩርፊያን ጨለማ።
ጠብ መምጫውን መንገድ ባቋራጭ አሳብሮ፣
ጠብ መንጃውን መሪ አፈሙዝ አዙሮ።
አይተው እንዳላዩ እንዳልሰሙ ሰምተው፣
ቸለል ቀለል አርገው በማለፍ በመተው፡
ችሎ ተችሎ ነው ሰው አብሮ ሚኖረው!
በመቻቻል እንጂ እየተላለፉ፣
በትንሽ ትልቁ ከተኮራረፉ፧
መቼ ቀን ሊገፉ!
ይሞቷታል እንጂ ቂም እንደቋጠሩ፣
በንዴት፣ በጸጸት፣ ቁ…ጭት እያረሩ፡
መቼ ሰላም ሊያድሩ፧
ለመወቃቀስም ቆሞ ባደባባይ፣
ለመግለጥ ደመና በይቅርታ ፀሃይ።
የለ አቃቤ ሰዓት፣
ለምልጃ ደጅ ጥናት።
መቼ ጊዜ ተርፎ መቼ ጊዜ አለና፧
ድሮ እንጂ ዘንድሮ ቀርቷል ሽምግልና።
ተጣልቶ መታረቅ ላማላጅ ቀጠሮ፣
ለይቅርታ ካሣ ጊዜ የለም ዘንድሮ፡
ጊዜ ቀረ ድሮ።


@kederasiyan


Zeraf Books dan repost
"አውሮራ"
"ታላቁ ተቃርኖ"
"የቄሳር እንባ"
"አስኳላ"
"ሕንፍሽፍሽ"
"የሱፍ አበባ"
"አንፋሮ"

የተሰኙትን መጻሕፍት የደረሰው ሀብታሙ አለባቸው።


Jafer Books 📚 dan repost
ለትምህርት ለንግድ ለግል ንባብ ልምዳችሁ ይጠቅማቹሃልና የምትፈልጉት በዚህ ሊንክ    @abumame በኩል ስለዋጋው አውሩን ::


Zeraf Books dan repost
"ወዲያውኑ ቅድመ ዝግጅቴን ጀመርኩ። እናቴ ስሙኒ ሰጥታኝ ጸጉሬን 'ተማሪ ቁርጥ' ተስተካከልኩ፣ ቁንጮዬንም ተሰናበትኳት። በወቅቱ የአራተኛ ክፍል ተማሪ የነበረው ከበደ ደብተሬ ላይ አንድ ማሳሰቢያ ጻፈልኝ: ‘ይህ ደብተር የተማሪ ተስፋዬ ዜራሞ ደብተር ነው፣ ማንም እንዳይነካ። የነካ አርባ ጅራፍ ይገረፋል።’ ቆጥሬ አንብቤው ተገቢው ማስታወቂያ በተገቢው ቦታ ላይ በመስፈሩ ተደሰትኩኝ።

በዚህ አኳኋን የቄስ ትምህርቴን 'ዊዝድሮው' አድርጌ ዳዊት ሳልደግም ከሳቴ ብርሃን አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ዜሮ ክፍል ገባሁ።”

(ዘነበ ወላ ~ ልጅነት)
፨፨፨፨፨፨


Inbox @Zerafb or Call us on 0985333153 To Order. Shipping Worldwide 🇺🇸🇮🇸🇨🇦🇩🇪🇰🇷🇿🇦~🌎 & Delivering Locally.


Jafer Books 📚 dan repost
የምድራዊው ሕይወታችን ስንሞት ይገታና በሰማይ ቤት አምላካችን ዘንድ በመቅረብ ፍርዳችንን እንቀበላለን፡፡

ጥሩ የከወነ ወደ ገነት ሲገባ ትዕዛዝ ያላከበረ እና በኃጢአት የተዘፈቀ ደግሞ ወደ ሲኦል ይጣላል፡፡

የገነት እና የሲኦል ገጽታ ምን ይመስል ይሆን?

ሰው ከሞተ በኋላ “በምድር ሳለህ ጥሩ ከውነሀልና ገነት ትገባለህ!” ሲባል እንዴት ያለ ቦታ ይሆን የሚገባው?

በተቃራኒው “ስትበድል ኖረሃልና መዳረሻህ ሲኦል ነው!” ሲባልስ እንዴት ያለ ቦታ ይሆን የሚጣለው?

ገነት ማለት በልምላሜ ያማረ ፣ ምንም ነገር ተፈልጎ የማይታጣበት ፣ መሻት ሁሉ የሚፈጸምበት ቦታ ይሆን?

ሲኦል ማለትስ የማይበርድ ፍም ያለበት ፣ የሚንቀለቀል እሳት የሞላበት ቦታ ይሆን?

ቢሆን ብንል…

ሲኦል በስቃይ የተሞላች ፣ ገነት ደግሞ ስልቹነት የሚያጠቃው ቦታ ይሆን ይሆን?

እሳት ውስጥ መጣል ለስቃይ እንደሚዳርግ የሚያጠያይቅ እንዳልሆነው ሁሉ ገነት ውስጥ መኖርም እንደሚሰለች ግልጽ አይሆን ይሆን?

ምኞት ሲሰምር ፣ መሻት ይፈጸም ዘንድ ልፋት አልጠይቅ ሲል ፣ ሁሉ በእጅ ሁሉ በደጅ ሲሆን ስልቹነት መከተሉ ይቀር ይሆን?

ስልቹነት ያጠቃው ሕይወት ገነት ሲኦል አይሆንበት ይሆን?

"ዛሬ ቅዳሜ አይደለም"


ግጥም ብቻ 📘 dan repost
.........-------....የዝምታው ጩኸት....-------.........

አንተን ከመሰለህ፣ የፍቅር መግለጫው፣
በል በደንብ ኩራ፣ እስከ ዓለም ዳርቻው፣
ግን ይህን አስብ፣ ከቶ እንዳትዘነጋው።

ነገር ተገልብጦ፣ አንተኑ ብመስል፣
አስተማሪው ጎበዝ፣ ልጅቱ ነች በሳል።

ብጠፋ በድንገት፣ ከዓይንህ ብሰወር፣
ውሎዬን ብቀይር፣ ከቶ እነዳትሰኝ ቅር።

በፈገግታዬ ውስጥ፣ ከባድ ሀመም አለ፣
በዝምታዬም ውስጥ፣ ትልቅ ጩኸት አለ።

አሁን ግን------------
የውሸት መሳቁ፣ ህመሙ ከብዶኛል፣
የዝምታው ጩኸት፣ አቅሌን አስቶኛል።

ከቶ ሳላሳብቅ፣ ምንም ሳልል ዘመም፣
ጥርሴን እያሳየሁ፣ ብዙ ደበቅኩ ህመም።

አሁን ግን ይበቃል፣ ምላሽ ፈልጋለሁ፣
ጠልቶኝ ይሆን እያልኩ፣ ሠላም አጥቻለሁ።

.........................................................
             
            ሳምሪ የዝኑ ልጅ
            25-02-2016ዓ.ም

@getem
@getem
@paappii


Nomadic Poems dan repost
ኂሳዊ ንባብ በእያዩ ፈንገስ፣ ቧለቲካ

1. ይዘት

“እያዩ ፈንገስ” በቴአትር ይዘቱ ከፖለቲካዊ ስላቅ (political satire) እና ከማኅበራዊ ትችት (social commentary) ዘርፍ የሚመደብ የአንድ ሰው ተውኔት (one man show) ነው። የተውኔት ዝግጅቱ በአንዲት ሀገር ውስጥ ያለን ዐቢይ ማኅበራዊ፣ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ ክስተቶችን፣ የጊዜውን መንፈስ (sign of the times) በጥልቀት በመታዘብ እና በማጥናት፣ በመተንተን (በተለይም ፖለቲካል ዲስኮርስ እርም በኾነበት ሀገር) ኪናዊ በኾነ መንገድ የራሱ ሕልውና ባለው በአንድ ገጸ ባሕርይ በኩል የነጠረ ትችትና ምክረ ዐሳብ በማቅረብ ላይ የተመረኮዘ ነው።

ትዕይንትና ቃለ ተውኔቱም የአንድን አካል በጌጥ የተለበጠ ውድቀት በድፍረት እያነሡ መሳቂያ፣ መሳለቂያ ማድረግ ላይ ትኩረቱን ያደርጋል። የገጸ ባሕርይው ተአምኖት ለእውነት ብቻ ነው። በዚህም አንድ በሥልጣን ኃይሉ የሚመካ አካል በቁም ነገር የወሰደውን አነዋወር (way of life) ያለምንም ፍራቻ እየተሳለቀ ውድቅ ያደርግበታል። ይህን ሲያደርግ ግን እንደ ሰይፍ በኹለቱም ገጽ በተሳለ፣ በተምሳሌት በታሸ ንግግርና መነባንብ ነው። ቃለ ተውኔቱ በታሪክ (story)፣ በግጥም፣ በመረጃ (fact)… የደረጀ ነው። ተውኔቱ እንደ ውኃ ላይ ኩበት ተንሳፋፊ አይደለም። ክሶቹና ትችቶቹ መሬት በያዘ ተጨባጭ እውነታ ላይ የተመሠረቱ መኾን ይጠበቅባቸዋል። በዚህም ለግልጋሎታዊ ኪነ ጥበብነት (utilitarian art) ይቀርባል።

ጸሐፈ ተውኔቱ በረከት በላይነህ በፈረስ አፉ ገጸ ባሕርይው (through his mouthpiece character) በእያዩ ፈንገስ በኩል ለሕዝብና ለመንግሥት ያለውን ኂስ ያቀርባል። ክፍተታቸውን እንዲያርቁ፣ ጉድለታቸውን እንዲሞሉ፣ አካሄዳቸውን እንዲያቀኑ፣ ስሕተታቸውን እንዲያርሙ እየነቀሰ ይጠቁማል። ይሞግታል። ለድምፅ አልባ ዜጎችም ጉልህ ድምፅ (voice for the voiceless) ይኾናል። እንዲያም ኾኖ በውብ ሥነ ጥበባዊ አቀራረቡና በትረካ ፍሰቱ ዓይነ ግቡ ነው። በሕይወት ምስቅልቅሎሽና ቀውስ ውስጥ ያለፈው ተደራሲ በመራር ሕይወቱ ላይ እንዲስቅ ይጋብዘዋል። በሳቁ ያክመዋል። የፈውስ ጉዞ "therapeutic" ይኾንለታል። በተመሳሳይ ቅጽበት አሳዛኝ ሕይወቱ አስቂኝ እንደ ኾነ ይገልጥለታል።

እዚህ ጋር ከማሳቅ ጉዳይ ጋር በተያያዘ አንድ ነገር ላንሣ። ደረጄ ኃይሌ ስለኮሜዲ ተጠይቆ በተናገረበት አንድ ቃለ ምልልስ ላይ ቀልድ ከመረረ ሕይወት ውስጥ የሚወለድ ጥብብ እንደኾነ እንደ ተናገረ አስታውሳለሁ። የኮሜዲ አቻ አማርኛ “ቀልድ” ነው ብዬ አላምንም። ይህ ስያሜ ከያኒውንም ኾነ ይዘቱን እንደ አጫዋችና ጨዋታ ብቻ እንዲወሰድ የራሱን አሉታዊ አስተዋጽዖ እንዳደረገ ይሰማኛል።

ኮሜዲያን ዳኒ ቁንጮ ከአለቤሾው ጋር ባደረገው አንድ ቃለ ምልልስ ላይ ሰዎች ስለ ኮሜዲ ያላቸውን አሉታዊ እሳቤ የሚያንጸባርቅ የግል ገጠመኙን አውግቶ ነበር። እንዲህ ነው፦ ዳኒ በሥራው ዕውቅና እና የገንዘብ ሽልማት ማግኘቱን ተከትሎ ለእናቱ በግ አርዶ፣ ከገንዘቡ ላይም ተቆራጭ ያደርግላታል። ይህን ያየች እናቱ ቡና እያፈላች “አንተ ዳንኤል ቀልደህ ይህን ያህል ብር ካገኘህ ቁም ነገር ብትሠራ ስንት ልታገኝ ነው?” እንዳለችው ተናግሮ ነበር። መልእክቱ ግልጽ ነው። በየትኛውም “ቀልድ” ውስጥ መራር እውነታና ቁም ነገር አለ። እሴት (substance) አልባ ቀልድ ማለት ከሳቅ ጋር ሞቶ የሚረሳ ነው።

ለምሳሌ ያህል፦ የዝነኛው የቻርሊ ቻፕሊ ድምፅ አልባ ተንቀሳቃሽ ምስሎች ከበሳቅ ገዳይነታቸው ጀርባ በሴማቸው (as a theme) ከታላቁ ድቀት (the great depression) በኋላ በተከተሉ የአድማ፣ የሕዝብ አመፅ፣ የሥራ አጥነት፣ የድኅነት፣ የፋብሪካ ማሺኖች የበላይነትና በወዝ (በላብ) አደሮች ሕይወት፣ በሰው ልጅ የደስታ ኀሰሳ ላይ የተሰነዘሩ ኂሶች (bold statements) ነበሩ። ከመልእክቱ አብዛኛውን በዋናነት ያደረሰውም የዓለም ቋንቋ በኾነ “ዝምታ” ብቻ ነው። አሳየ እንጂ አልተናገረም። ነገር ግን ዓለም መልእክቱን በግልጽ ሰምቷል። መዝግቧልም።

ቻርሊ በታላቁ ድቀት ወቅት እንደ ዊንስተን ቸርችል፣ በርናንድ ሾ፣ አልበርት አንሽታይን… ካሉ ግለሰቦች ጋር የተገናኘበት አጋጣሚዎች እንዳሉ ጥቁምታ የሚሰጡ መረጃዎች አሉ። ዛሬ ዛሬም እነዚህ በቻርሊ የሲኒማ አበርክትዎች ቀድሞ የተነሡ ጉዳዮች በተለያዩ የክፍለ ዘመናችን ዐሳቢያን የመወያያ መድረኮችና የመጻሕፍት አጀንዳዎች ኾነው እንደ ዘለቁ ናቸው። ዓለም ቻርሊ ቻፕሊን ከጥምዝ ጽሕሙ፣ ከባርኔጣው፣ ከትልቅ ሸፋፋ ቆዳ ጫማው፣ ከተራ ሱቱ፣ ከአስቂኝ ገጽታው በላይ በተራማጅ ዐሳቦቹና በላቀ የትወና ጥበቡ ይዘክረዋል።

እያዩ ፈንገስ በዘውጉ ኮሜዲ አይደለም። ነገር ግን እንደ ዋና ቀለምና መሣሪያው (element and tool) ይገለገልበታል። ጥርስ ባያስከድንም ትችቱ አይነቅዝም። ተውኔቱ የተመደረከበት ጊዜና ዘመን አልፎም መልእክቱ አይነጥፍም። ከታዳሚ ሳቅ ጋር አይሞትም። የመልእክቱ ዕድሜ እንደ ታዳሚ ከምንስቀው ሳቅ ይረዝማል። ነገር ግን ስለ ኮሜዲም ኾነ፣ ስለ ፖለቲካና ማኅበራዊ ስላቅ ትክክለኛ የትርጉም ቅኝት በሌለው ማኅበረሰብና ተደራሲ ዘንድ የእያዩ ምጸቶች በተሳሳተ መንገድ ሊወሰዱ የሚችሉበት ዕድል ሰፊ ነው።

የሚያስቅ ነገርንና ኩሸትን እንደ አዝናኝ ቀልድ ብቻ የመውሰድ ተለምዷዊ አረዳድ አለ። የዚህ አረዳድ ሰለባ ከኾኑ የሥነ ጽሑፍ ሥራዎች መካከል የበዕውቀቱ ስዩምን “መግባትና መውጣት” በምሳሌነት መጥቀስ ይቻላል። በአብዛኛው አንባቢ ዘንድ የብሉይ ሥራነት ስፍራ የተሰጠው በማሳቁ እንጂ በሥነ ጽሑፋዊ ዋጋው (based on its literary values) አይመስልም።

ከማሳቁ ባሻገር አልፈን ከያኒው በመግባትና መውጣት ሥራው በስተ መጨረሻ ለማለት የፈለገውን ነገር (say) ከልቡናችን መጻፍ አለብን። ይህን ማረቅ የሥነ ጽሑፍ ኀያሲያንና ዐቃቢያን ሥራ ነው። ከተውኔቱ ማግስት ኂሳዊ ዳሰሳዎች መጻፍ አለባቸው። በዚሁ አግባብ እያዩ ፈንገስ ከ “ዕብድነቱ”፣ ከፌስታሉና ከአጀንዳው፣ ከተዥጎረጎረ ልብሱ፣ ተጠግቶ ከሚኖርበት ግድግዳ በላይ ነው። እኛም እንደ ታዳሚ በ “ቀልዱ” ሳይኾን ይዞት በመጣው መልእክት ልናስታውሰው ይገባናል።


(ይህ ጽሑፍ መግቢያ ነው። ክፍል ኹለት ይኖረዋል።)


ሊንኩን በመጫን ሰብስክራይብ በማድረግ ምርጥ ምርጥ አማርኛ ፊልሞችን ያግኙ
በቅርብ ቀን ይጀምራል




Ethio music instruments dan repost
ልዩ እና ጊዜ የማይሽረው ተሰጥኦ ያላቸውን የኢትዮጵያን አርቲስቶችን የሚያሳዩ የክብር ቴምብሮች ልናትም ነው! ማንን እንምረጥ? በቴሌግራም ቻናላችን ድምፅ በመስጠት ለወደዱት ድጋፍ ይስጡ!

https://t.me/Ethiopianpostal/696

Ethiopost is celebrating Ethiopian artists! We will be printing honorary stamps depicting unique and timeless talent, and we need your help!

Vote for your favorite on our Telegram channel!
https://t.me/Ethiopianpostal/696

20 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.