ከ25 ዓመት እድሜ በላይ ተገልጋዮች የሚታተሙ ፓስፖርቶች የእድሳት ጊዜያቸው ወደ 10 ዓመት ከፍ ተደረገ::
የእድሳት አገልግሎት ቁጥርን ለመቀነስ ከ25 ዓመት እድሜ በላይ ተገልጋዮች የሚታተሙ ፓስፖርቶች የእድሳት ጊዜያቸው ከአምስት ዓመት ወደ አስር ዓመት ጊዜ ገደብ እንደሚደረግ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት አስታወቀ።
የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት የ2017 በጀት ዓመት የሩብ ዓመት አፈፃፀሙን በተመለከተ በሰጡት መግለጫ በየብስ እና በአየር ኬላዎች የሚሰጡ አገልግሎቶች ምቹና ቀልጣፋ እንዲሆኑ በርካታ ስራዎች ተመሰራታቸውን ገልጸዋል።
በያዝነው በጀት ዓመት በ3 ወር ውስጥ 1 ነጥብ 1 ሚሊየን በላይ መንገደኞችን ማስተናገዱንም ጠቁመዋል።
በተቋሙ የሚስተዋሉ የአቅም ውስንነቶችን ከመቅረፍ አኳያ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሯ የሰው ኃይል አደረጃጀቱን የተሻለ ለማድረግ 125 ለሚሆኑ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የአንድ ወር ስልጠና መሰጠቱን አመልክተዋል።
በሩብ ዓመቱ 478 ሺሕ ቡክሌቶች ውስጥ 357 ሺሕ ፓስፖርቶች ተሰራጨ ሲሆን በዚህም 97 ነጥብ 2 በመቶ አፈፃፀም ተመዝግቧልም ነው ያሉት።
በሩብ በጀት ዓመቱ በኢ ቪዛ 259 ሺሕ 705 ደንበኞች አገልግሎት ማግኘታቸውን አንስተው በቀጣይ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራርን ለመተግበር ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑም ጠቁመዋል።
ከመጪው ጥር ጀምሮ የኢ-ፓስፖርት አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምርም ተቋሙ አስታውቋል።
@maraki_news
@maraki_news
የእድሳት አገልግሎት ቁጥርን ለመቀነስ ከ25 ዓመት እድሜ በላይ ተገልጋዮች የሚታተሙ ፓስፖርቶች የእድሳት ጊዜያቸው ከአምስት ዓመት ወደ አስር ዓመት ጊዜ ገደብ እንደሚደረግ የኢሚግሬሽን እና ዜግነት አገልግሎት አስታወቀ።
የአገልግሎቱ ዋና ዳይሬክተር ሰላማዊት ዳዊት የ2017 በጀት ዓመት የሩብ ዓመት አፈፃፀሙን በተመለከተ በሰጡት መግለጫ በየብስ እና በአየር ኬላዎች የሚሰጡ አገልግሎቶች ምቹና ቀልጣፋ እንዲሆኑ በርካታ ስራዎች ተመሰራታቸውን ገልጸዋል።
በያዝነው በጀት ዓመት በ3 ወር ውስጥ 1 ነጥብ 1 ሚሊየን በላይ መንገደኞችን ማስተናገዱንም ጠቁመዋል።
በተቋሙ የሚስተዋሉ የአቅም ውስንነቶችን ከመቅረፍ አኳያ በርካታ ስራዎች መሰራታቸውን የገለጹት ዋና ዳይሬክተሯ የሰው ኃይል አደረጃጀቱን የተሻለ ለማድረግ 125 ለሚሆኑ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የአንድ ወር ስልጠና መሰጠቱን አመልክተዋል።
በሩብ ዓመቱ 478 ሺሕ ቡክሌቶች ውስጥ 357 ሺሕ ፓስፖርቶች ተሰራጨ ሲሆን በዚህም 97 ነጥብ 2 በመቶ አፈፃፀም ተመዝግቧልም ነው ያሉት።
በሩብ በጀት ዓመቱ በኢ ቪዛ 259 ሺሕ 705 ደንበኞች አገልግሎት ማግኘታቸውን አንስተው በቀጣይ በቴክኖሎጂ የተደገፈ አሰራርን ለመተግበር ትኩረት ተሰጥቶ እየተሰራ መሆኑም ጠቁመዋል።
ከመጪው ጥር ጀምሮ የኢ-ፓስፖርት አገልግሎት መስጠት እንደሚጀምርም ተቋሙ አስታውቋል።
@maraki_news
@maraki_news