ማኅበረ ቅዱሳን ዋናው ማእከል


Kanal geosi va tili: Efiopiya, Amharcha
Toifa: ko‘rsatilmagan


Похожие каналы

Kanal geosi va tili
Efiopiya, Amharcha
Toifa
ko‘rsatilmagan
Statistika
Postlar filtri


ቡስካ ማር




በተለያዩ አከባቢዎች በልዩ ልዩ የትምህር ዘርፍ ሲማሩ የቆዩ የግቢ ጉባኤያት  ተማሪዎች መመረቃቸው ተገለጸ

የካቲት ፲፰/፳፻፲፯ ዓ.ም 

በተለያዩ አከባቢዎች በልዩ ልዩ የትምህር ዘርፍ ሲማሩ የነበሩ የግቢ ጉባኤያት  ተማሪዎች በከፍተኛ ማዕረግ  መመረቃቸው ተገልጿል።

ከእነዚህም መካከል በመቱ፣ በወላይታ፣በአዲስ አበባ፣በቡሌ ሆራ ፣በአርባምንጭ ና በደብረ ታቦር ዩንቨርስቲዎች ላይ ሲማሩ የቆዩ ግቢ ጉባኤያት ተማሪዎች  ይጠቀሳሉ።

በምርቃት  መርሐ ግብሮቹ  ወረብ፣ ትምህርተ ወንጌልና መልእክት የተላለፈ ሲሆን ለተመራቂ ተማሪዎች የመስቀል ሥጦታ ተበርክቶላቸዋል ።


የቅጥር ማስታወቂያ


This week is also known as “Hercules’s fast.” The naming is related with the finding of the Holy Cross that the Lord was crucified on. The King regained back the cross from the theft committed by King of Persia, Cyrus. Then, the people pronounced it to the King demanding justice. The King brought back the Cross onwards a battle with the Persian King. But after his triumph on the war, he faced another trial. The rule of Church on killing stated that “a person who killed shall fast his entire life.” Therefore, the people fasted the fasting King Hercules’s was order to fast by distributing the age of the King amongst themselves. In the commemoration of him, the first week is known as “The Fast of Hercules” and all Christians fast it. (Book of Ethiopian Synaxarium Megabit 10)
Though Zewerede is not included amongst the forty days our Lord fasted, the Church made order and included it amongst The Great Lent. We then fast it as an order but not by owns will.
May God’s mercy be upon us throughout this fast; Amen!


He Who Comes Down
The First Sabbath of “The Great Lent” according to our Holy Church’s teachings is known as “Zewerede” to mean “He Who Comes Down.” Saint Jared’s hymn for this holiday states about The Holy Son Coming from the heavens as He vowed to the first mankind Adam and for the salvation of all human race. (Book of Tsome Deguua)
This week is the commemoration of the Lord Who Came Down from His mysterious in highness and everlasting holiness and be revealed on this vain world, in search of man by His unconditional love.
Saint Athanasius said, “For this purpose, then, the incorporeal and incorruptible and immaterial Word of God entered our world. In one sense, indeed, He was not far from it before, for no part of creation had ever been without Him Who, while ever abiding in union with the Father, yet fills all things that are. But now He entered the world in a new way, stooping to our level in His love and Self-revealing to us. He saw the reasonable race, the race of men that, like Himself, expressed the Father's Mind, wasting out of existence, and death reigning over all in corruption. He saw that corruption held us all the closer, because it was the penalty for the Transgression; He saw, too, how unthinkable it would be for the law to be repealed before it was fulfilled. He saw how unseemly it was that the very things of which He Himself was the Artificer should be disappearing. He saw how the surpassing wickedness of men was mounting up against them; He saw also their universal liability to death. All this He saw and, pitying our race, moved with compassion for our limitation, unable to endure that death should have the mastery, rather than that His creatures should perish and the work of His Father for us men come to nought, He took to Himself a body, a human body even as our own. Nor did He will merely to become embodied or merely to appear; had that been so, He could have revealed His divine majesty in some other and better way. No, He took our body, and not only so, but He took it directly from a spotless, stainless virgin, without the agency of human father--a pure body, untainted by intercourse with man. He, the Mighty One, the Artificer of all, Himself prepared this body in the virgin as a temple for Himself, and took it for His very own, as the instrument through which He was known and in which He dwelt. Thus, taking a body like our own, because all our bodies were liable to the corruption of death, He surrendered His body to death instead of all, and offered it to the Father. This He did out of sheer love for us, so that in His death all might die, and the law of death thereby be abolished because, having fulfilled in His body that for which it was appointed, it was thereafter voided of its power for men. This He did that He might turn again to incorruption men who had turned back to corruption, and make them alive through death by the appropriation of His body and by the grace of His resurrection. Thus He would make death to disappear from them as utterly as straw from fire.” (On the Incarnation: Saint Athanasius page 6)
The first Sabbath “Zewerede” is also known as “Adam’s Week.” The Lord and Savior Jesus Christ Came Down and Be Born from the Virgin Saint Mary, to search for Adam, raise him from his failure; take him out from hell and for the fulfillment of the prophecy. The Apostle Paul said, “But when the fullness of the time had come, God sent forth His Son, born of a woman, born under the law.” (Galatians 4:4)


ዘወረደ
እንኳን አደረሳችሁ!

ዘወረደ ማለት "ከላይ የመጣ፣ የወረደ'' ማለት ነው። ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችን "ዘወረደ እምላዕሉ አይሁድ ሰቀሉ ወሚመ ኢያእመሩ እግዚአ ኩሉ ዘየሐዩ፤ አዳምን ለማዳን ከሰማይ የወረደውን አምላክ አይሁድ ሰቀሉት፤ የሰማይ ሥልጣን ያለው የሁሉ ጌታ እንደሆነም ምንም አላወቁም" እያለች በሰንበት ዋዜማ ዜማውን መሐትው (መግቢያ) አድርጋ የሳምንቱን ዜማ በማስተጋባት የጌታችንን ከሰማይ መውረድ ታመሠጥርበታለች፤ ታመሰግንበታለች። (ጾመ ድጓ፥ ዘዘወረደ ዋዜማ)
ይህን ሳምንት በልዕልና በዘለዓለማዊ ቅድስና እና በማትመረመር ጥበብ ራሱን ሰውሮ የሚኖር አምላክ በገሃድ ለሰው ልጅ የተገለጠበትን፣ ዘለዓለማዊ አምላክ ሰውን ከተደበቀበት ለመፈለግ ብሎ ''ኦ አዳም አይቴ ሀሎከ- አዳም ሆይ ወዴት ነህ" እያለ በማያልቅ የፍቅር ድምፅ ፍለጋ ወደ ዱር (ወደ ዓለም) የገባበትን ሳምንት የምንዘክርበት ነው። አምላካችን እግዚአብሔር የሰውን ልጅ ምን ያህል በበዛ ፍቅሩ እንደሚፈልገው፣ ከፍ ላለ ዓላማውም እንዳጨው ያሳየበት፣ ከሁሉም ደግሞ በሕሊና ሊታሰብ የማይችለውን የሰማይ አኗኗሩን ትቶ በሚታይ የአዳም ሥጋ የተገለጠበት፣ መጋረጃው እሳት፣ ዙፋኑ እሳት፣ ልብሱ እሳት የሆነው አምላክ በሚበሰብስ ሥጋ የተገለጠበት፣ በጨርቅ፣ ያንን የሚያስደነግጥ መለኮታዊ ክብሩን ስለ ሰው ልጅ መዳን ተጨንቆ በሕፃን አምሳል ተገልጦ በበረት የተገኘበትን ሳምንት እናስብበታለን። ቅዱስ አትናቴዎስ የእግዚአብሔር ልጅ ለሰው ልጅ ድኅነት ሲል መወለዱን እንዲህ በማለት ይገልጠዋል፡፡ "ለዚሁ ዓላማ (ለሰው ልጅ ድኅነት) የማይበሰብስ፣ የማይሞት አካል ያለው የእግዚአብሔር ልጅ ወደዚህ ዓለም ገባ" (On the Incarnation: Saint Athanasius page 6)
ዘወረደ ከዚህ ትርጉም ባለፈ የአዳም ሳምንት ተብሎ ይጠራል። አዳምን ከጠፋበት ሊፈልግ፣ ከወደቀበት ሊያነሣ፣ ከገባበት ሊያወጣ የትንቢቱ ጊዜ በደረሰ ሰዓት ከብላቴናይቱ ድንግል ተወልዶ ተስፋ አዳም ተፈጽሞበታልና። “ነገር ግን የዘመኑ ፍጻሜ በደረሰ ጊዜ እግዚአብሔር ከሴት የተወለደውን ከሕግም በታች የተወለደውን ልጁን ላከ፤" እንዲል ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ (ገላ.፬:፬)።
ሠለስቱ ምዕት በጸሎተ ሃይማኖት "ዘበእንቲአነ ለሰብእ ወበእንተ መድኃኒትነ ወረደ እምሰማያት፤ ተሰብአ ወተሰገወ እመንፈስ ቅዱስ ወእማርያም እምቅድስት ድንግል፤ ስለ እኛ ስለ ሰዎች እኛን ለማዳን ከሰማይ ወረደ በመንፈስ ቅዱስ ግብር ከቅድስት ድንግል ማርያም ፍጹም ሰው ሆነ" (ጸሎተ ሃይማኖት) እንዲሉ በሥጋ የአዳምን ዘር ለማዳን ሰው ሆኖ ለአዳም የገባውን ኪዳን ፈጸመ። የሥጋ ዘመዳችንም ሆነ። (ሃይማኖተ አበው ዘቅዱስ ጎርጎርዮስ)
ሌላኛው ይህ ሳምንት ጾመ ሕርቃል በመባል ይታወቃል። ይህም በ፮፻፲፬ ዓ.ም የፋርስ ንጉሥ ኪርዮስ ኢየሩሳሌምን ወርሮ፣ አብያተ ክርስቲያናትን ዘርፎ እና መዝብሮ ክርስቲያኖችን ማርኮ ንግሥት ዕሌኒ ካሠራችው ቤተ መቅደስ የክርስቶስን መስቀል ዲያቆናትን አሸክሞ በምርኮ ወሰደ። ከምርኮ ያመለጡ ክርስቲያኖች ወደ ሮሙ ንጉሥ ከ፲፬ ዓመት በኋላ በ፮፻፳፰ ዓ.ም ለንጉሥ ሕርቃል ጩኹታቸውን ያሰማሉ፤ እርሱም በፋርሱ ንጉሥ በኪርዮስ ላይ ድል አግኝቶ መስቀሉን መለሰላቸው። በሕገ ቤተ ክርስቲያን ‹‹ሰው የገደለ ዘመኑን ሁሉ ይጹም›› የሚል በሐዋርያት ስለተደነገገ የንጉሡን ዕድሜ ተከፋፍለው አንድ ሳምንት ደርሶባቸው ስለ ንጉሡ ጾመወለታል፤ በዚህም የእርሱ መታሰቢያ ይሆን ዘንድ ይህ ሳምንት ጾመ ሕርቃል በመባል ይጠራል። እኛም ይህንን ዋቢ አድርገን እንጾማለን። (ምንጭ፡- ስንክሳር ዘወርኀ መጋቢት ፲)
ዘወረደ ከአርብዓው ዕለት የሚካተት ባይሆንም ቤተ ክርስቲያን ትእዛዝ አድርጋ ከአርብዓው ዕለታት ጋር ደምራ እንድንጾም ሕግ ሠርታለታች። እኛም እንደ ፈቃድ ሳይሆን እንደ ትእዛዝ ተቀብለን እንጾማለን።

ቅዳሴ፡- ቅዳሴ እግዚእ

"ዘበእንቲአነ ለሰብእ ወበእንተ መድኃኒትነ ወረደ እምሰማያት፤ ተሰብአ ወተሰገወ እመንፈስ ቅዱስ ወእማርያም እምቅድስት ድንግል፤ ስለ እኛ ስለ ሰዎች እኛን ለማዳን ከሰማይ ወረደ በመንፈስ ቅዱስ ግብር ከቅድስት ድንግል ማርያም ፍጹም ሰው ሆነ፡፡" ወንጌል (ዮሐ.፫፥፲-፩፬)
ምስባክ ዘነግህ:- (መዝ.፪፥፲፩) "ዘበእንቲአነ ለሰብእ ወበእንተ መድኃኒትነ ወረደ እምሰማያት፤ ተሰብአ ወተሰገወ እመንፈስ ቅዱስ ወእማርያም እምቅድስት ድንግል፤ ስለ እኛ ስለ ሰዎች እኛን ለማዳን ከሰማይ ወረደ በመንፈስ ቅዱስ ግብር ከቅድስት ድንግል ማርያም ፍጹም ሰው ሆነ"
ምስባክ ዘቅዳሴ:- (መዝ.፪፥፲፩) “ተቀነዩ ለእግዚአብሔር፤ ወተሐሠዩ ሎቱ በረዓድ፤ አጽንዕዋ ለጥበብ ከመ ኢይትመዐዕ እግዚአብሔር፤ ለእግዚአብሔር በፍርሃት ተገዙ፤ በረዓድም ደስ ይበላችሁ፤ ጌታ እንዳይቆጣ ተግሣጹንም ተቀበሉ፡፡”
መልእክታት:-
ሠራኢ ዲያቆን ዕብ.፲፫፥፲፯
ንፍቅ ዲያቆን ያዕ. ፬፥፮- ፍጻሜው
ንፍቅ ካህን የሐዋ. ፳፭፥፲፫-ፍጻሜ

ስብሐት ለእግዚአብሔር፤ አሜን!


የሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ የሕክምና እና የጤና ሳይንስ ኮሌጅ  የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎች መመረቃቸውን ማኅበረ ቅዱሳን ሐዋሳ ማእከል አስታወቀ  ፡፡

የካቲት ፲፭/፳፻፲፯ ዓ.ም

ማኅበረ ቅዱሳን ሐዋሳ ማእከል በሐዋሳ ደብረ ኢየሱስ ወቅድስት አርሴማ ቤተ ክርስቲያን ከ127 በላይ በልዩ ልዩ የጤና ዘርፍ ትምህርታቸውን ሲከታተሉ የቆዩ የሐዋሳ ዩኒቨርሲቲ ጤና ሳይንስ ኮሌጅ  የግቢ ጉባኤያት ተማሪዎች በትናንትናው ዕለት የካቲት 14 ቀን 2017 ዓ.ም ተመርቀዋል።

በምርቃት መርሐ ግብሩ ላይ የግቢ ጉባኤው የአብነት መምህር በሆኑት የኔታ ነቃ ጥበብ የወንጌል ትምህርት ተሰጥቷል።

በተጨማሪም በተመራቂ ተማሪዎች መዝሙር እና ወረብ ቀርቧል፡፡

በዕለቱም የቤተ ክርስቲያኑ አባቶች ካህናት፣ምእመናን እና የተመራቂ  ቤተሰቦች የተገኙ ሲሆን ለተመራቂ ተማሪዎችም የአደራ መስቀል ተበርክቶላቸዋል።


እሱም ተስፋ ቆርጦና በጌታችን መንፈሳዊ ልዕልና ተሸንፎ ሂዶአል::
የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!
ከጌታችን ጾም የምንወስደው ብዙ ትምህርት አለ፤ ከሁሉ በፊት ሰው በሕይወት መኖር የሚችለው በእንጀራ ብቻ ኣይደለም ብሎናል፤ ይህ ኣባባል በሕይወት ለመኖር እንጀራ አያስፈልግም ማለት ኣይደለም፤
ሕይወትን ማኖር የሚቻለው በእንጀራ ብቻ እንደ ሆነ አድርገን እንዳናስብ ግን ቃሉ ያስተምራል፤ይህም በዓለማችን በየዕለቱ የምናውቀው ሓቅ ነው፤ ብዙ ሰዎች እንጀራን ሳያጡ በየዕለቱ ሕይወትን ያጣሉ፤ ምክንያቱም በሕይወት ለመኖር የእግዚአብሔር ቃልም እንጂ እንጀራ ብቻው በቂ አይደለምና ነው::
ዓለማት ሁሉ በእግዚአብሔር ቃል ሁኑ ተብለው በቃሉ እንደተፈጠሩ፤ በቃሉም ጸንተው እንደሚኖሩ ኋላም በቃሉ እንደሚያልፉ ሁሉ የሰው ሕይወትም በዚህ ቃል ይወሰናል፤

እንጀራ ኖረም አልኖረ ቃሉ በቃ ካለ ያበቃል፤ ኑር ካለ ደግሞ እንጀራ ባይኖርም ይኖራል፤ ስለዚህ በሕይወታችን ወሳኝ ሥልጣን ያለው የእግዚአብሔር ቃል እንጂ፣ እንጀራ ብቻ ኣለመሆኑ ጌታችን በዚህ ኣስተምሮናል::
ከዚህም ሌላ የዲያብሎስን ፈተናዎች እንዴት በድል ማለፍ እንደምንችል ጌታችን በተግባር ኣሳይቶናል፤ ጌታችን ዲያብሎስን ያሸነበፈበት ስልት በመንፈስ ልዕልና እንጂ በዱላም፣ በካባድ መሳሪያም ኣይደለም፤ አለመሆኑንም የድርጊቱ ሂደት በግልጽ ያመለክታል፤ እንግዲያውስ እኛም ዲያብሎስን የምናሸንፈው በዚህ የመንፈስ  ልዕልና ነው ማለት ነው::
ይህም ማለት በእግዚአብሔር የተከለከሉትን ግብረ ኃጣውእ እንድንፈጽም ዲያብሎስ ኅሊናችንን ሲገፋፋው፣ ያን ጊዜ ዲያብሎስ ሊፈትነን እየከጀለ እንደሆነ መንቃት  ያስፈልገናል::
ጌታችን እንዳሳየንም ለክፉው ግብረ ኃጢኣት የእሺታ መልስ ሳይሆን የእንቢታ ግብረ መልስ መስጠት ይገባናል ማለት ነው፤ ይህንን ኣቅዋም የሕይወታችን ቀዋሚ መርሕ ካደረግን፤ ዲያብሎስ እየተሸነፈ፣ እኛም እያሸነፍን እንኖራለን፤ ይህንን ስንለማመድ ሓሳባችን ወይም መንፈሳችን ከዲያብሎስ በላይ የላቀና የተራቀቀ ይሆናል፤
ዲያብሎስ ረቂቅ ነው፤ የሚጣላንም ረቂቁን አእምሮኣችን በመጠቀም ነው፤ እኛም እሱን መዋጋትና ማሸነፍ የምንችለው ረቂቁ ኣእምሮኣችን ከሱ የላቀና የረቀቀ ኣድርገን በመጠቀም መሆኑን መገንዘብ ይገባል፤ይህን ካደረግን እሱ በኛ ላይ  ዓቅም ኣይኖረውም::

የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት!
ጾመ ኢየሱስ እያልን በየዓመቱ የምንጾመው የታላቁ ጾማችን ዓላማ ዲያብሎስን ለማሸነፍ ነው፤ የዲያብሎስ ማሸነፊያ ስልት የመልካም ኅሊና ልዕልና ነው፤
ሰውነታችን በመብልና በመጠጥ ሲደነድን መልካም ኅሊና በውስጣችን ዓቅም ያጥረዋል፤ መልካም ኅሊና ሲያጥረን ዲያብሎስ ዘው ብሎ ይገባና ወደ ክፉ ኅሊና፣ ከዚያም ወደ ግብረ ኃጢኣት ይወስደናል፤ በዚህ ጊዜ እኛ ተሸናፊዎች እሱ ኣሸናፊ ይሆናል፤

በአንጻሩ ደግሞ ሰውነታችን ከመብልና ከመጠጥ ሲለይ መልካም ኅሊና፣ ቊጥብነት፣ ማስተዋልና ማመዛዘን በውስጣችን ትልቅ ጉልበት ያገኛሉ፤
እነሱ ጐለበቱ ማለት ዲያብሎስ መግቢያ አጣ ማለት ነው፤ እሱ ካልገባ ግብረ ኃጢኣት አንፈጽምም፤ በዚህ ጊዜ ዲያብሎስ ተሸናፊ እኛ ኣሸናፊዎች እንሆናለን፤ ስለሆነም ጾምን የምንጾመው በዚህ ስልት ዲያብሎስንና ግብረ ኃጢአትን ለማሸነፍ  ነው::
ከዚህ አኳያ ዲያብሎስን ለማሸነፍ መጾም ግድ ስለሆነ ጌታችን በከፈተልንና ባሳየን መንገድ እንጾማለን፤ እንግዲህ በወርኃ ጾም ከመልካም ኅሊና የሚመነጭ መልካም ስራ ማከናወን ግድ ይለናል፤

ምክንያቱም ጾምን የምንጾመው መልካም ኅሊና ኖሮን ለእግዚአብሔር ለመታዘዝና ለመገዛት፣ ከዚያም ከቃሉ በተነገረን መሠረት የተራቡትን ልንመግብ፣ የተራቈቱትን ልናለብስ፣ የተጣሉትን ልናስታርቅ፣ ፍትሕ ያጡትን ፍትሕ እንዲያገኙ ልናደርግ፣ ለንኡሳን የሕብረተ ሰብ ክፍሎች የተለየ ትኵረት ልንሰጥ፤ እኩልና ፍትሓዊ የሀብት ክፍፍል በሰው ልጆች መካከል ልናረጋግጥ፣ ሰብኣዊ ክብር እንዳይነካ ጦርነት፣ ጥላቻ፣ አደገኛ የቃላት ውርወራና መነቃቀፍ እንዲቀር ልናደርግ ነው፤
በዚህ መንፈስ ጾሙን ከጾምን ጾማችን ግቡን መትቶአል፤ ዲያብሎስም ተሸንፎአል ማለት ነው፤ ስለሆነም በዚህ መንፈስ ጾሙን ልንጾም ይገባል፡፡

በመጨረሻም፡-
ወርኀ ጾሙን የተራበውን በመመገብ የተራቈተውን በማልበስ በኃላፊነት ያለን የኅብረተሰብ መሪዎችም ፍትሕንና እኩልነትን በማስፈንና ከነገሮች ሁሉ በፊት ለሰላምና ለአንድነት ቅድሚያ በመስጠት ጾሙን እንድናሳልፍ በእግዚአብሔር ስም አባታዊ መልእክታችንን እናስተላልፋለን::
መልካም ወርኀ ጾም ያድርግልን
እግዚአብሔር ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
አሜን!!

                    አባ ማትያስ ቀዳማዊ
       ፓትርያርክ   ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ
ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለሃይማኖት

           የካቲት ፲፯ ቀን ፳፻፲፯ ዓ.ም
             አዲስ አበባ፣ ኢትዮጵያ
ምንጭ የኢ/ኦ/ተ/ ቤተ ክርስቲያን  ሕዝብ ግንኙነት መምሪያ


መልእክተ ቅዱስ ፓትርያርክ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን፣

በሀገር ውስጥና በውጭ ሀገር የምትገኙ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ተከታዮች ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት በሙሉ፤
የዲያብሎስን የፈተና ወጥመዶች በጣጥሶ በድል ኣድራጊነት የተገለጠው ጌታችን ኣምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለሁለት ሺሕ ዐሥራ ሰባት ዓመተ ምሕረት የጾመ ኢየሱስ ሱባዔ ኣደረሰን አደረሳችሁ!
“አኮ በኅብስት ክመ ዘየሓዩ ሰብእ አላ በኵሉ ቃል ዘይወፅእ እምኣፉሁ ለእግዚአብሔር፡- ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ ኣይኖርም” (ማቴ.፬÷፬)፤
ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በፈለገ ዮርዳኖስ ከተጠመቀ በኋላ ሳይውል ሳያድር ወዲያውኑ ወደ በረኻ በመሄድ አርባ ቀንና አርባ ሌሊት ጾመ፡፡
በአርባዎቹ ቀናት ሁሉ በቀንም ሆነ በሌሊት ምንም አልበላም ነበር፤ ካርባ ቀንም በኋላ ተራበ፤ በመብል ሰውን ከእግዚአብሔር ጋር ማጣላት ልማዱ የሆነ ዲያብሎስም መራቡን ኣይቶ ለምን ትራባለህ?
እነዚህ ድንጋዮች እንጀራ ይሁኑ ብለህ እዘዝና ብላ፤ የእግዚአብሔር ልጅ አይደለህምን? ይህንን ማድረግ ኣያቅትህም ብሎ በመብል ምክንያት የሱ ታዛዥ እንዲሆን ፈተነው::
በዚህ ጊዜ የጌታችን መልስ “ሰው ከእግዚአብሔር አፍ በሚወጣ ቃል ሁሉ እንጂ በእንጀራ ብቻ ኣይኖርም” የሚል ነበረ፤
ጌታችን በዚህ አባባሉ የዲያብሎስን ክፉ ሐሳብ የሚንድ እንጂ የእሱ ታዛዥ አለመሆኑን ኣሳየ፤ ዲያብሎስ በዚህ ሳያበቃ በትዕቢት በፍቅረ ንዋይና በባዕድ አምልኮ ሊጥለው ደጋግሞ ሙከራ አደረገ፤ ግን አልተሳካለትም፤
በመጨረሻም ጌታ “ሑር እምድኅሬየ ሰይጣን፣ ሰይጣን ከኋላዬ ወግድ” ብሎ እኩይ ተግባሩን ውድቅ ኣድርጎበታል፤


ይህንም እንዳየች የኃጥአንንም መኖሪያ ያሳዩአት ዘንድ ወደ ኃጥአን ማደሪያም በወሰዷት ጊዜ የእነርሱን ሥቃይ አይታ እመቤታችን ርኅርኅተ ልብ ናትና ልጇ ከመከራ ያወጣቸው ዘንድ በጎልጎታ ስትጸልይ የካቲት ፲፮ ቀን ልጇ ወዳጇ የእናቱን ልመና ሰምቶ እልፍ አእላፋት መላእክትን አስከትሎ መጥቶ ሌላው ይቅርና ቀዝቃዛ ውኃ እንኳን በስማ የሰጠውን እንደሚምርላት ነግሯት ይህም የሰጣት ቃል ኪዳን እንዳይታበይ በራሱ ምሎላታል፡፡ (ሙሉ ሐሳቡን የካቲት ፲፮ ስንክሳር ላይ ይመልከቱ።)
የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ጸሎቷ፣ አማላጅነቷና ተረዳኢነቷ አይለየን፤ አሜን!

11 ta oxirgi post ko‘rsatilgan.