የጉዞ ማስታወሻ
በሜሪ ጌታለም
ሁለት ያባረረ.....እንደምታውቁት ነው(ርዕስ)
ሞላም ጎደለ ያለ ስስት ማካፈል ከሞላበት የአያቶቼ ገጠራማ መንደር ወደከተመው ዘግቶ ፈጅ ሀገሬ ለመሄድ እያዋከቡ በወሰዱኝ ከ ሶስት በላይ ወያላወች ግፊት እና ጉትጎታ የጨረጨሰች ሚኒባስ ውስጥ ገባሁ..................
በእነሡ ጩኸት እና ወከባ ወላ ገደል ውስጥ ቢሉኝ የምገባ አይነት ነኝ...............ሲፈጥረኝ የተንቀዠቀዠ ነገር አልወድም።
አንዳንዴ እንደውም ሮጥክም አዘገምክ መሆን ያለበት ከመሆን አለመሆን ያለበት ካለመሆን ዝንፍ አይልም የምል ሠው ነኝ.................................................
አብዝቶ መንቀራፈፍ ባልወድም ከበዛ ወከባ ብዙ እጅ ይሻለኛል።ያንዱን ጥፍጥና ሳያጣጥሙ ሌላኛውን ለመቅመስ መስገብገብ፣አንዱን በዉል ሳይዙ ወደሌላው መዝለል አይነት ብክነት..................................................
ሁሉም በጊዜው ሲሆን ይዋብ የለ ........ነገን ዛሬ ላይ ለመኖር መንደፍደፍ ብሎ ነገር አላውቅም።
የጊዜ ጥቅም አለቅጥ የገባቸው የሚመስሉኝ አንዳንድ ሠወች ከልክ በላይ ሲሮጡ የተቀመጠላቸውን አልፈው ካልሆነ ቦታ ላይ ራሳቸውን በፍለጋ የሚያደክሙ ይመስለኛል(30 የሆነው በምክንያትም አይደል)..............................ኤታባቱ!ሠው እንደው አንዳሻው በሀሳብ የመፈንጨት ነፃነቱ ትልቁ ፀጋው ሳይሆን አይቀርም.......አንገት የሚያስደፋ ኮርኳሚ፣ደረት የሚያስነፋ አጨብጫቢ በሌለበት ለብቻ ከሀሳብ ጋር መላፋት።
የመጨረሻ ወንበር ላይ ገና አራት ሠወች ብቻ ስለነበርን አሳፍቼ ተቀምጬ በሀሳብ ከሄድኩበት 2 በተመሳሳይ ዕድሜ ላይ እንደሆኑ የገመትኳቸው ወጣቶች ወግ እንደ ድንገት ጆሮየ ውስጥ ጠልቆ ስለሳበኝ....መቋጫ የሌለውን ሀሳቤን በየትም አይሄድም ተውኩትና ሙሉ ትኩረቴን ወደ እነሡ አደረግኩ።
........."እና የታክሲ ረዳት ነኝ አልሽኝ?"አለ ወንዱ።
እኔ ደግሞ አንገቷ ስር ተወሽቆ የተጋለጠ ገላዋ ላይ እያፈጠጠ ሳየው ትኩስ ፍቀረኛሞች መስለውኝ..... ገና በትውውቅ እንደዚ መለጠፍ .....ወወይ ዘንድሮ..... ወይይይ ዘንድሮ።
ቁጭ ብድግ የምትል ይመስል ከትከሻዋ ከፍ ዝቅ እያለች ጆሮ የሚበሳ ሳቋን ለቀቀችው።ልጁ የተናገረው ከሳቀችው ጋር አልመጣጠን ቢለኝ ያመለጠኝ ነገር እንዳለ በማሰብ .....ቀጣዩን በደንብ ለመከታተል ጠጋ ብየ በመካከላችን ያለውን ርቀት አጠበብኩት።
ሲፈጥረኝ ወግ አፍቃሪ አድርጎ ነው............በልጀነቴ ነው አሉ እቤታችን ሠው በመጣ ቁጥር በእንቅልፌ መጣ አሣብቤ የክብር አልጋው ላይ(ሳሎን ውስጥ ለዕይታ ይሁን ለክፍተት መሙያ አሉ በተባሉ አልጋ ልብሶች አሸብርቆ የሚቀመጥ )ተዘርሬ እየተቁለጨለጭኩ የሠፈሩን ሰው ወግ መቃረም የጀመርኩት።እ
ንግዳ እያለ አብሮ መቀመጥማ ነውር ነዋ........በቃ ዝም ማለትም ዝም ያለ ነገርም ይጎረብጠኛል።
ዝምብም ይግባ በረሮ የፈለጉትን ተናግሮ የመሸበት ማደር! ቢሆንም ግን ቀኑን በሙሉ ጉንጫ አልፋ ዝባዝንኬ ስዘብብ የምውልም አይደለሁም።
"ሴት ሆነሽ ግን አይከብድም?"
ጆሮዋ ስር ተለጥፎ እስከ ሌላኛው መኪና ድረስ በሚሠማ ድምፅ ከመለፍለፉ በላይ ልጅቷን እንደልብ አላሳየኝ ስላለ አናዶኛል።
"ኸረ ምንም አይከብድም ዋና ስራየ እኮ የሆነ ትልቅ ሆቴል ጥበቃነት ነው"አለች እንደሰውነቷ ቅጥን ባለች ድምፅ እየተቅበጠበጠች።
"ኦ እና በቃ ስልክሽን ስጭኝና የሆነ ትልቅ ሆቴላችውን special.. ራት ልጋብዝሽ አላት እንደሷ እየተሟዘዘ።
ወደእሷ ለመጠጋት ከመንሻፈፉ የተነሳ እንዲሁ ወደጎን እንዳጋደለ እንዳይቀር ሰግቼለታለሁ።
እኔ ዝም'ም....... ልበል ከስሩ ሊነቀል የደረሰ ዛፍ እኮ ነው የሚመስለው በቅጡ እንኳን አልተቀመጠም።
እኔም ከእሡ እኩል የልጅቷን መልስ አሰፍስፌ እየጠበኩ እያለ ረዳቱ "አባ ጠጋ ጠጋ በሉናማ አስቀምጧቸው" አለ። ቱ ይሄ ምቀኛ የሚባል ነገር በየሄድኩበት አጃቢየ ሆነ እኮ .......ምን አለበት አሁን አሠልችውን የመኪና መንገድ ለብቻየ በማያልቅ ሀሳብ እየናወዝኩ ከምሄድ ይህን የመሠለ ትዕይንት ብኮመኩምበት።............(ያው ለብቻየ ማሰብን ጠልቼው ሳይሆን ከነበረን የተሻለ ነገር ስናገኝ ሸርተት እንል የለ ....እንደዛ በዛ ላይ የኔ ሀሳብ እኔው ጋ ነው በፈለኩት ሰዐት መዥረጥ አድርጌ መትጋት ነው ህእ)።ልጁ በንዴት ገፍቶኝ ወደእኔ ተጠግቶ ቁጭ አለ።ምን አለበት ወርዶ ቢያሳልፋቸው አረገፈኝ እኮ።አይጥ በበላ.....ያው ይሄንም ታውቁት የለ።
ጅንጀናው የተደናቀፈበት ወጣት ባሽቀነጠረኝ ጊዜ ነበር በስተግራየ ከጆሮው ማዳመጫ ሰክቶ ርዕሱ የማይታየኝን መፅሀፍ እያነበበ ያለ ሌላ ወጣት እንዳለ ያስተዋልኩት።ወይ መሠጠት!.......እኔ የፈለገው ነገር ይሁን የሚታይ ነገር ባለበት፣ሰው የሚበዛበት ቦታ ላይ ተጠሙኜ ማንበብም ማዳመጥም አልችልም።በቃ አይኔ ከወዲያ ወዲህ እየቀላወጠ ያፍርስብኛል።
...........ከብዙ ሙከራ በኋላ ለደቂቃወች የተጎለትንባት መኪና አጣጥራ መንገዷን ጀመረች.....
አለ ገና እንቀጥላለን...........
joiN 💡
@Mahitot 💡
https://t.me/joinchat/RCoIiTkrDoOp77Kz @sheelff